ch
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

前往频道在 Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

显示更多
671
订阅者
+324 小时
+77 天
+430 天
帖子存档
“አንድ ምንም እውቀቱና ልምዱ የሌለው ሰው ዝም ብሎ መሬት ስለ ቆፈረ ብቻ ወርቅ አያገኝም፡፡ ከዚያ ይልቅ ምንም ረብሕና ጥቅም የሌለውን ድካም ያተርፋል እንጂ፡፡ ባስ ካለም የቆፈረው ጉድጓድ ተደርምሶበት ሕይወቱን ሊያጣ ይችላል፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ እንዴት እንደሚነበብና እንዴት መረዳት እንዳለበት ያለወቀ ሰውም ይህን ሰው ይመስላል፡፡” ቅዱስ ዮሐንስ  አፈወርቅ

"ጠላቴ ሆይ ብወድቅ እነሳለሁና በጨለማ ብቀመጥ እግዚአብሔር ብርሀን ይሆንልኛልና በእኔ ላይ ደስ አይበልህ" ።                            ሚክያስ 7፥8

" 44 ጥንዶች በሥርዓተ ተክሊልና በመዓስባን በአንድ ቀን ጋብቻቸውን ይፈጽማሉ "  - ማኀበሩ ለሁለተኛው ጊዜ በተዘጋጀው " የብዙኀን ጋብቻ " ፕሮግራም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓት ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ/ም 44 ጥንዶችን በኀብረት እንደሚሞሸሩ የኢትዮጵያ ጃንደረባው ትውልድ ጃን ቃና ዘገሊላ ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ። " 44 ጥንዶች በአንድ ቀን ጋብቻቸውን ይፈጽማሉ " ያለው ማኀበሩ፣ ፕሮግራሙ እንደ ሺሕ ጋብቻ አይነት ሆኖ ግን የቤተክርስቲያንን ስርዓት በጠበቀ መልኩ የሚከናወን የሰርግ መርሃ ግብር መሆኑን አስረድቷል። ጥንዶቹ እያንዳንዳቸው 20 ቤተሰቦቻቸውን በሰርጋቸው ቀን ምሳ እንደሚጋብዙ፣ በግብዣው 1,500 ሰዎች ይገኛሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ፣ ሰርጉ ጦር ኃይሎች አካባቢ በሚገኘው ቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን እንደሚፈጸም ተመልክቷል። ከሙሽሮቹ ቀለበትና ልብስ ውጭ የሰርጉ ወጪ በማኀበሩና በእስፖንሰሮች እንደደተሸፈነ፣ የፕሮግራሙ ዓላማ " ቤተ ክርስቲያን ልጆቿን የምትድርበት ቀን ክሬት በማድረግ " ወጣቶች በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ጋብቻቸውን እንዲፈጽሙ ለማድረግ እንደሆነ ተብራርቷል። ከዚህ ባሻገር ጥንዶቹ ከጋብቻ በኋላም በኢኮኖሚም ሆነ በማኀበራዊ ሕይወት ትስስር ለመፍጠር እንዲችሉ ማድረግ የፕሮግራሙ ዓላማ መሆኑ ተመልክቷል። ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ ይህ አይነቱ ፕሮግራም በሥዓተ ተክሊልም ሆነ በመዓስባን ለሚጋቡ ሙሽሮች ቅድሚያ የንስሃ አባት ሊኖራቸውና የትዳር ሥርዓትን ጭምር በጽሞና ሊማሩ እንደሚገባ የቤተ ክርስቲያኗ አስተምህሮ ያስረዳል፤ ሙሽሮቹ ይህን ቅድመ ሁኔታ አሟልተዋል ? ሲል ማኀበሩን ጠይቋል። ምዝገባ የተደረገው ማኀበራዊ ሚዲያ እንደሆነ፤ አጠር ያለ ገለጻ ተሰጥቷቸው እንደሚመጡ እንደተነገራቸው፣ ንስሃ አባት እንዳላቸውና እንደሌላቸው ተረጋግጦ የሌላቸውን ንስሃ አባት እንዲይዙ እንደተደረገ በመግለጽ ማኀበሩ ምላሽ ሰጥቷል። " በሥርዓተ ተክሊልና በመዓስባን የሚያጋቡ ጥንዶች ተለይተዋል። ስለጋብቻ ብቻ ሳይሆን ስለአጠቃላይ የትዳር ሕይወት፣ የልጆች አስተዳደግ፣ ስለስብዕናና ተግባቦት በተለያዩ መምህራን አንድ ወር ሙሉ ኮርስ ወስደዋል። ከመጀመሪያውም መሠረታዊ የሃይማኖት እውቀት ያላቸው ናቸው " ተብሏል። አቅም ስለሚፈትን ቢያንስ በየሁለት ዓመቱ " የብዙኅን ጋብቻ " እንደሚዘጋጅ፣ ፕሮግራሙን ያዩ በቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ያልተጋቡ ወገኖች እድሉ እንዲመቻችላቸው እየጠየቁ በመሆኑ፣ ንስሃ አባት ይዘው ሥጋወደሙ የሚቀበሉበትን የጋራ የቁርባን መርሃ ግብር ለማዘጋጀት በመስከረም 2 ቀን 2018 ዓ/ም እንደታቀደም ማኀበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግሯል።

✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿 "በክርስቶስ  ፊት ቆመህ በምትጸልይበት ጊዜ እንዳታፍር በሦራ ሁሉ የስጋ ንጽሕና ገንዘብ አድርግ"             ማር ይሳሐቅ "በራስ ጽድቅ አትታመን ለላፈው አትጨነቅ ይልቁኑ አንደበትህንና ሆድህን ግዛ"       አባ እንጦንስ

#EOTC " መንግሥት ሦስቱ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ሀገር እንዲገቡ በመፍቀዱና ተግባራዊ ምላሽ በመስጠቱ ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን " - ቋሚ ሲኖዶስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የሦስቱ የብፁዓን አባቶችን ወደ ሀገር መግባት በተመለከተ መግለጫ አውጥቷል። ቋሚ ሲኖዶስ በመግለጫው ፥ " በውጭ አህጉረ ስብከት ተመድበው ሐዋርያዊ አገልግሎታቸውን በመፈጸም ላይ የሚገኙት ፦ - ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ፤ - ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ (ዶ/ር) የሰሜን ካሊፎርኒያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፤ - ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የጆርጅያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ወደ ሀገር ቤት በመግባት ዓመታዊ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤን እንዲሳተፉ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በቅዱስ ሲኖዶስ በኩል ጥያቄ አቅርባ ነበር " ብሏል። " መንግሥትም ሀገራዊ ተቋማትን ለማጠናከር ያለው ቁርጠኝነት የጸና መሆኑን በገለጸበት መግለጫ እንደተመለከትነው የሀገራችንን ሰላም ለማጽናት፤ የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን የታሪክ ገጽታ ለመጠበቅ ተቀራርቦ መነጋገር የተሻለ መፍትሔ መሆኑን ተረድቶ ሦስቱ ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ሀገር ገብተው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤን እንዲሳተፉ መፍቀዱን ተረድተናል " ሲል ገልጿል። " በመሆኑም መንግሥት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ያቀረበችውን ጥያቄ ተቀብሎ ሦስቱ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ወደ ሀገር እንዲገቡ በመፍቀዱና ተግባራዊ ምላሽ በመስጠቱ ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን " ብሏል። ቋሚ ሲኖዶስ፥ " ወደፊትም እግዚአብሔር በሰጠን ምድር፤ አባቶቻችን ባቆዩልን ሀገር አስተማማኝ ሰላም እንዲኖርለሀገራችንና ለሕዝባችን በሚጠቅሙ ጉዳዮች ላይ ግንኙነታችንን በማጠናከር በጋራ ለመሥራት ዝግጁዎች መሆናችንን እንገልጻለን " ሲል አሳውቋል። ጥፋታቸው ምን ነበር???

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨        ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊ 🔖በዚህች ዕለት ከ72ቱ አርድእት አንዱ የሆነ ወንጌላዊ፥ ሐዋርያ፥ ሰማዕት፤ ዘአንበሳና ርዕሰ ሊቃነ ዻዻሳት የተባለ ቅዱስ ማርቆስ በሰማዕትነት ግብፅ ውስጥ ዐርፏል። 🔖ቅዱስ ማርቆስ እናቱ ማርያም አባቱ አርስጦቦሎስ ይባላሉ። በልጅነቱ ኦሪትንና የዘመኑን ጥበብ ሥጋዊ በሚገባ ተምሮ ክርስቶስን ከቤተሰቦቹ ጋር ተከትሏል። 🔖የመጀመሪያ ስሙ ዮሐንስ ሲሆን ከ120ው ቤተሰብ በዕድሜ በጣም ትንሹ (20 ዓመት) እርሱ ነበር። ለ3 ዓመታት ከጌታ እግር ሥር ተምሮ በበዓለ ሃምሳ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ተቀብሎ ለሐዋርያዊ አገልግሎት ብዙ ደክሟል። 🔖በተለይ የግብፅና የኢትዮዽያ ቤተ ክርስቲያን አባት ነው። ክህነትን ያገኘነው ከእርሱ ነውና። ቅዱስ ማርቆስ 16 ምዕራፍ ያለውን ወንጌሉን ሲጽፍ ኪሩብ ገጸ አንበሳ በቀኙ፥ ሊቀ ሐዋርያት በግራው ሆነው ይራዱት ነበር። 🔖ቅዱሱ ከቅዱስ ጳውሎስ፥ ከቅዱስ በርናባስና ከቅዱስ ጴጥሮስ ጋር ተጉዟል። ከብዙ ስቃይና መከራ በኋላ ሰሜን አፍሪካ አካባቢ በዚህ ቀን [በ60 ዓ.ም. አካባቢ] አረማውያን ገድለውታል። 🔖ቤታቸው (ጽርሐ ጽዮን) የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን ስትሆን ይህች ቤት ምሴተ ሐሙስ የቁርባን ሥርዓት ተሠርቶባታል፥ መንፈስ ቅዱስ በ50ኛው ቀን ለ120ው ቤተሰብ ወርዶባታል፥ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ግንዘትም ተከናውኖባታል። እግዚአብሔር ከሐዋርያዊው ቅዱስ                      ማርቆስ በረከትን ያድለን፨ ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

"የወንድማማች መዋደድ ይኑር። እንግዶችን መቀበል አትርሱ ፤ በዚህ አንዳንዶች ሳያውቁ መላእክትን እንግድነት ተቀብለዋልና።" ዕብ 13÷4

"መከራን በመከራነቱ ሳይሆን በመካሪነቱ ውደደው።"         ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

"ችግር ለራሳችን እንድንጸልይ ያነቃቃናል፤ ፍቅር ደግሞ ለሌሎች ሰዎች እንድንጸልይ ያስገድደናል"      ✦ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ✦

"እግዚአብሔር ትንሽ ይናገራል ብዙ ያደርጋል እኛ ግን ብዙ እንናገራለን ጥቂት እንሰራለን።"     ቅዱስ ሳዊሮስ

#Update ብፁዕ አቡነ ገብርኤል በመኖሪያ ቤታቸው ተአቅበው እንዲቆዩ ቋሚ ሲኖዶስ ወሳኔ አሳለፈ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ከቤተክርስቲያኗ የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ በፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር አዳራሽ የሰጡትን ትምህርትና በማኅበሩ ሚዲያ የተላለፈበትን ሁኔታ በተመለከተ በዛሬ መደበኛ ጉባኤ ተወያይቶ ለመወሰን በያዘው ቀጠሮ መሰረት ውይይት ካደረገ በኋላ ውሳኔ አሳልፏል። በዚህም ፦ 1. ፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር በተለያዩ ጊዜያት ከቅድስት ቤተ ክርስቲያኗ አስተምህሮ ውጪ በሚዲያው ያስተላለፈው የስሕተት ትምህርት የቤተክርስቲያኗን አባቶች፣ ሊቃውንቱንና መላው ሕዝበ ክርስቲያኑን ያሳዘነ በመሆኑ በማህበራት ምዝገባ ክትትልና ቁጥጥር መምሪያ በኩል ጊዜያዊ የእገዳ ደብዳቤ እንዲደርሰው እና በመምሪያው በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ክትትል እንዲደረግ ሆኖ በጉዳዩ ላይ የመጨረሻ ውሳኔ መስጠት ይቻል ዘንድ 5 አባላት ያሉት ኮሚቴ እንዲቋቋም አድርጓል። ቋሚ ሲኖዶስ ያቋቋማቸው አጣሪ ልዑካን አጠቃላይ የማህበሩን ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ እና በሚዲያው ያስተላለፋቸውን የስህተት ትምህርቶች በተመለከተ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት እና ከማህበራት ምዝገባ፣ ቁጥጥርና ክትትል መምሪያ ጋር በመነጋገር በሚገባ መርምርውና አጣርተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከውሳኔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርቡ ወስኗል። 2. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል “ ማርያም ቤዛዊተ ዓለም ” አትባልም በማለት ከቤተ ክርስቲያኗ የነገረ ማርያም አስተምህሮ ውጪ የሰጡት ሕጸጽ ያለበት ትምህርት በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በሚገባ ተመርምሮና ተጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጋር ለቋሚ ሲኖዶስ በአስቸኳይ እንዲቀርብ ብፁዕነታቸውም ጉዳዩ ተጣርቶ የመጨረሻ ውሳኔ እስኪያገኝ ድረስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በተአቅቦ እንዲቆዩ ወንሷል። 3. ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝደንት እና ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካሊፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ያስተላለፏቸው የስሕተት ትምህርቶችና በሌሎችም መምህራን የተላለፉ ነቀፋ ያለባቸው ትምህርቶች ካሉ የሊቃውንት ጉባኤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ አስተምህሮ አንጻር በሚገባ መርምሮና አጣርቶ ከመፍትሔ ሐሳብ ጭምር በአጭር ጊዜ ውስጥ ለቋሚ ሲኖዶስ እንዲያቀርብ ወስኗል። 4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኝ ብዙኃን ስርጭት ድርጅት ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማህበር ሚዲያ የአየር ሰዓት የሰጠበትን ዝርዝር ሁኔታና ከማኅበሩ ጋር በተያያዘ አየር ላይ ያዋላቸውን ትምህርቶች የሚያሳይ ሪፖርት እንዲያቀርብ እንዲደረግ ወስኗል። መረጃው የቤተክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።

" ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።” — ማቴዎስ 10፥41 #ታላቅ_መንፈሳዊ_የንግስ_ክብረ_በዓል_ጥሪ በአሰላ ደብረ መድሐኒት መድኋኔዓለም ካቴድራል ቤተክርስቲያን #የፃድቁ_አባ
" ጻድቅንም በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ ይወስዳል።”   — ማቴዎስ 10፥41
#ታላቅ_መንፈሳዊ_የንግስ_ክብረ_በዓል_ጥሪ
በአሰላ ደብረ መድሐኒት መድኋኔዓለም ካቴድራል ቤተክርስቲያን
#የፃድቁ_አባታችን_የአቡነ_እስትፋሰ_ክርስቶስ_አመታዊ_የንግስ_ክብረ_በአል_የፊታችን_እሁድ_ሚያዚያ_9_በታላቅ_ድምቀት_ይከበራል ።
እርሶም ከፃድቁ አባታችን ረድኤት በረከት ይካፈሉ ስትል እናት ቅድስት ቤተክርስቲያ ጥሪዋን ታስተላልፋለች።
#ዳግም_ትንሳኤን_በደብረ_መድሐኒት_ፈፅሞ_አይርም

#Update ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ተሰጥቶ የነበረው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው ታገደ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ከዚህ ቀደም በቤተክርስቲያን መሰረት እ
+1
#Update ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ተሰጥቶ የነበረው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው ታገደ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ከዚህ ቀደም በቤተክርስቲያን መሰረት እምነት፣ ሥርዓተ አምልኮና ትውፊት አክብሮ በቤተክርስቲያን ዙሪያ ዘገባ እንዲያከናውን ለፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን ፍቃድ መሰጠቱ ይታወሳል። ሆኖም ግን በፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በዕለተ ስቅለት " ቅድስት ድንግል ማርያም ቤዛዊተ ዓለም አትባልም " በሚል ርእስ  የተላለፈው ትምህርት ውዝግብ በማሰነሳቱና ቋሚ ሲኖዶስ በጉዳዩ ዙሪያ ተወያይቶ ውሳኔ ለመስጠት ለረቡዕ ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ የያዘ በመሆኑና ጉዳዩ በሚገባ ተጣርቶ ውሳኔ እስከሚሰጠው ድረስ ከመምሪያው ለፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን የተሰጠው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው መታገዱን የቤተክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ዛሬ አሳውቋል። በሌላ በኩል የሕዝብ ግንኙነት መምሪያው ለፍኖተ ጽድቅ በጻፈው ደብዳቤ " ማኅበሩ ከተቋቋመበት ዓላማ ውጭ ርቱዕ እምነትን ከሥነ ምግባር ጋር ይዞ የሚኖረውን ሕዝበ ክርስቲያን ያሳዘነ፣ እናት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንን ለጠላት መሳለቂያ እንድትሆን ያደረገ ከቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ጋር የሚቃረን ' እመቤታችን ቤዛ አይደለችም ' የሚል ጤናማ ያልሆነ ትምህርት ሚያዝያ 10 ቀን 2017 ዓም በማኅበሩ ሚዲያ ማስተላለፉን ተመልክተናል " ሲል ገልጿል። በዕለተ ስቅለት የተላለፈው ትምህርት ቪዲዩ በአስቸኳይ ከማኅበሩ ዩቲዩብ እንዲወርድ እንዲያደርግና በዕለቱ የተላለፈውን ትምህርት ሙሉ ቪዲዮ ቅጂ ለመምሪያው እንዲያቀርብ እንዲሁም ማብራሪያ እንዲሰጥ ጥብቅ መመሪያ ሰጥቷል።

ብቻህን ማሰብ ስትጀምር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የብቻችን የሆነ ትምህርት የለም። በማኅበር እንማራለን ፤ በማኅበር እንጸልያለን ፤ አንድ ሆነን የተዘጋጀልንን ማዕድ ቅዱስ ቊርባን እንቀበላለን ፤ በመጨረሻም የተዘጋጀልንን የተስፋ አገር እንቀበላለን። ክርስቶስ ያስተማረ በጉባኤ ነው ፤ ስለዚህም ቤተ ክርስቲያን ምንጊዜም ጉባኤአዊት ሆና ትቀጥላለች እንጅ ማንም ምንም ቢሆን የራሱን ትምህርት አምጥቶ ሊያስተምር የሚችልበት ዕድል የለውም። የብቻው የሆነ ክርስቶስ ስለሌለው የብቻው የሆነ ትምህርትም ሊኖረው አይችልም። ብቻህን ማሰብ ከጀመርህ ከጉባኤው የተለየ አስተምህሮ ማምጣትህ ስለማይቀር “ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንተ ላዕለ ኵሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት” የሚለውን የሃይማኖት መግለጫ አስቀድመን እንድናውቅ መደረጉ ስለዚህ ነው። በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚኖር ማንም ቢሆን ቤተ ክርስቲያን ካስተማረችው ትምህርት የወጣ እንደሆነ መዐርጉ ፣ የዕውቀት ደረጃው ፣ የወገኑ የሀብቱ ብዛት ሊያድነው አይችልም። በመጀመሪያ ከቃሉ የሰሙ ሰዎች “የተናገርኸውን ትምህርት አስበኸው ከሆነ አትናገረው ተናግረኸውም ከሆነ አትድገመው” ብለው ይመክሩታል። ምክራቸውን ሰምቶ በዚህ ካቆመ ይተዉታል፤ ምክራቸውን አልሰማ ብሎ ከቀጠለ ግን ወደ መምህራን ያደርሱታል፤ መምህራንንም አልሰማ ካለ ወደ ጉባኤ {ሲኖዶስ} ይቀርባል። ሲኖዶሱን ካልሰማ ተወግዞ ይለያል። በሰሞኑ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል የሰጡትን ትምህርት በቪዲዮ አንዲት ወዳጄ ልካልኝ ተመለከትሁት፤ ምናልባት ከባልንጀሮቻቸው ጋር ተማክረውበት ከበታቾቻቸውም ጋር ተከራክረውበት የነበረ ጉዳይ ከሆነ “አስበኸው ከሆነ አትናገረው ተናግረኸውም ከሆነ አትድገመው” ሊሏቸው ይገባ ነበር። አሁን ግን በሹክሹክታ ሳይሆን በሰገነት ላይ የተሰበከ የስሕተት ስብከት ስለሆነ ጉዳዩ ከዚህ ያለፈ ይመስለኛል። ከረፈደም ቢሆን ባየሁት መረጃ መሠረት ብዙ ሊቃውንት ሀሳብ ሰጥተውበታል ፤ ይሄ ለብፁዕነታቸው መልካም ዕድል ነው ብየ አምናለሁ። ሀሳባቸውን የገለጹ ሊቃውንት ቤተ ክርስቲያን በሊቅነታቸው የምታምንባቸው ሊቃውንት እንደመሆናቸው መጠን ምክሩን ይቀበሉታል ብየ ስለማምን ነው። ሀሳቡን ሳይንቁ በቶሎ በሰገነት ላይ ያጠፉትን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት በሰገነት ላይ ወጥተው ቤተ ክርስቲያኒቱን ይቅርታ ሊጠይቁ ይገባል። “አትደንግጡ” ብለውናል እንዳንደነግጥ ያድርጉን። ይህንን ትምህርት አባቶቻችን አልነገሩንም መጻሕፍቶቻችን ላይ ተጽፎ አላገኘነውም። ብፁዕ ሊቀ ጳጳሱ መጻሕፍቶቻችንን አባቶቻችንን ተቃውመዋል።  ዛሬ መልስ አልጽፍም፤ ምክንያቱም መልሱን ከብፁዕነትዎ ስለምጠብቅ ነው። ሊቀ ሊቃውንት ስምዓ ኮነ መልአክ