ch
Feedback
ግጥም

ግጥም

前往频道在 Telegram

በዚህ ቻናል በጣም ምርጥ እና መንፈስን የሚያድሱ ግጥሞች ፣ ተከታታይ ታሪኮች ፣ የኦንላይን ቢዝነስ ቲፖች ይቀርቡበታል መርጣችሁ አብራችሁን ስላላችሁ እናመሰግናለን Buy Ads https://telega.io/c/gitm_post ADMIN 👉 @Big_jor

显示更多
5 361
订阅者
+324 小时
+677 天
+18730 天
帖子存档
#ለሰው_የሚታየው! በአይናችን ቦይ መስመር የሚንዠቀዠቀው የሚታየው እንባ ጎርፍ ሆኖ የሚወርደው የብዙ አመት ህመም የስቃይ ምንጭ ነው በልባችን ኩሬ በግድ ተገድቦ ታፍኖ የኖረው በጉንጫችን ዳገት ቁልቁል መስመር ሰርቶ በሐይል አስገድዶ ሁለት ቅንድብ ገፍቶ የአንድ ቀን አይደለም ድንገት የሚመጣ በጥቂት ሀዘን ቁልፍ ተከፍቶ የሚወጣ የከራረመ ነው የዘለላ ድምር ከልባችን ሳሎን ቀድሞ የሚቋጠር ሲሞላ ግድቡ የሚወርደው ጥሶ ከታቻምናው አምና ዘንድሮን ቀንሶ ከገደብ ያለፈው የተራረፈው ነው ቅጥሩን እየጣሰ ለሰው የሚታየው          @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ     ✍  ስንታየሁ ሀብታሙ

📢 Advertising in this channel You can place an ad via Telega․io. It takes just a few minutes. Formats and current rates: Vie
📢 Advertising in this channel You can place an ad via Telega․io. It takes just a few minutes. Formats and current rates: View details

📢 Advertising in this channel You can place an ad via Telega․io. It takes just a few minutes. Formats and current rates: Vie
📢 Advertising in this channel You can place an ad via Telega․io. It takes just a few minutes. Formats and current rates: View details

#አፍቃሪ_ያሳጣሽ ካለሽ ውበት በላይ አምረሽ ተኳኩለሽ ከቤት ስትወጪ እንደ ፀሀይ ደመቀሽ በምቴጂው መንገድ.. ከአንድ አንቺ በስተቀር ሰዎች አይኑሩበት አንቺን የማይነካም ወጥመድ ይዙርበት። ተወለጋገጂ ስተሄጅ በመንገዱ ማንም አይመኝሽ ለወዳጅ ዘመዱ። ያርግሽ ነገረኛ ከሰው አትስማሚ ለሚመለከትሽ መሳይ ሁኝ ታማሚ። ብቻ... የኔ ሰሞነኛ የዘወትር ፀሎቴ ይህ ነው አለሜ ውዳሴ ዳዊቴ። ምክኒያቱም አለሜ ስስቴ ሁነሻል በልቤ ማሳ ላይ ውብ ፍቅርን ዘርተሻል። እናም.. በይ እስኪ እወቂ የልቤን ውስጥ እውነት በፍቅርሽ ደክሜ እንዳጣሁኝ ገሉበት አንቺን ለማግኘት ስል እንደገባሁ ስለት አንቺን እያሰብኩም ከቤተ መቅደሱ አሀዱ እንዳሉ መስቀል ይዘው ቄሱ። ብቻ... የዘወትር ፀሎቴ  ውዳሴ  ዳዊቴ አፍቃሪ ያሳጣሽ የሚል ነው ስስቴ። አዎ አለሜዋ የኔ ሁሉ ነገር አፍቃሪ ያሳጣሽ ከአንድ እኔ በስተቀር።          @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ

#በሆድ_ጉርምርምታ ስጠግብ ከጻፍኩት ስሜት አልባ ቅኝት ቤት ካልመታ ስንኝ ትርጉም አልባ ስሜት ሲርበኝ የጻፍኩት በዜማ ታጅቦ በሆድ ጉርምርምታ ባልበላሁት ምግብ ባይኔ በሚዞረው የውብ ጠረን ሽታ ይሻላል አስር እጅ ጠንካራ ነው ቃሉ ቅኔ ነው ትርጉሙ ከውስጥ የመነጨ የስቃይ ደም እንባ ጥልቅ ነው ህመሙ ስሜት ከማይሰጠው ጠግቤ ከጻፍኩት ከቃላት ጋጋታ ከላይ ከላይ ስሜት የውሸት ፈገግታ እቃቃ ጨዋታ እርቦኝ የፃፍኩት ትርጉም አለው ለኔ ጥልቅ ነው ስሜቱ ከባህር የሰፋ ከየብስም የሚበልጥ ሰፊ ነው እውነቱ          @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ   ✍ ስንታየሁ ሀብታሙ

#አትምጭ_በህልሜ    ኸረ ምኑን ትቼ ምኑን ልንገርሽ፡ እንቅልፍ አላስተኛ ብሎኛል ፍቅርሽ፡፡ ጣራውን እያየሁ ከአልጋው ተጋድሜ፡ ሌት ሳልተኛ አድራለሁ ቀኑን ሙሉ ቁሜ፡፡ በሀሳብ ዋልሁና ቀኑን ስንገላታ፡ ተኝቼ በህልሜ አየሁሽ በማታ፡፡ ወይ ዛሬ ወይ ነገ አገኝሻለሁ ስል፡ ጥለሽብኝ ቀረሽ የህሌና ቁስል፡፡ በንፁሁ ልቤ በደማቁ ፅፌሽ፡ ሌሊቱን በህልሜ አደርሁኝ አቅፌሽ፡፡ እያሽለበለበኝ ከአልጋው ተጋድሜ፡ ስትፍነከነኪ አየሁሽ በህልሜ፡፡ ቀን አልበቃኝ ብሎ አንቺን መመልከቱ፡ ስጨነቅ አድራለሁ ላይሽ በሌሊቱ፡፡          @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ

'' እኔ ምን አገባኝ ! ''  ~ የምንላት ሐረግ ፥ እርሱ ነው ሀገሬን ~ ያረዳት እንደ - በግ ፥ የሚል ግጥም ልፅፍ ~ ተነሳሁኝና ፥ ምናገባኝ ብዬ ~ ተዉኩት እንደገና ።         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ   ✍ ኑረዲን_ኢሳ

#ሱሰኛ_ነኝ አዎ ሱሰኛ ነኝ ሱሴ እልፍ የበዛ፣ አንድ ሁለት ካላልኩ ፊቴ የማይወዛ፣ ቀኔ የማይበራ ሚጨልም ደንጋዛ፣ አይኔ ማይከፈት እንዲሁ በዋዛ፣ አጨሳለሁ ገና መቼ ተጨሰና፣ የፊደል ጭራሮ መች ተለኮሰና፣ የቃላት ቅርንጫፍ መች ተማገደና፣ በጭሱ ናውዤ በዜማው ሰክሬ፣ አልችልም ልላቀቅ ክፉኛ ታስሬ፣ አዎ ሱሰኛ ነኝ ውስጡ ተነክሬ፣ ድንገት ያጣው ጊዜ አልችልም ዳክሬ፣ ምርኩዝ አያነሳኝ ምቀር ተሰብሬ፣ አዎ ሱሴ በዝቷል ጠልቆ ከደም ስሬ፣ ቃል ከቃል ሲጋጠም በሚፈጥረው ግለት፣ ስቃጠል ኖራለሁ ካጣው ስለምሞት፣ የፊደል ስደራ የወግ አቀማመጥ፣ የቃሎቹ ጉልበት ሲጮሁ ብለው ፀጥ፣ ወኔ ቢስ ሲሰማው የሚያረገው ሸነጥ፣ የሀረግ ሹል ስለት የብዕር ረመጥ፣ ያቅበዘብዘኛል ብሎኝ አላስቀምጥ፣ አዎ ሱሰኛ ነኝ የቃላት ግጥምጥም፣ የቤት መቺዎቹ እኛ ያሉት ፍርጥም፣ ጊዜ ማይሽራቸው ስንቱን ቢሽሩትም፣ አዎ ሱሰኛ ነኝ እኔማ የግጥም።         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ

#ምትወደኝ_ከሆነ ምትወደኝ ከሆነ ከምር ምትሳሳልኝ ገፆቼን አንብበህ ትርጉሙን ፍታልኝ የእውነት ካነበብከው ምንድነው የሚሉት ጥቂት ከተፃፉት ገፆቼ ላይ ካሉት ...ብዬ ስጠይቅህ አንተ ምንም ያልከኝ በአፌ ባልነግርህም በጣም አሳዘንከኝ ታውቀኛለህ ብዬ አንተ ላይ ስመካ አጠገቤ ሁነህ አታውቀኝም ለካ በል ስማኝ የኔ አለም እንዲዚ ነው ሚሉት በጉልህ ሚታዩት ከፊቴ ላይ ያሉት እነዚ አይኖቼ አንዳች ነገር ሆነው ፍቅርን ተርበው ፍቅርህን ተጠምተው እንደዚ ሁኛለሁ እንደዚም ባይሉ ዝምታዬ መሃል ቃላቶችም አሉ ዳሩ ግን ሌላ ነው አንተ አይገባህም ከኔ ጋ ቆምክ እንጂ ከኔ ጋ አይደለህም።         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ         ✍ ነጋሲ ግደይ

#ጆሮዬን_መልሽ! ይመስለኝ ነበረ ... ልቤን የሰወርሽው ፥ እንዳያስብ ሌላ ዓይኔን የጋረድሽው ፥ በመውደድሽ ጥላ፣... ይመስለኝ ነበረ ... ከንፈሬን ያሸግሽው ፥ የሰው እንዳይነካ አሁን ሳስተውለው ... ጆሮዬን ጨምረሽ ፥ ወስደሽዋል ለካ! ዘፈን እንዴት ላድምጥ? ... ፍቅርን አስቀይሜ ፥ ቃል ኪዳኔን ጥዬ አምባሰል ነሽ ባቲ ፥ ኧረግ አንቺ ሆዬ! ክራር ጤና ነሳኝ ... መሰንቆና ዋሽንት ፥  ከበሮ ድለቃ ... እንዳውም ይቅርብኝ!  ኃጢኣት ነው ሙዚቃ። ለደስታ ካልሆነኝ                  ዝንቱ ከንቱ ውእቱ ጥርቅም!  ....  ኤ--ታ--ባ--ቱ!! ዋ! ሞኙ! ዋ!  እኔ! ያበጀሁኝ መስሎኝ ፥ ያቀናሁ በቤቴ ባሳብ ለሚዋልል ፥ ርብሽብሽ ስሜቴ ፀጥታን ላጣጥም ፥ እፎይ ከማለቴ፣ ... ናፍቆትን ቀስቅሶ ፥ በንፋስ ጣት ንዝረት በሽንቁር ሾላኪ ፥ ፉጨት - ርግብግቢት፣... ጥሩሩን አጥልቆ ስውር ሰይፉን ታጥቆ፣ ... ዜመኛው ዝምታሽ ፥ ሊሸርፈኝ ይከንፋል ትዝታ እንደ ዘፈን ፥ ተጫውቶ መች ያልፋል?

#እቴዋ_ልምከርሽ ! ማሬ ማሬ እያለ የሚነጠፍልሽ፣ እኔን እኔን ብሎ ድንግጥ የሚልልሽ፣ ከአንቺ ሌላ እያለ በስምሽ የሚምል፣ ስርስርሽን በዝቶ ሲከብሽ የሚውል፣ ማርሽን ፍለጋ መሆኑን አትርሽ፣ በጥርስሽ እየሳቅሽ ልብሽን አሽሽ! እውነተኛ አፍቃሪ ላንች የተፈጠረ፣ አይቀርም መምጣቱ የተመረመረ፣ እቴዋ ልምከርሽ በስንኝ ቋጠሮ መኖርን ከፈለግሽ ሴትነትሽ ከብሮ ውበትሽን አርግፎ ልብሽን ለሚሰብር፣ አትስጭ ቸኩለሽ ክብርሽ ነው ብር አንባር !         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ    ✍ ስንታየሁ ሀብታሙ

#አርፎ_አይቀመጥም ሰው መንገደኛ ነው ተጓዤ በየዕለቱ ባአቀበት ቁልቁለት የተሰራ ቤቱ ሲወጣ ሲወርድ ይነጋል ለሊቱ ካአፈር የተገኘ ሸክላ  አከላቱ መቸ ያስችለዋል ልተወው ቢልኳ ደርሶ እየተናደ የካበው ሲንኳኳ መስመሯን ስቀይር ህይወት ለታሪኳ ልቡ ባህር ገብቶ ሲቀዘፍ በታንኳ ግር ይለዋልና እስኪለምደው ድረስ ሲቀኘው ይውላል ትዝታን ሲደርስ ሽው ሽው እያለ  እንደቀኑ ንፋስ ወስዶ እስኪመልሰው  የሀሰቡ ፈርስ አርፎ አይቀመጥም ከመሬቱ ጎኑ እስኪሸልብ ድርስ እስካለ በውኑ ኮሽ ባለቁጥር ይገለጣል አይኑ ትንፍሹ እንድሰማ እንደሸት ጠረኑ!! @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ       ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢʰᵃʳᵉ ✍ ሊድያ ማሞ

#ሳብድ_ለምን_መጣሽ? ከሄድሽ ጀምሮ ••• ትዝታና ናፍቆት አቅም እያሳጡ ሲጥሉ ሲያነሱኝ ወራቶች ሲሮጡ በሞት መኖር መሀል ጎኔ ተሰንቅሮ በምኞት  በማየት  ስለነገ  አሻግሮ በግድ ስላለፍኩት ወራት አመታቱ ብታውቂም አልመጣሽ ተይዤ በብርቱ            እሺ ይሄም ይቅር ዕልፍ የሆኑ ወቅቶች በተስፋ ማለሙ የመጠበቅ ደዌ ጠንቶብኝ ህመሙ እድሜን ያህል ነገር ስላንቺ መስጠቴ የዘመኔን ክፋይ ላንቺው መሰዋቴ ስሜቱ እየገባሽ ከእንቅልፍ መኳረፍ ገላን ብቻ አንጋሎ በሀሳብ መንሳፈፍ እንደው እንዴት ሆነ ብለሽ ሳጠይቂ ዕልፍ አሳልፈሻል ለብቻሽ ስትስቂ                     ከአይኖቼ በመፍለቅ ትራሴን ያራሱት ዘለላ እምባዎቼ ስላንቺ ያነቡት በዋዛ ተቆጥረው ሁነውብሽ ተራ እንዲያ በመሆኔም ልብሽም ሳይራራ             ቀርተሻል በዘበት እግርሽ አረገጠም እኔም ካለሁበት                     የሳቅ ደስታ ትርጉም እስኪጠፋኝ ድረስ ሌተቀን በማዘን እድሌንም ስወቅስ ትመጫለሽ በሚል ሰርክ በመጠበቅ ደጁን እያማተርኩ ሳጣሽም ስሳቀቅ ብስቁልቁል ብዬ ስላዩ ባክኜ ባላፊው አግዳሚው በሰው ተኮንኜ እኔው በታመምኩት እኔው ብንገላታ አላስቀምጥ ብሎኝ የሰው አሉባልታ ማንም ከማያቀኝ ከአዲስ ቦታ መንደር ከሰው ተገልዬ ሁኜ እንደ ባይተዋር በጣር ስለኖርኩት ስላለፍኩት ስቃይ እያወቀሽ ሁሉንም መጥተሽ አይኔን ሳታይ እኔን ለኔው ትተሽ ስላንቺው ኑረሻል መቼም አትክጂውም ሁሉን ልብሽ ያውቃል                  ታዲያ •                               •                                 ለምን                                 •                               •                        ይሆን ?              ዛሬ ሁሉ ረፍዶ ጎኔ እንደናፈቀሽ ግዜው ሄዶ ሄዶ ከለየልኝ   ዃላ  ጨርቄ   ተቀዳዶ ሰዎች ሲያወሩልሽ የማበዴን መርዶ ልታዪኝ  መምጣትሽ ካለሽበት ማዶ አዝነሽ ነው ፀፅቶሽ ፣ ወይስ ደስ ብሎሽ ? ንገሪኝ  እውነቱን ሳብድ ለምን  መጣሽ ?         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ       ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ    ˢʰᵃʳᵉ

#የመሸበት_የለም የመሸ ቢመስለኝ የጨለመ በእኔ ነገ ጤዛ ሆኖ ይረግፋል ሀዘኔ በእኔ የምትሰራው ገና ሆኖ ግዜው አንተ እኮ ጌታዬ መምጫህ በድንገት ነው የተውከኝ ቢመስለኝ የረሳኸኝ ዛሬ ነገም ያንተ ቀን ነው ይመለሳል ክብሬ እጠብቅሃለሁ በተስፋ ቃል ኪዳን አንተን ተስፋ አድርጎ የመሸበት የለም ወድቆ ቀረው ሲሉ አንሳኝና ልቁም አምላክ ባንተ ስራ ጠላትም ይደመም።          @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ     ✍ ስንታየሁ ሀብታሙ

ቤተሰብ አንድ ነገር ላስቸግራችሁ እኔን ለማገዝ ፍቃደኛ የሆናችሁ 700 ሰዎች ይኸን የቴሌግራም ቻናል join እያደረጋችሁ screenshot ላኩልኝ የ5 ቀን ቻሌንጅ ሰተውኝ ነው ስለትብብራችሁ ከወዲሁ ከልብ አመሰግናለሁ 🙏

please support me by join this channel

#የእብደቴ_መነሻ        ፀሐይን አግብቼ ጨረቃን ስወሽም፣        "ይኼ ሰው ምን ነካው?" ትያለሽ ሁልሽም፤                   በተስፈኛ ምድር......        ደራሲ ገጣሚ አድርጎ ሲፈጥረኝ፣        በዚያች ዕለት ነበር እብደት የጀመረኝ።         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ

#ምኞትሽ_ላይ_በርቺ! አንፖልን ለማብራት ይቃጣሉ ጣቶች ጨለማ ም ነበረ ፋኖስ የሚያደምቁ ... ባይኖሩ ለኳሾች ። እመኚኝ እታለም! በምታይው ዓለም.. . አምፖልም ፋኖስም ድምቀቶች አይደሉም ብርሀን ለማፍለቅ እንደሚገለጥ ህልም ፈፅሞ አይፈኩም! መፍካት በመሻት ነው  በምኞት ነው መንቃት ጨለማን ለመስበር ... ከፋኖሱ ቀድመሽ... ልብሽን ነው ማብራት።         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ   ✍ ሚካኤል አስጨናቂ

#በቃልሽ_ታስሬ የልቤ ላይ ንግስት አንቺ ውቧ ፍቅሬ ቀናትን በመቁጠር ወራትን ደምሬ ከጎንሽ ባልሆንም ከአንቺው ጋር አብሬ በፍቅርሽ ሰንሰለት በፅናት ታስሬ አሜን ይሁን ብዬ ቃልሽን አክብሬ ለልቤ ትርታ ለደም ዝውውሬ ለመንፈሴ እርካታ ብታመም ዶክተሬ ደስታን ለማጣጣም ፍቅርሽን ዘምሬ እስትንፋሴ ነብሴ ሆነሽ ለእኔ ጤና ለመኖሬ ትርጉም የሂወቴ ቃና አዛኝ እንደ ሄዋን ሩህሩህ ነሽና አለም አስር ትሙላ ከቤቴ ግቢና         @gitm_post     ♡ ㅤ     ❍ㅤ        ⌲                ˡᶦᵏᵉ    ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ     ˢʰᵃʳᵉ