ASTU Network ®️
前往频道在 Telegram
🛜 ASTU Network ®️ ➲ Join us || @ASTU_Network || || @ASTU_Network_Group || 📚 Library: @ASTU_Network_Library 👁🗨 We are here to keep you updated! ➲ Admin 📩 👤 @NS_Nazu Ⓝ Ŋazarene Ŝon [🥷] |➲| @ASTU_Network
显示更多4 804
订阅者
+324 小时
+467 天
+28130 天
帖子存档
4 814
Good Morning Fam! 🤗
...Someone said:
🗣 “If you’re not using AI, you’re training yourself for a world that no longer exists :)”
Is that true? 😁
.
4 814
💁🏻♂ ለማሳወቅ ወይም ለማስታወስ ያክል❕💻⚙
አብዛኛዎቻችን ለላፕቶፕ ኮምፒውተራችን የMicrosoft ምርት የሆነውን Windows Operating System እንደምንጠቀም ይታወቃል። በብዛት ደግሞ Windows 10ን እንጠቀማለን።
ነገርግን በባለፈው አመት በ2024 Microsoft ለWindows 10 ያለውን support በዚህ አመት በOctober ወር አቆማለሁ ብሎ ባሳወቀው መሰረት በOctober 14, 2025 ለኦፕሬቲንግ ሲስተሙ ያለውን support አቁሟል።
Microsoft ለWindows 10 ያለውን support አቆመ ማለት ምን ማለት ነው❓💻⚙🤔
ይህ ማለት Microsoft ለWindows 10 የሚያደርገውን የ security update ፣ የ feature update እና ቴክኒካል assistance አቆመ ማለት ነው። ይሄም ኮምፒውተሩን ለቫይረስ እና malware ተጋላጭ ሊያደርገው ይችላል።
ኮምፒውተሩ በትክክል መስራቱን ይቀጥላል። ነገርግን የደህንነቱ ጉዳይ እርግጥ አይሆንም። ስለዚህ Windows Operating Systemን የምትጠቀሙ እና Windows 10ን የጫናችሁ ሰዎች ፣ Windows 11ን መሸከም የሚችል ወይም compatible የሆነ ላፕቶፕ ካላችሁ ለደህንነት ያክል Operating System'አችሁን ወደ Windows 11 upgrade ብታደርጉ ይመረጣል።
Setting ውስጥ ከገባችሁ በኋላ Update & Security የሚለው ጋር ኮምፒውተራችሁ ለWindows 11 Eligible እንደሆነ ማየት ትችላላችሁ። እዛው የWindows 11ን የመጫን process መጀመር ትችላላችሁ። ካልሆነ ደግሞ ከየትኛውም source Windows 11ን manually መጫንም ትችላላችሁ።
ለደህንነት ያክል ለማለት ነው ቤተሰብ! 😊
መልካም ምሽት! 🫶🏽🤗
|| @ASTU_Network
4 814
Repost from 🔖 ASTU Marketplace 🛒
+1
YouTube Channel for sale! 🌐
👉 Subscribers: +9K
👉 Views: 1.1M
👉 Watch time (hours): 17.3K
👉 Estimated revenue: $32.73
DM: YTChannel
@Astu_marketplace
4 814
#Fun 😸
Wait... ✋
Did you notice something during this exam time❓🤔
People aren't talking about the exams. They're actually, but it isn't as they used to do before.
It might be one of the two reasons:
1. They did well 🧠🦾 and became mature 🦍. They choose silence in any situation...🙂
2. They got cooked like h*ll as usual 😁, getting cooked became normal 🤷♂️, and got bored of crying every time they get done 😞, so they just chose to be silent...😒
But the first one seems insane... 😁 lol
.
4 814
+1
በማርበግር ቫይረስ ዛሬ የአንድ ሰው ህይወት ማለፉ ሪፖርት ተደረገ።
ዛሬ 13 የላብራቶሪ ምርመራ ተደርጎ በ2 ሰዎች ላይ ቫይረሱ ተገኝቷል።
በዛሬው ዕለት በተደረገው ምርመራ በቫይረሱ መያዛቸው የተረጋገጠው ታማሚዎች ከዚህ በፊት ከተገለፀው ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጂንካ ከተማ በለይቶ ማቆያ የነበሩ ሲሆኑ በተመሳሳይ ቦታም የህክምና ክትትላቸውን እያደረጉ ይገኛሉ።
በአጠቃላይ በማርበርግ ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 8 የደረሰ ሲሆን ህይወታቸው እንዳለፈ የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር 4 ደርሷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
4 814
በጅማ ዮኒቨርሲቲ አዘጋጅነት ለሚደረገው የዮኒቨርሲቲዎች ስፖርት ፌስቲቫል የተመዘገባቹ ተማሪዎች በሙሉ ዛሬ 10፡00 LT የሁሉም ስፖርቶች አሰልጣኝ ስለሚገኙ DUBAI ሜዳ ሳታረፍዱ እንድትገኙ እናሳስባለን።
ቦታውን ለማታውቁት Central library ጀርባ DUBAI ሜዳ
Barattoonni Feestivaala Ispoortii Yuunivarsiitii Jimmaatiin qophaa'eef galmoofttan hundi osoo hin Barfatiin istaadiyeemii DUBAI akka dhufttan kabajaan dhaamna, leenjistoonni ispoortii hundaaf har'a sa'aatii 10:00 LT irratti waan argamaniif.
Astu sport and Entertainment Club
STUDENTS UNION
@Astupost
4 814
#MidExam
ዛሬ የመጀመሪያ ሴሚስቴር የሚድ ፈተናችሁን ተፈትናችሁ የጨረሳችሁ ተማሪዎች እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉🤗😁
ቀጣይ ሳምንት የምትጨርሱ ተማሪዎች ደግሞ አይዟችሁ! 😁 ይሄም ያልፋል! 🤧... ለዛሬ እረፍት አድርጉ። ትንሽ አየር ውሰዱ ፣ ተፍታቱ!🤗 ከፈለጋችሁ ከከተማም ወጣ በሉ ቤተሰብ ጋር ምናምን... ከዚያ ቀስ ብላችሁ ማንበብ ትጀምራላችሁ...🙂
አይ እኔ ጊዜ አላባክንም አጠናለሁ የምትሉ TEMRO NERDS 🤓 ካላችሁ ደግሞ ላይብረሪው ለእናንተ ክፍት ነው! 🫳 🫤 😸
|| @ASTU_Network
4 814
#አሳዛኝ_ዜና! 😭💔
ትናንት ህዳር 11/2018 ዓ.ም ጠዋት ላይ በደባርቅ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ተማሪዎች "የምግብ እጥረት አለ ይስተካካከል" ብለው ሰላማዊ ሰልፍ በወጡበት የግቢው ዘበኞች ተኩስ ከፍተው የ2 ተማሪዎች ህይወት እንዳለፈ እና ሌሎች ላይ ጉዳት እንደደረሰ የደረሰን መረጃ ያመላክታል። (#አዩዘሀበሻ)
|| @ASTU_Network
4 814
🛑 #ATTENTION‼️
⚠ ለሲኒየር ወንዶች በሙሉ❕☝
ሰሞኑን ከወንዶች ዶርም እቃ እየተሰረቀ ነው። በተለይ second-year እንደ 367 ያሉ blocks ላይ። ተማሪ ሆነው ተማሪን የሚሰርቁ የማይረቡ ሰዎች እየበዙ ነው። የተለያየ አጋጣሚ እየተጠቀሙ ፣ በተለይ ተማሪዎች ለፈተና ሲወጡ እና ሌላ ቦታ ሲሄዱ እቃ የሚሰርቁ ተማሪዎች እንዳሉ እያየን ነው። ትላንትም እቃ ተሰርቋል። ዛሬ እራሱ እነዚህ ከንቱ እና ማፈርያ የሆኑ ሰዎች አንድ ዶርም ልጆቹ የሌሉ መስሏቸው በሩን ለመክፈት እየሞከሩ ነበር።
እንደዚህ አይነት ቆሻሻ ስራ የምትሰሩ ተራ ፣ ከንቱ እና ማፈርያ የሆናችሁ ሰዎች ጠብቁ ብቻ ፣ ዋጋችሁን ታገኛላችሁ! 🤨
Just wait and see እንዴት አድርገን አሳልፈን እንደምንሰጣችሁ! ከዚያ በኋላ ይቅርታም ሆነ ለቅሶ የለም! 🫵
አንተ ሌባ ፣ ጓዝህን ጠቅልለህ ሻንጣህን ሸክፈህ 🧳 ወደ ቤትህ ትሄዳታለህ! 🤬 እዚህ ከእኛ ጋር አትጨማለቅም! 🧌
We will show you no mercy! 🤫😈
|| @ASTU_Network
4 814
#Fun 😸
ብሬ ትኩረት ሁሉ ወደ ትምህርት እያለ ነው! 😁
👴🗣 ብሬ ለወንዶች be like:
... አትታለሉ አትታለሉ አትታለሉ... 😸☝
.
4 814
#ተጨማሪ_መረጃ ፧ አዲሱ መመሪያ‼️
ሴት ተማሪዎች የጥፍር፣ የፀጉርና የከንፈር ቀለም መቀባት፣ ቅንድብ መቀንደብና መኳኳል፣ አላስፈላጊ ጌጣ ጌጦችን አድርጎ ወደ ትምህርት ቤት መሄድ የሚከለክል መመሪያ ትምህርት ሚኒስቴር አዘጋጀ፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር የተማሪዎችን ሥነ ምግባር ለመቆጣጠር ያዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ማንኛውም ተማሪዎች ከተፈጥሮ ጸጉራቸው በስተቀር አርቴፊሻል ፀጉር መቀጠል አይችሉም ተብሏል፡፡
ከዚህ ባለፈም በትምህርት ቤት ውስጥ አላስፈላጊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነት ባህልን የማይገልፁ በዓላት በተለይም እንደ ክሬዚ ዴይ፣ ኦልድ ዴይ፣ ቤቢ ዴይ፣ ቶማቶ ዴይ፣ ከለር ዴይ፣ ቫላንታይን ዴይ እና ሌሎችም የበዓል ቀናቶች ተብለው የሚከበሩ በዓላት ማክበር በመመሪያው ተከልክሏል፡፡
በትምህርት ቤት የደንብ ልብስ በተገቢ መንገድ መልሰብ ሲል ባወጣው መመሪያ ስር ሴቶች ጉርድ ቀሚስ ከባት በታች የሆነ ቁመት ያለው ለብሶ መገኘት አለባቸው ተብሏል፡፡
ከደንብ ልብስ ውጪ ቢሆን ከአካባቢው ባህል ጋር የማይቃረን አለባበስ መልበስ ይጠበቅባቸዋል ይላል ረቂቅ መመሪያው፡፡
ትምህርት ቤት ውስጥ መፈፀም የተከለከሉ ድርጊቶች ብሎ ከዘረዘራቸው መካከል ደግሞ የትምህርት ቤቱን መምህራን፣ የትምህርት አመራር፣ ሠራተኞችና ሌሎች የትምህርት ማህበረሰብ አካላትን መዝለፍ፣ መስደብ፣ ማንቋሸሽና አካላዊ ጥቃት መፈጸም ቅጣት የሚያስከትል ተግባር ነው ተብሏል፡፡
ተንቀሳቃሽ ስልክ ወይም ሞባይል እና የሙዚቃ ማዳመጫ መሣሪያዎችን ትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ይዞ መገኘት ረቂቅ መመሪያው ከልክሏል፡፡
በቃል፣ በምልክትም ሆነ በጽሑፍ ፀያፍ ነገሮችን መግለፅ፤ ጨዋነት የጎደላቸውን እንዲሁም ሐይማኖታዊና ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸውን ምስሎችና ጽሑፎች በትምህርት ቤት ውስጥ ይዞ መገኘትና ማሰራጨት አይፈቀድም፡፡
በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ የማንኛውንም ዓይነት የኃይማኖት አምልኮ ሥርዓትና የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችን ማካሄድ ይከለክላል፡፡
ማንኛውም ተማሪ አገራዊ እሴት ያልሆኑና መጤ የሆኑ ነገሮችን በሰውነት ላይ ምልክት ማድረግ፤ ከአገራዊ እሴት ጋር የሚቃረኑ አሉታዊ መጤ ምልክቶችን በሰውነት ላይ መነቀስ፣ ማሳየት፣ ማድረግ፣ መጠቀም ፍፁም የተከለከለ ነው ብሏል ረቂቅ መመሪያው፡፡
ከ9 እስከ 12ተኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች አንድ ተማሪ በሥነ-ምግባር ጉድለት እጅ ከፍንጅ ከተያዘና የመማር ማስተማሩን ሂደት የሚያውክ ሆኖ ከተገኘ ውሳኔ እስኪሰጠው ከትምህርት ቤት ሊታገድ እንደሚችልም በመመሪያው ሰፍሯል፡፡
ተማሪዎች ተደጋጋሚ ጥፋት አጥፍተው ሲገኙ በተለይም ከ7 እስከ 12ተኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎች እስከ 1 ዓመት ድረስ እንደ ጥፋቱ መጠን ታይቶ ከትምህርት ሊታገዱ ይችላልም ሲል ረቂቅ መመርያው አስቀምጧል፡፡
በሌላ በኩል በትምህርት ቤቶችና አካባቢ የትምህርት አዋኪ ጉዳዮችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር ለሚኒስትሮች ምክር ቤት የቀረበ ረቂቅ ደንብ ተሰናድቷል፡፡
በዚህ ረቂቅ ደንብ ትምባሆ(ሲጋራ፣ ሺሻ)፣ ጫት፣ አልኮል የናርኮቲክ እና ሳይኮትሮፒክ ዝርያ ያላቸው አደገኛ ህገ ወጥ መድኃኒቶች እና ሱስ አስያዥ ዕፆች ትምህርት ቤት አካባቢ መሸጥም ሆነ ይዞ መገኘትን ይከለክላል።
የአልኮል መሸጫ እና ማከፋፈያ ቤቶች፣ የሲጋራ መሻጫ ሱቆች፣ ሺሻ ቤቶች፣ ጫት መሸጫና መቃሚያ ቤቶች፣ ጭፈራ ቤቶች፤ ቁማር ቤቶች፤ የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች እና የሰውነት መታሻ ወይም ማሳጅ ቤቶች በትምህርት ቤቶች በ500 ሜትር ርቀት ውስጥ መክፈት አይቻልም፡፡
ፊልም ማጫዎቻ ቤቶች፣ ፕሌይ ስቴሽን ቤቶች፣ ዲ.ኤስ.ቲቪ ቤቶች፣ ከረንቡላ፣ ፑል፣ ጆተኒ፣ ቢንጎ እና የስፖርት ቁማር መጫወቻ ቤቶችም በትምህርት ቤት አቅራቢያ መክፈትን ከልክሏል።
#ሸገር_ሬዲዮ
|| @ASTU_Network
4 814
+1
🚨⚠🚨 #ALERT 🚨⚠🚨
በሽታው መስፋፋቱን ቀጥሏል‼️😥
በቅርቡ የተከሰተው የማርበርግ ቫይረስ በሽታ እስከአሁን ድረስ በተከሰተበት ጂንካ አከባቢ ብቻ እንደሚገኝ ፣ ወደ ሌሎች አከባቢዎች እንዳልተስፋፋ እና ስርጭቱን ባለበት ሙሉበሙሉ ለመግታት እየተሰራ እንደሆነ የጤና ሚኒስቴር መግለጹ ይታወቃል።
ነገርግን ይሄ ሳይሆን ቀርቶ በአርሲ ዞን አሰኮ ወረዳ ሁሉቆ ቀበሌ ላይ በማርበርግ ቫይረስ በሽታ እንደተጠቁ የተጠረጠሩ 13 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የመሰረት ሚዲያን ዘገባ ዋቢ አድርገን መዘገባችን ይታወሳል። አሁንም በሽታው እየተስፋፋ እንደሚገኝ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
በማርበርግ ቫይረስ ምክንያት በሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል አንድ ሰው ህይወቱ አልፏል ተብሏል። በመዲናችን በአዲስ አበባ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ደግሞ ምልክቱ የታየባቸው ሰዎች ለይቶ ማቆያ እየገቡ መሆኑን መሰረት ሚዲያ ማረጋገጡን ዘግቧል።
ባሳለፍነው ሳምንት በጂንካ ከተማ እንደተገኘ ይፋ የሆነው የማርበርግ ቫይረስ ስርጭቱ እየሰፋ መጥቶ እንደ ሀዋሳ እና አዲስ አበባ ባሉ ከተሞች ምልክቶች መታየት መጀመራቸውን መሰረት ሚዲያ ከጤና ባለሙያዎች መስማቱን ዘግቧል።
በሽታው በፍጥነት እየተዛመተ ያለ ይመስላል። በዚህ በሽታ የተያዘ ሰው ደግሞ የመሞት እድሉ ከፍተኛ እንደሆነ እየተነገረ ነው። ጉዳዩ በጣም አሳሳቢ ስለሆነ ፣ ሁላችንም በየሃይማኖታችን እንጸልይ። 🤲🧎♂🙏
ደግሞ ሁሌም ጥንቃቄ አይለየን! ☝
🦠 የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምልክቶችን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ 👇
🔗 Link: https://t.me/ASTU_Network/2265እራሳችንን እንጠብቅ! 🙏 || @ASTU_Network
4 814
የተማሪዎች የሥነ ምግባር ረቂቅ መመሪያ በውስጡ ምን ምን አካቷል ?
➡️ " Crazy day ፣ olds day ፣ Valentine day " እና ሌሎችም አላስፈላጊ የሆኑ ባህልን የማይገልፁ ድርጊቶችን ማክበር ይከለክላል።
መመሪያው በመንግስት ፣ መንግስታዊ ባልሆኑ ፣ የግል ፣ በኃይማኖት ተቋማት የሚተዳደሩ ትምህርት ቤቶችና ከኢትዮጵያ ውጪ ባሉ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት በሚማሩ ተማሪዎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል።
በመመሪያው የተማሪዎች መብትና ግዴታዎች ሲቀመጡ በተማሪዎች ግዴታ ስር ፀጉርን በአግባቡ መሰራት/ማሳጠር፣ ከተፈጥሯዊ ጸጉራቸው ውጪ እንዳይጠቀሙ ተቀምጧል።
የሴቶቾ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ ቀሚስ ቁመት ከባት በታች መሆን ያለበት ሲሆን ከአካባቢው ባህል ጋር የማይቃረን ልብስ መልበስ የሚለውም ተካቷል።
በመመሪያው ከተከለከሉ ተግባራት መካከል ሲጋራ ማጨስ፣ አልኮል መጠጣት፣ ጫት መቃም፣ ዕፆችን መጠቀም/ማዘዋወር እንደዚሁም ሞባይልና የሙዚቃ ማዳመጫዎችን ወደ ትምህርት ቤት ይዞ መምጣት ይገኙበታል።
በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ኃይማኖታዊ አምልኮ ስርዓትና የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችን ማከናወንም በመመሪያው ተከልክሏል።
በመመሪያው ሀገራዊ እሴት ያልሆኑ መጤ ነገሮችን በሰውነት ላይ መነቀስ ሲከለከል፤ ሴት ተማሪዎች የጥፍር፣ የፀጉርና የከንፈር ቀለም ከመቀባትና ከመኳኳል እንደዚሁም አላስፈላጊ ጌጥ ከማድረግ ይከለክላል።
በተጨማሪም በረቂቁ በትምህርት ቤት ውስጥ አላስፈላጊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነት ባህልን የማይገልፁ ያላቸውን ድርጊቶች ፦
• Crazy Day,
• Gentle Day,
• Olds Day,
• Baby Day,
• Fruit Day,
• Tomato Day,
• Valentine Day,
• April the full,
• Color Day,
• Pyjama Day…etc መፈጸም፤ እና ሌሎችም አላስፈላጊ የሆኑ ባህልን የማይገልፁ ድርጊቶችን ማክበር እንደማይቻል ተገልጿል።
የተከለከሉ ተግባራትን በሚፈፅመት ላይ የተለያያ የእርምት እርምጃዎች ሲቀመጡ ቀላል እርምጃ ሊያስወስዱ በሚችሉ ጥፋቶች ስር ከፀጉር ጋር የተያያዙ እና ሌሎች ቀላል ጥፋቶች ተካተዋል።
የትምህርት ቤት ፕላዝማና ኮምፒውተር ለሌላ አላማ መጠቀም፣ በአጥር መዝልና መሽሎክ፣ ከላይ የተጠቀሱ አላስፈላጊ ባህሎችን ማክበር፣ አሉታዊ ምልክቶችን መነቀስ፣ ድብድብ እንደዚሁም ኃይማኖታዊ ስርዓት መፈፀምና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ በከባድ ጥፋት ውስጥ ተካተዋል።
የቅጣት እርከኑ እንደ ተማሪዎች የትምህርት ደረጃና ጥፋቱ ሲለያይ ለከባድ የስነ ምግባር ግድፈት በመደበኛ ህግ መሰረት የህግ ተጠያቂነት ይኖራል።
መመሪያው የዲሲፕሊን ክስ አመሰራረት፣ የዲስፕሊን ኮሚቴ ስብጥር እንደዚሁም ተግባርና ኃላፊነትን በዝርዝር አስቀምጧል።
ከዚህ ባለፈ ፦
• ትምባሆ (ሲጋራ፣ ሺሻ)
• ጫት
• አልኮል
• የናርኮቲክ እና ሳይኮትሮፒክ ዝርያ ያላቸው አደገኛ ህገ ወጥ መድኃኒቶችና ሱስ አስያዥ ዕፆች በትምህርት ቤቶችና አካባቢ መገኘት፣ መጠቀም፣ መሸጥ፣ ማብቀል፣ ማምረት ወይም መለወጥ የተከለከለ እንደሆነ መመሪያው ላይ ተቀምጧል።
እንዲሁም ፦
• የአልኮል መሸጫና ማከፋፈያ ቤቶች
• የሲጋራ መሸጫ ሱቆች
• ሺሻ ቤቶች
• ጫት መሸጫና መቃሚያ ቤቶች
• ጭፈራ ቤቶች
• ቁማር ቤቶች
• የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች
• የሰውነት መታሻ (ማሳጅ) ቤቶች
• የፊልም ማጫዎቻ ቤቶች
• ፕሌይ ስቴሽን ቤቶች
• ዲ.ኤስ.ቲቪ ቤቶች
• ከረንቡላ ፑል
• ጆተኒ
• ቢንጎ እና የስፖርት ቁማር መጫወቻ ቤቶችም እገዳ ተጥሎባቸዋል።
በተጨማሪም መመሪያው በየደረጃው ያሉ የባለድርሻ አካላትን ተግባርያ ኃላፊነትም ዘርዝሮ ሲያስቀምጥ ማንኛውም ትምህርት ቤት ያለ መሸኛ ተማሪዎችን ተቀብሎ መመዝገብንም ከልክሏል።
ትምህርት ሚኒስቴር በመመሪያው ላይ ምክረ ሃሳብ ያላቸው ሰዎች በ https://forms.gle/R72ai6EiMnzZtGsC6 እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
Via @TikvahethMagazine
4 814
አዲስ የትምህርት ደንብ‼️ እስከ 150,000 ብር የሚደርስ ቅጣት እና የባህል ጥበቃ‼️
የትምህርት ሚኒስቴር በትምህርት ተቋማትና አካባቢያቸው የትምህርት አዋኪ ድርጊቶችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችል አዲስ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ረቂቅ ደንብ ማውጣቱን አስታወቀ።
ይህ ደንብ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ እና ብቁ ዜጎችን ለመፍጠር ያለመ ነው።
ዋና ዋና ነጥቦች እና ዓላማዎች:
* የትምህርት አዋኪ ድርጊቶችን የሚፈጽሙ ግለሰቦች እና ተቋማት እስከ 150,000 ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው ተመላክቷል።
ደንቡ እየጨመሩ የመጡትን አዋኪ ጉዳዮች ከመግታት ባሻገር፣ ከኢትዮጵያውያን ወግና ልማድ ጋር ይቃረናሉ ተብለው የተለዩ የውጭ ባህላዊ ልማዶችን በትምህርት ተቋማት አካባቢ መፈጸም ሙሉ በሙሉ ይከለክላል።
ዋንኛው ዓላማ በትምህርት ቤቶችና አካባቢ የሚስተዋሉ አዋኪ ጉዳዮችን በመከላከል፣ ሁለንተናዊ ስብዕናው የተሟላ፣ በመልካም ሥነ-ምግባር የታነፀና ግብረ-ገብነትን የተላበሰ ብቁ ትውልድ እንዲፈጠር ማስቻል ነው።
የተከለከሉ የውጭ ባህላዊ ድርጊቶች ምሳሌዎች:
አዲሱ ደንብ የሀገሪቷን ባህልና ወግ ይቃረናሉ ተብለው በግልጽ የዘረዘራቸውን አሉታዊ መጤ ድርጊቶችንና ክብረ በዓላትን ይከለክላል።
ከእነዚህም መካከል:
* Crazy Day
* Gentle Day
* Olds Day
* Valentine Day
* Color Day
* Pyjama Day የሚሉት ይገኙበታል።
|| @ASTU_Network
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
