ch
Feedback
ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

前往频道在 Telegram

በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው። የቴሌግራም ቻናል:-  @Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- @FinoteWongel27 የቲክቶክ ገፅ:- https://www.tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- https://www.youtube.com/@Finote_Wongel ©ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት

显示更多
669
订阅者
-124 小时
+37 天
无数据30 天
帖子存档
🎲 Quiz 'ፍኖተ ወንጌል ልዩ መንፈሳዊ የጥያቄና መልስ ውድድር "start the quiz"የሚለውን ይጫኑ"i am ready "ሲጫኑ ጥያቄው ይጀምራል። መልካም ዕድል🛎🛎🛎' 🖊 6 questions · ⏱ 30 sec

ልዩ መንፈሳዊ በፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት እየተዘጋጀ የሚቀርብ የጥያቄ እና መልስ መርሐ ግብር። ዘወትር በየሳምንቱ አርብ ምሽት ከ2:00 ⏰ ጀምሮ እስከ 4:00 ⏰ ድረስ ወደ እናንተ ይደርሳል። ይሳተ
ልዩ መንፈሳዊ በፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት እየተዘጋጀ የሚቀርብ የጥያቄ እና መልስ መርሐ ግብር።
       ዘወትር በየሳምንቱ አርብ ምሽት ከ2:00 ⏰ ጀምሮ እስከ 4:00 ⏰ ድረስ ወደ እናንተ ይደርሳል።                 ይሳተፋ! ለኦርቶዶክሳውያን ሼር በማድረግ ይጋብዙ! የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475

የጳጉሜን ወር በጸሎት በንስሓ ተወስነን ወደ አዲሱ ዓመት የምንሸጋገርባት ድልድይ ናት፡፡ ከዚህም የተነሳ  እግዚአብሔር የፈቀደላቸው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ጸሎት በመጸለይ ጸበል በመጠመቅ ያስቧታል፡፡  በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ በዚህ በጳጉሜን ወር የምንጾመው ሲሆን መሠረት የሚደረገውም ጾመ ዮዲት ነው፡፡ የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው ነው፡፡ ይህን መሠረት አድርገው ሕዝቡ ሳይቀር “ጳጉሜን ዕድሜ ትሰጠናለች፤ በኋላም ታድነናለች” ብለው ጾም ይጾሙባታል፡፡ (ምንጭ-ቅዱስ መልከ ጸዴቅ ድርሳን)፤ በሀገራችንም ንግሥት ዘውዲቱ እና ምኒልክ የጾም ሥርዐት ይፈጽሙባት ነበር፡፡ ሌሎችም ሽማግሌዎችና ባልቴቶች አክብረው ይጾሙባታል፡፡ የጳጉሜንን አቆጣጠር አንዱ ከቀን ጋራ ሲያደርገው፣ ሌለኛው ደግሞ ከወር ጋራ ቢያደርገውም በሁሉም አቆጣጠር ውስጥ ሕያዊት ሆና መገኘቷ የታወቀ ነው፡፡ የዐውደ ዓመት መሸጋገሪያ ናት፡ ይህም ጳጉሜን ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት፣ ከክረምት ወቅት ወደ ጸደይ መሸጋገሪያ ናት፡፡ ጳጉሜን የዓመቱ መጨረሻ ወር ናት፡፡ ወርኃ ጳጉሜ አዲሱን ዓመት ለመቀበል የዝግጅት ጊዜ ናት፡፡ ስለሆነም አዲሱ ዘመን የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የልማት፣ የመተሳሰብ ዘመን እንዲሆንልን በጾምና በጸሎት ማሰብ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ነገረ ምጽአት የሚታሰብባት ናት የጳጉሜን ወር የነገረ ምጽአት የሚታሰብባት ስትሆን ምጽአት ማለት የጌታን መምጣት የሚያስረዳ በመሆኑም ቤተ ክርስቲያን የጌታን ምጽአት በዓመት ሁለት ጊዜ ታስታውሳለች፤ ይኸውም በጳጉሜን ወርና በጌታ ጾም እኩሌታ (በደብረ ዘይት) ነው። ቅዱስ ዳዊት ”እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል፤ ዝም አይልም፤ እሳት በፊቱ ይነዳል፤” እንዲል፤ (መዝሙረ ዳዊት ፵፱ ፣ ፪-፬)፡፡  ይህ ስለ ነገረ ምጽአት ያስረዳል፡፡ ይህም ጳጉሜን ከአሮጌው ዓመት ወደ ዐዲሱ ዓመት፣ ከክረምት ወቅት ወደ ጸደይ ወቅት መሸጋገሪያ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ፣ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ፣ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ናትና ነው፡፡ ጳጉሜን የክረምቱ ማብቂያ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም በመጨረሻው ዘመን መከራ የሚበዛበት የዚህ ዓለም ማብቂያ ናት፡፡ ወርኃ ጳጉሜን አዲሱን ዓመት ለመቀበል የዝግጅት ጊዜ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ጻድቃን ዐዲሲቷን ምድር (መንግሥተ ሰማያትን) ለመውረስ ተዘጋጅተው “ኑ የአባቴ ብሩካን ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀላችሁን የእግዚአብሔር መንግሥት ውረሱ” የሚባሉባት ቀን ናት፡፡ የጌታ አመጣጥ ሳይታሰብ ነውና በተሰጠን ጸጋ ቅዱስ አምላካችንን እያመሰገንን ተዘጋጅተን እንድንጠብቀው  የድንግል ማርያም ልጅ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይርዳን፤ ቀጣዩ ዘመንም ቃሉን ፈጽመን መልካም ፍሬ የምናፈራበት ዓመት ይሁንልን፤ አሜን !!! ©ማኅበረ ቅዱሳን

🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ጳጉሜን የሚለው ስያሜዋ ግን “ሄፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ መሆኑን አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ተነግሯል፡፡ “ኤፓጉሜኔ” ማለት ጭማሪ ማለት ነው፡፡ በግእ
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ጳጉሜን የሚለው ስያሜዋ ግን “ሄፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ መሆኑን አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ተነግሯል፡፡ “ኤፓጉሜኔ” ማለት ጭማሪ ማለት ነው፡፡ በግእዝ ቋንቋችን ተውሳክ ማለት ነው፡፡ ተውሳክ ማለት ተጨማሪ ማለት ነው፡፡ “ወሰከ - ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው፡፡ (ምንጭ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፱፻፭)፡፡ ምዕራባዊያኑ ጳጉሜን  ተጨማሪ ቀን አድርገዋታል፡፡ እኛ ግን የወር ተጨማሪ አድርገናታል፡፡ በጽርዕ ኤፓጉሜኔ ትባል እንጂ ሊቃውንት ግን ተረፍ ይሏታል፡፡ ጳጒሜን የአሮጌው ዓመት ማብቂያ የአዲሱ ዓመት መንደርደሪያ ዕለት እንደሆነች የክርስቶስ ልደትም የዓመተ ፍዳ ማቆሚያ የዓመተ ምሕረት መጀመሪያ በመሆኑ ዕለታቸው ራሱ በተመሳሳይ ቀን ተቀምሮ ይውላል፡፡ የጳጉሜን ወር ‹‹የምሕረት ወር›› ስለመባሏ፡- ኢትዮጵያ በዓለም ብቸኛዋ የ፲፫ ወራት ጸጋ ባለቤት ስትሆን የጳጉሜን ወርም በኢትዮጵያውያን ዘንድ የምሕረት ወር ተብሎ ይታመናል። በተለይም  በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ጸሎት የሚያርግበት ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበት የምሕረት ወር መሆኑን ታስተምራለች፡፡ በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት መሠረት ምእመናኑ በጳጉሜን ጸበል በመጠመቅ ድኅነት በማግኘታቸው የምሕረት ወር መሆኑን ምእመናን ያብራራሉ፡፡

ምክረ አበው እግዚአብሔር_የሚወዳችሁ_እናንተም_የምትወዱት ልጆቼ! አዲሱ ዓመት የእውነት አዲስ ዓመት እንዲኾንላችሁ ካሻችሁ ነፍሳችሁን ከኀጢአት ቀንበር አላቋት እንጂ ድጋሜ በኀጢአት ሸክም አትጫኗት፡፡ አሮጌው ዓመት እንዳለቀ ስታዩ እግዚአብሔርን አመስግኑት፡፡ 🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼 ወደሌላ ዘመን አሸጋግሯችዋልና እግዚአብሔርን አመስግኑት፡፡ ልቡናችሁንም ውቀሱት፡፡ በዕሜአችሁ ስንት ጊዜ እያለፈ እንደ ኾነ እያሰባችሁም ራሳችሁን እንዲህ ብላችሁ ጠይቁት፡- “ቀናት እየሮጡ ነው፡፡ ዓመታቱም እየነጐዱ ነው፡፡ የዕድሜዬ መንገድም እየተጋመሰ ነው፡፡ ታዲያ ምን በጐ ምግባር ያዝኩ? ከዚህ ምድር የማልፍበት ቀን እየቀረበ ነው፡፡ ታዲያ ምን የጽድቅ ሥራ ሠራሁ? በዚህ ዕድሜዬ መሥራት የነበረብኝ ምግባር ትሩፋት ዕድሜዬ ሲገፋ ማድረግ አልችልም፡፡ ታዲያ ዕድሜዬ ሲገፋ ማድረግ የማልችላቸውም የጽድቅ ሥራዎች (ፆም፣ ጸሎት፣ ስግደት፣ አገልግሎት፣… ዕድሜ ሲገፋ ይከብዳሉና) እንዳቅሜ እያደረግኩ ነውን?” በማለት ልቡናችሁን ጠይቁት፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27

"ከእነዚህ ከታናናሾቹ ወንድሞች ለአንዱ ያደረጋችሁት ሁሉ ለእኔ አደረጋችሁት።" ማቴ 25:40 በዓመት አንድ ቀን በፈለጉት ወርና እለት ነድያኑን መግበው በረከት ማግኘት ከፈለጉ በሚከተሉት አድራሻዎች
"ከእነዚህ ከታናናሾቹ ወንድሞች ለአንዱ ያደረጋችሁት ሁሉ ለእኔ አደረጋችሁት።" ማቴ 25:40
       በዓመት አንድ ቀን በፈለጉት ወርና እለት ነድያኑን መግበው በረከት ማግኘት ከፈለጉ በሚከተሉት አድራሻዎች ያገኙናል:-       :- የሰንበት ት/ቤቱ ፅህፈት ቤት ጠዋትና ማታ       :- በሰንበት ት/ቤቱ ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel 🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel 🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475 ▭▭▭▭▭▭▭▭ T.me/FinoteWongel1 ▭▭▭▭

"ከእነዚህ ከታናናሾቹ ወንድሞች ለአንዱ ያደረጋችሁት ሁሉ ለእኔ አደረጋችሁት።" ማቴ 25:40 በዓመት አንድ ቀን በፈለጉት ወርና እለት ነድያኑን መግበው በረከት ማግኘት ከፈለጉ በሚከተሉት አድራሻዎች
"ከእነዚህ ከታናናሾቹ ወንድሞች ለአንዱ ያደረጋችሁት ሁሉ ለእኔ አደረጋችሁት።" ማቴ 25:40
       በዓመት አንድ ቀን በፈለጉት ወርና እለት ነድያኑን መግበው በረከት ማግኘት ከፈለጉ በሚከተሉት አድራሻዎች ያገኙናል:-       :- የሰንበት ት/ቤቱ ፅህፈት ቤት ጠዋትና ማታ       :- በሰንበት ት/ቤቱ ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel 🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel 🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475 ▭▭▭▭▭▭▭▭ T.me/FinoteWongel1 ▭▭▭▭

​ 🌿🍁✨🌿🌿🍁✨🌿🌿🍁✨🌿🌿🍁✨🌿
“ወንድማችሁን ለመግፋት ሳይሆን ለማዳን ችላ አትበሉ”
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ከያዕቆብ መልእክት /ያዕ.5፡13-20/ ጋር በተያያዘ በሌላ መጽሐፍ ከተናገረው የተወሰደ፡ መጠነኛ ለውጥ ተደርጎበታል። “ወንድሞቼ! ከእናንተ መካከል አንድ ዐይነ ሥዉር ሰው ወደ ጕድጓድ ገብቶ ሊወድቅ ሲል እጁን ዘርግቶ የማይደግፈው ማን ነው? ታድያ ወንድሞቻችንና እኅቶቻችን በልቡናቸው ታውረው ወደ ሲዖል ጕድጓድ ለዘለዓለም ሲወድቁ እንደምን እጃችን የበለጠ አይዘረጋም? ወገኖቼ! በነፍስም በሥጋም የታመመ ሰውን ስታዩ “ይህ የእኔ ሥራ አይደለም፤ የቀሳውስትና የመነኰሳት ሥራ እንጂ፡፡ ምክንያቱም ሚስት አለችኝ፤ ልጆችንም አሳድጋለሁ” አትበሉ፡፡ እስኪ ምሳሌ መስዬ ልጠይቃችሁ፤ እናንተም መልሱልኝ፡፡ አንድ ትልቅ በወርቅ የተሞላ ሳጥን ወድቆ ብታዩ “ይህ እኔን አይመለከተኝም፤ ሌሎች መጥተው ያንሡት እንጂ” ትላላችሁን? ግራ ቀኛችሁን አይታችሁ በፍጥነት የምታነሡት አይደለምን? እንግዲያውስ ይህ ወደ ዘለዓለም ጕድጓድ እየወደቀ ያለው ወንድማችሁም ከዚያ ወርቅ በላይ ውድ የእግዚአብሔር ሀብት ነውና አንሡት እንጂ የበለጠ እንዲወድቅ አትግፉት፡፡ እግዚአብሔር ይህን በተመለከተ በአፈ ያዕቆብ እንዲህ ብሏልና፡- “ወንድሞቻችን ሆይ! ከእናንተ ወገን ከጽድቅ ወጥቶ የበደለ ቢኖር መክሮ አስተምሮ ከበደሉ የመለሰው ቢኖር ራሱን አንድም ወንድሙን ከሞት እንዳዳነ ይወቅ፡፡ የራሱን አንድም የወንድሙን ብዙ ኃጢአቱን እንዳስተሠረየ ይወቅ፡፡ አንድም የወንድሙን ነፍስ እንዳዳነ ይወቅ” ያዕ 5፡19-20። 📝በገብረ እግዚአብሔር ኪደ ​ 🌿🍁✨🌿🌿🍁✨🌿🌿🍁✨🌿🌿🍁✨🌿 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27

ልደቱ ለአቡነ ዘርዐ ቡሩክ(ነሐሴ 27) በትንቢት ‹‹ከአንዲት ሴት ልጅ በጸሎቱ ዓለምን የሚያድን፣ በአማላጅነቱ ነፍሳትን የሚዋጅ ልጅ ይወለዳል›› ተብሎ ከተነገረ ከብዙ ዘመን በኋላ እግዚአብሔርን የምታመልክ ስሟ ማርያም ሞገሳ የምትባል ሴት ልጅ ተወለደች:: ያችንም ሴት ልጅ እናትና አባቷ ለአቅመ ሔዋን እስክትደርስ ድረስ እግዚአብሔርን በመፍራትና በዕውቀት አሳደጓት:: ዕድሜዋም ለትዳር ሲደርስ እናትና አባቷ እግዚአብሔርን ለሚፈራ ስሙ ደመ ክርስቶስ ለሚባል ሰው ዳሯት:: በዚያን ጊዜ ስልጣኑ ከሰማይ የሆነና ክብሩ እጅግም የሆነ ልጅ ጸነሰች:: እርሱን ከጸነሰች ጊዜ ጀምሮ እስክትወልደው ድረስም ልብሷን አትታጠቅም፤ ለወገቧም መቀነትን አትፈልግም ነበር:: በእናቱ ማህፀን ተአምራትን እንዳደረገ እንደ ዘካርያስ ልጅ እንደ ዮሐንስ በደስታ እየሰገደ በእናቱ ማህፀን ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደርግ ነበርና:: እርሷም የመውለጃዋ ቀን እስኪደርስ በጾምና በጸሎት ተወስና ስታገለግል ኖረች:: በነሐሴ ፳፯ ቀን በሰው ዘንድ የተናቀ በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደ ይህን ክቡር ጻድቅ ወለደችው:: በተወለደም ጊዜ በእናትና አባቱ እንዲሁም በሀገሩ ሰዎችም ዘንድ ፌሽታ ሆነ፤ እስከ ሰባት ቀንም ድረስ ግብዣ አደረጉ:: ይህም ጻድቅ ባሕታዊ በተወለደበት (ክርስትና) በተነሳበት ቀን በካህናት አፍ ጸጋ ክርስቶስ ተባለ:: የኃጢአት ማሰሪያን ሁሉ ያስርና ይፈታ ዘንድ ጵጵስና በሾመው ጊዜ እግዚአብሔር ያወጣለት ሁለተኛው ስሙ ዘርዓ ብሩክ ነው:: ሦስተኛ ስሙ ደግሞ ጸጋ ኢየሱስ (በጸሎት ተደጋግሞ ብዙ ይገኛል) ይባላል:: ከልደቱ በኋላ ያንንም ሕፃን አባቱና እናቱ እስከ ሰባት ዓመቱ ድረስ እግዚአብሔርን በመፍራት፣ በአምልኮት እና በዕውቀት አሳደጉት:: ሰባት ዓመት ሲሆነው የሚያልፈውንና የሚጠፋውን ዓለም ሁሉ እንዳያይ ዓይኖቹ ታወሩ:: የልጃቸው ዓይኖች በጠፉበት ቀን እናትና አባቱ አዘኑ፤ ታውሮም በቤታቸው አንዲት ዓመት ኖረ:: ከተወለደ ሰባት ዓመት ሲሆነው ረቡዕና ዓርብን መጾም ጀመረ:: እናትና አባቱም በተወለደ በሰባት ዓመቱ ሲጾም ባዩት ጊዜ ሀዘናቸው ወደ ደስታ ተለወጠ:: ከዚህም በኋላ በእኒህ እንዲተዳደር ብሎ እንደተናገረው መጽሐፍትን ቢማር ያለበትን ነውር እንደሚሰውር እና በእነዚህም እንዲተዳደር አውቀው የቤተ ክርስቲያንን መጽሐፍት ሁሉ እንዲያስተምረው ለመምህር ሊሰጡት ተማከሩ:: እርሱ ሲማር እግዚአብሔር ብርቱ መከራንና የሚያስጨንቅ በሽታ አመጣበት:: አባትና እናቱም በልጃቸው ላይ የሆነውን ነገር አይተው ዓይኖቹ የታወሩ ‹‹ይህ ልጃችን በምን ይተዳደራል? በዚህ ዓለምስ አኗኗሩ እንደምን ይሆናል?›› ብለው ታላቅ ሀዘንን አዘኑ:: እግዚአብሔርም ከእርሱ (ከእግዚአብሔር) በቀር መጻሕፍትን ሁሉ ከማንም እንዲማር እንዳልፈቀደለት ፈጽመው አስተውለው አላወቁም ነበር:: ይህ ትንሽ ሕፃን ግን ለአባትና ለእናቱ ሲታዘዝ (ሲያገለግላቸው) ኖረ:: ሐዋርያትም በሲኖዶሳቸው እንዳዘዙት ከተወለደ ፲፪ ዓመት ሲሆነው ይጾም ነበር:: ዐሥራ ሁለት ዓመት ከሆነውም በኋላ የጌታችንን ጾም አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡ አምላክን የወለደች የእመቤታችን ማርያምን ጾም፣ ሐዋርያት የሠሩትን ጾም፣ ሁሉ መጾም ጀመረ:: አባትና እናቱም በዐሥራ ሁለት ዓመቱ ጾሙን ሁሉ ሲጾም አይተው ተደሰቱ:: ይህ ሕፃን ልጃቸው በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ እንደጸና አላወቁም:: እግዚአብሔር አምላክም ለዚህ ጻድቅ አባት መጻሕፍተ ብሉያትንና መጻሕፍተ ሐዲሳትን፤ መጻሕፍተ ሊቃውንትንና መጻሕፍተ መነኮሳትንም፤ አዋልድ መጻሕፍትንም፤ የመላእክትንና የሰውን ነገር (ፍትህን ሁሉ፤ የማኅሌታይ የቅዱስ ያሬድንም ዜማ) ገለጠለት፤ እግዚአብሔር ይህንን ድንቅ ተአምራት ለወዳጁ ለብፁዕ አባታችን ለአቡነ ዘርዐ ብሩክ የተሰጠው ገና በልጅነቱ ነበር:: ለእኛም ፈጣሪያችን እንዲሁ ተአምራትን ያድርግልን፤ በመከራችን ጊዜ ደስታን ያሰማን፤ ለእርሱ እንደገለጠለት መጻሕፍትን ሁሉ ይግለጥልን፤ መታሰብያውን ለምናደርግ፣ ስሙንም ለምንጠራ እና በጸሎቱ ለምንማጸን ለወንዶችና ለሴቶች ልጆቹ በጻድቁ ጸሎት ነፍሳችንን ይማርልን፤ አሜን !! ምንጭ፤ ገድለ ዘርዐ ቡሩክ

ብፁዕ አቡነ አብርሃም ሊቀ ጳጳስ በተለያዩ ቦታዎች በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት ሕይወታቸውን ባጡና በተጎዱ ወገኖች የተሰማቸውን ኀዘንና የማጽናኛ መልእክት አስተላለፉ። ነሐሴ ፳፬/፳፻፲፮ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ሊቀ ጳጳስ በተለያዩ ቦታዎች በተከሰተው የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት ሕይወታቸውን ባጡና በተጎዱ ወገኖች የተሰማቸውን ኀዘንና የማጽናኛ መልእክት አስተላለፉ። ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕርዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት የኀዘንና የማጽናናኛ መልእክት በነሐሴ ወር በብዙ ቦታዎች የተፈጥሮ አደጋዎች መከሰታቸውን አስታውሰው ሕይወታቸውን ባጡ ወገኖች በእጅጉ ማዘናቸውን ገልጸዋል። ብፁዕነታቸው ቀጥለውም ጉዳቱ በጎፋ ዞን፣ ወላይታ፣በሲዳማ ፣ በምዕራብ ጎንደር በጠለምትና በመቐለ አደጋው መከሰቱን አብራርተዋል። በቅርብ አመታትን እንዲህ የመሰለ አደጋ በሀገራችን በተለያዩ ቦታዎች ተከስቶ እንደማያውቅ ያስታወሱት ብፁዕነታቸው ይህ ሰው ከሰው  መጠላቱ አልበቃ ብሎ ተፈጥሮ እንኳን ምንያልህ እንደተጣላን ማሳያ ነው ብለዋል። ይህ ዓይነቱ የተፈጥሮ መከራ የሚያስታግሰው  የሥጋዊ ቀመራችንና መላምታችን ሳይሆን   መሐሪው አምላክ እግዚአብሔር  ብቻ  መሆኑን ተረድተን ወደ እርሱ መጮህና ማንጋጠጥ ይገባል ብለዋል። በተለይም የአሮጌው ዓመት መካተቻ የመጪው አዲስ ዓመት መሸጋገሪ በሆነችው  የኢትዮጵያ ጳጉሜን ወር ቀናት ሁላችን በእውነተኛ ንስሐ፣ በተሰበረ ልብ፣ ነገርን በተው ሕሊናና ነውር በሌላው ጸሎት  ወደ እግዚአብሔር በመንበርከክ  ምሕረት ልንጠይቅ አዲስ ዓመት ልንቀበል ይገባል ብለዋል። ከዚሁ ጋር በአደጋው ምክንያቱም ለተጎዱ፣ ከሞቀ ቤታቸው፣ ከለመዱት ቀያቸው ተፈናቅለው #ስደታቸው በክረምት የሆነባቸውን ወጎኖቻችን አለንላችሁ በማለት በተግባር በተገለጠ ርኅራኄ ልንደርስላቸው ይገባል በማለት አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን  አደጋ በደረሰባቸው ቦታዎች በተለይም በጎፋ ዞን በብፁዓን አባቾች የተመራ ልዑክ በአካል ሔደው ማጽናናታቸውን ያስታወሱሰቱ ብፁዕነታቸው በሌሎች ቦታዎችም  የቤተ ክርስቲያናቸን አባቶችና ልጆች የበኩላቸውን ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል። ብፁዕ አቡነ አብርሃም አክለውም የሀገራችን ዜጎች ከተፈጥሮ ጋር እንዲህ ባለ ብርቱ የሕይወት ሰልፍ ላይ መሆናቸው እየታወቀ አሁንም ችግሮችን በሆደ ሰፊነትና በውይይት ለመፍታት አለመቻሉ  ሌላው ኀዘን መሆኑን ገልጸዋል። ስለሆነም ይላሉ ብፁዕነታቸው  የሀገርን ክብር በመጠነ፤ የትውልድን አደራ ተሸካሚነትን ባገናዘበና ዘለቂታዊ አንድነትና አብሮነትን በሚያጠናክር መልኩ ችግሮችን በውይይትና በመነጋገር በመፍታትን  የአዲስ ዘመንን በእውነተኛ አንድነት ልንቀበለው ይገባል በማለት አሳስበዋል። በመጨረሻም ብፁዕነታቸው  በመጪው ዘመን ያቀድነው እንዲሳካና ተስፋችንን እንድናገኝ ይቻል ዘንድ የሀገረ ሰላም በእጅጉ አስፈላጊ ነው። ስለሆነም ባለፈው ዘመን ያለፈብን ዋይታ፣ መፈናቀል፣ ጦርነትና ችግር ሁሉ በቃ በማለት ወደ ሰላም ልንመጣ ይገባል ሲሉ  አባታዊ መልእክታቻውን አስተላልፈዋል። ምንጭ ፦ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

🎲 Quiz 'ፍኖተ ወንጌል ልዩ መንፈሳዊ የጥያቄ እና መልስ ውድድር"start the quiz"የሚለውን ይጫኑ"i am ready "ሲጫኑ ጥያቄው ይጀምራል። መልካም ዕድል🛎🛎🛎' 🖊 7 questions · ⏱ 30 sec

ልዩ መንፈሳዊ በፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት እየተዘጋጀ የሚቀርብ የጥያቄ እና መልስ መርሐ ግብር። ዘወትር በየሳምንቱ አርብ ምሽት ከ2:00 ⏰ ጀምሮ እስከ 4:00 ⏰ ድረስ ወደ እናንተ ይደርሳል። ይሳተ
ልዩ መንፈሳዊ በፍኖተ ወንጌል ሰ/ት/ቤት እየተዘጋጀ የሚቀርብ የጥያቄ እና መልስ መርሐ ግብር።
       ዘወትር በየሳምንቱ አርብ ምሽት ከ2:00 ⏰ ጀምሮ እስከ 4:00 ⏰ ድረስ ወደ እናንተ ይደርሳል።                 ይሳተፋ! ለኦርቶዶክሳውያን ሼር በማድረግ ይጋብዙ! የአሰላ ደ/መ/መ/ዓ/ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475

ነሐሴ 24 እንኳን ለኢትዮጵያውያን ጻድቃን ለታላቁ አባት ለከበረ ሐዲስ ሐዋርያ ለትሩፋትም መምህር ለሆነ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ዕረፍት እንዲሁም ለሰይጣን ምሕረትን ለለመነችው የሰላምና የይቅር
+1
ነሐሴ 24
እንኳን ለኢትዮጵያውያን ጻድቃን ለታላቁ አባት ለከበረ ሐዲስ ሐዋርያ ለትሩፋትም መምህር ለሆነ ለአቡነ ተክለ ሃይማኖት በዓለ ዕረፍት እንዲሁም ለሰይጣን ምሕረትን ለለመነችው የሰላምና የይቅርታ እናት ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሰን።
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel 🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel 🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475 ▭▭▭▭▭▭▭▭ T.me/FinoteWongel1 ▭▭▭▭

የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 🔎 የቴሌግራም ቻናል:- T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 🔎 የቲክቶክ ገጽ:-
+1
የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel 🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel 🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475 ▭▭▭▭▭▭▭▭ T.me/FinoteWongel1 ▭▭▭▭

ጉዞ ወደ ደብረ ሊባኖስ በሰላም ያግባቹ🙏
+4
ጉዞ ወደ ደብረ ሊባኖስ    በሰላም  ያግባቹ🙏

ጉዞ ወደ ደብረ ሊባኖስ    በሰላም  ያግባቹ🙏

1 ቀን ቀረው! ተመዝግበዋል? የማይቀርበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ደብረ ሊባኖስ ኑ አብረን እንጓዝ! መመዝገቢያ ቦታ:- በሰንበት ት/ቤቱ ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል
1 ቀን ቀረው!
ተመዝግበዋል?
የማይቀርበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ደብረ ሊባኖስ
ኑ አብረን እንጓዝ!
መመዝገቢያ ቦታ:- በሰንበት ት/ቤቱ ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel 🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel 🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475 ▭▭▭▭▭▭▭▭ T.me/FinoteWongel1 ▭▭▭▭

2 ቀን ቀረው! የማይቀርበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ደብረ ሊባኖስ ኑ አብረን እንጓዝ! መመዝገቢያ ቦታ:- በሰንበት ት/ቤቱ ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል
2 ቀን ቀረው! የማይቀርበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ደብረ ሊባኖስ ኑ አብረን እንጓዝ! መመዝገቢያ ቦታ:- በሰንበት ት/ቤቱ ንዋያተ ቅድሳት መሸጫ ሱቅ የአሰላ ደ/መ/መ/ዓለም ካቴድራል ፍኖተ ወንጌል ሰንበት ት/ቤት 🔎 የቴሌግራም ቻናል:-  T.me/Finote_Wongel 🔎 የቴሌግራም ግሩፕ:- T.me/FinoteWongel27 🔎 የቲክቶክ ገጽ:- tiktok.com/@finotewongel27 🔎 Youtube:- youtube.com/@Finote_Wongel 🔎 Instagram:- https://www.instagram.com/finote_wongel 🔎 Facebook:- https://www.facebook.com/profile.php?id=61558615513475 ▭▭▭▭▭▭▭▭ T.me/FinoteWongel1 ▭▭▭▭