916
订阅者
无数据24 小时
+47 天
-430 天
帖子存档
ሚያዚያ 22/2018 ዓ.ም
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅህፈት ቤት
ባለፉት 5 ዓመታት የወረዳውን ህዝብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ማከናወኑን ገልጿል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ባለፉት አምስት አመታት የጤና ተቋማት ቁጥር ለማሳደግ አገልግሎት አሰጣጥ ለማሻሻልና ግበዓት ለማሟላት ከረጂ ድርጅቶች ፣ከመንግስት፣ከባለሀብትና ከህበረተሰብ ተሳትፎ ከ220 ሚሊዮን ብር በላይ በማስባሰብ በጤናው ዘርፈ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱን ጽ/ቤቱ አክሎ ገልጿል።
በወረዳው በአሁኑ ወቅት አንድ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል፣ 6 ጤና ጣቢያዎች ፣አንድ መሠረታዊ ጤና ኬላ፣25 መደበኛ ጤና ኬከላዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛሉ።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጤና ጥበቃ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አብራር እንደገለፁት በወረዳው በበሽታ መከላከልና አክሞ ማዳን ተግባራት ውጤታማ ስራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል።
የጤና አገልግሎትን ተደራሽነት ለማስፋት ሴቶችና ህፃናት መሰረታዊ የጤና አገልግሎት በወቅቱ እንዲያገኙ
ለማስቻል አበዘት ጤና ጣቢያ ግንባታ ፣ጅማ ጤና ጣቢያ የእናቶች ማረፊያ ቤት ግንባታ፣ከንትዋት 2ኛ ትውልድ ጤና ኬላ ግንባታ፣የመሀል አምባ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ካፌ ግንባታ፣ጅማ ፣ዋቦን ፣እንደብዮ ጤና ኬላ ግንባታዎች በአዲስ በመስራትና በማጠናቀቅ ህብረተሰቡ የጤና አገልግሎት ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ጠቅሰው ኢንጌ ጤና ጣብያ ጥገና ፣ጅማ ጤና ጣቢያ አጥር ጥገና፣መሀል ጉታዘር ጤና ጣቢያ አጥር ጥገና እና ጥላሞ ጤና ኬላ ጥገና መደረጉን አስታውቀዋል።
ጥራት ያለውና የተሻለ ህክምና አገልግሎት ለማስፋትና ተደራሽነትን በሁሉም የጤና ተቋማት ተጠናክሮ ለማስቀጠል በመንግስት፣ከረጂ ድርጅቶችና ከአከባቢ ተወላጅ ባለሀብቶች በማስተባበር ለመሀል አምባ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል x-ray ፣ገሬኖ ፣አበዘት ፣ጅማና ኢንጌ ጤና ጣቢያዎች የህክምና ግብዓት የማሟላት ስራ መሰራቱን የገለጹት አቶ ኢብራሂም በሁሉም ጤና ጣቢያዎች የንፅህና መጠበቂያ ፣የቆሻሻ ማስወገጃ፣የውሀ ሮቶዎች፣የልብስና ጋዎን ማጠቢያ ግንባታ የተከናወነ ሲሆን ለ12 ቀበሌዎች ዘሬ ፣ኮምበል፣ ጥላሞ፣ሰፋቶ ቀርሳ፣ቦሮቦር ሰፋቶ፣ዋቦን ጤና ኬላዎችና ጅማ ጤና ጣቢያ በአጋር ድርጅቶች በሶላር ሚሰራ ፍሪጅ ድጋፍ ተደርጓላቸዋል።
ፍትሃዊ የጤና አገልግሎት ለማዳረስና ህብረተሰቡ በገንዘብ እጦት ምክንያት ከህክምና አገልግሎት እንዳይስተጓጎል ከ26 ሺህ በላይ አባወራና እማወራ የማዐጤማ አባል ሆነው አገልግሎት ማግኘት ችለዋል የአባልነት መዋጮ የመክፈል አቅም የሌላቸው ለ5565 የህብረተሰብ ክፍሎች መንግስት በጀት ይዞላቸው በየአመቱ እየከፈለ ማህበረሰቡ በአነስተኛ መዋጮ እስከ ፌደራል ሆስፒታሎች ድረስ የህክምና አገልግሎት ማግኘት እንዲችሉ ተደርጓል።
የእናቶችና ህፃናት ደህንነት ለመጠበቅ የእናቶች የቤተሰብ ዕቅድ ከ5 አመታት በፊት 66% እንደነበረ ገልፀው አሁን ላይ 78% ማሳደግ እደተቻለ፣የቅድመ ወሊድ ክትትል ፣ድህረ ወሊድ እንክብካቤ ፤የቀዶ ህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርጓል እንዲሁም የእናቶች ከፍተኛ የህመም ስቃይ ሲያሳድርባቸው የነበረ የማህፀን ውልቃት ከ220 በላይ እናቶች በወረዳው መንግስት ድጋፍ ህክምና አግኝተው ከህመማቸው እንዲድኑ መደረጉን ገልጸዋል።
ዕድሜያቸው ከ5 አመት በታች በስርዓት ምግብ 14586 ህፃናት ተለክተው 1159 ህፃናት የምግብ እጥረት መታከም መቻላቸውና 284 ህፃናት ከባድ የምግብ እጥረት የታየባቸው ሙሉ በሙሉ እስኪድኑ ሆስፒታል ተኝተው ምግብና መድኃኒት ያለ ምንም ክፍያ እንዲታከሙ የተደረገ ሲሆን የቆልማማ እግር ፣የላንቃና የከንፈር መሰንጠቅ ችግር የነበረባቸው ከ5 አመት በታች ዕድሜ ያሉ ከ15 በላይ ህጻናት እንዲታከሙና ከችግሩ እንዲላቀቁ ተደግጓል።
በሽታን አስቀድሞ ለመከላከልና የአከባቢ ንፅህናን ለመጠበቅ ከአይነ ምድር ነፃ ቀበሌ መፍጠር የጤናው ዘርፍ ዋንኛ ተግባር መሆኑን አስታውሰው በሁሉም ቀበሌ እየተሰራ እንደሚገኝና 19 ቀበሌዎች ከአይነ ምድር ነፃ ተደርገው ሲመረቁ 7 ቀበሌዎች ደሞ ለማስመረቅ በሂደት ላይ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በመጨረሻም አቶ ኢብራሂም እንደገለጹት ባለፉት አምስት ዓመታት በበጎ ፈቃደኝነት 492 ዩኒት ደም በማሰባሰብ የብዙዎችን ህይወት መታደግ መቻሉን ጠቅሰው የጤና አገልግሎቱን ይበልጥ በማዘመንና በየደረጃው ካለው አመራርና ባለሙያ ጋር በመቀናጀት፣ ጤናማና አምራች ማህበረሰብ ለመፍጠር የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስበዋል።
ሚያዚያ 22/2018 ዓ/ም
በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም በተገኘ ድጋፍ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የጎምራ ቀበሌ ነፍሰ-ጡርና አጥቢ እናቶች እንዲሁም የስርዓተ ምግብ ጉድለት ላለባቸው ህፃናት 50 ፍየል ድጋፍ ተደረገላቸው።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም አማካኝነት በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ በጎምራ ቀበሌ በተመረጡ ሞዴል መንደሮች በአራት መቶ ሺህ ብር በጀት በመመደብ
ለ50 እናቶች ለእያንዳዳቸወ 1 ሴት ፍየል በድምሩ 50 ፍየል ተሰራጭቷል።
ሴት ፍየሎች የተሰጡበት ዋና አላማ የፍየል ወተት ስርዓተ ምግብን ለማሟላት ከላም ወተት የተሻለ ንጥረ ነገር በመያዙ ሲሆን ፍየሎችን በአግባቡ በመያዝ ወተታቸው ከሁለት አመት በታች ላሉ ህፃናትና አጥቢ እናቶች መጠቀም እንዳለባቸው ስልጠና ተሰጥቷል።
መረጃው የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ነው።
ሚያዚያ 22/2018 ዓ/ም
የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ የ9 ወር የስራ አፈጻጸም እና የዜጎች ቻርተር ውይይት በወልቂጤ ከተማ እያካሄደ ይገኛል።
፨፨፨፨፨//፨፨፨፨፨
የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን በመክፈቻ ንግግራቸው መምሪያው በዞኑ እየተሰሩ ያሉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን በጥራትና በፍጥነት በተለያዩ የሚዲያ አማራጮችን ለህዝብ ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።
በቴሌቪዥን ፣በሬድዮ፣በህትመት ውጤቶችና የተለያዩ የማህበራዊ ሚዲያ አማራጮች በመጠቀም መረጃን ለህዝቡ ተደራሽ የማድረግ ስራ እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል።
እስከ ታችኛው መዋቅር ድረስ ወቅታዊ የድጋፍና ክትትል ስራዎችን በማጠናከር ተቋሙ በሰው ሀይል ፣በቁሳቁስ እና በበጀት እንዲደገፍ በመደረጉ አበረታች ለውጦች መጥተዋል ብለዋል።
በተቋሙ የውስጥና የውጭ የመልካም አስተዳደር ችግሮች በመለየት ዘርፊን የማጠናከር ስራ እየተሰራ ሲሆን የጉራጌ የማህበረሰብ ቴሌቪዥን ጣበያ ለመክፈት ወደ ተግባር ተገብቶ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑን አቶ ሸምሱ ገልጿል።
7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ሰላማዊ ፣ፍትሀዊ እና ታማኒነት ያለው እንዲሆን በሚዲያና ኮሚኒኬሽን ዘርፉ በአጽንኦት እየተሰራበት ስለመሆኑ አስታውቀዋል።
በውይይት መድረኩም የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣የመምሪያው ባለሙያዎች ፣የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትና የተቋሟት ፍካል ፐርሰኖች ተገኝተዋል።
ሚያዝያ 21/2018 ዓ/ም
አካል ጉዳተኞችን እና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች በመደገፍ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ በሚደረገው ርብርብ ባለድርሻ አካላት ሊያግዙ እንደሚገባ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህን ያስታወቀው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ ዓመት የዜጎች ቻርተር የህዝብ ክንፍና አካቶ ትግበራ ዕቅድ አፈፃፀም ዙሪያ ከባለ ድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ባካሄደበት ወቅት ነው።
የጽህፈት ቤቱ ልማት እቅድ ባለሙያ የሆኑት አቶ መሀመድ ሙደሲር እና አቶ አ/ፈታ ጀማል የ2018 ዓ.ም የ3ኛ ሩብ አመት የዜጎች ቻርተርና የህዝብ ክንፍ ሰነድ አደነደዲሁም አካቶ ትግበራ ሪፖርት አቅርበው ውይይትና ምክክር ተደርጓበታል።
ከተነሱት ሃሳብና አስተያየቶች መካከል ተቋሙ በርካታ ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚያስተናግድ በመሆኑ ባለድርሻ አካላት ተቀናጅተው መስራት እንዳለባቸው፣ ሁሉም ተቋማት የአካል ጉዳተኞች ጉዳይ አካቶ መሰራት እንደሚያስፈልግ፣ሞዴል ቀበሌ መፍጠር እንደሚገባ ፤ዕድሜያቸው ለስራ ያልደረሱ ህፃናት ጉልበት ብዝበዛን መከላከል እንደሚገባ፤ከተቋሞች ጋር በቅርበትና በቅንጅት መስራት እንዳለባቸው በተለያዩ ድርጅቶች ተቀጥረው የሚሰሩ ሰራተኞችን ክትትልና ደሞዝ ክፍያቸው መከታተል ፤ተግባራትን በወጥነት ማስቀጠል እንደሚገባና አካል ጉዳተኞችን ተቋሞች መቅጠር እንደሚገባቸው የሚሉት የተነሱ ሀሳቦች ናቸው።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ተወካይ አቶ መሀመድ ሳኒ ደንበል በመድረኩ ተገኝተው እንደገለፁት ሞዴል ቀበሌ በመፍጠር ለሌሎች ቀበሌዎች ተሞክሮ በሚሆን መልኩ እንደሚሰሩ ገልፀው፤ የአቅመ ደካሞችን ችግር በዘላቂነት ለመፍታት በትኩረት እንደሚሰራ እንዲሁም በተለያዩ ድርጅቶች ቀጥረው የሚያሰሩ ድርጅቶች ዕድሜያቸው ለስራ ያልደረሱ ህፃናት ከመቅጠር እየታረሙ መሄዳቸውና ለውጥ መምጣት መቻሉን ተናግረዋል።
አቶ መሀመድ ሳሊ አክለው አረጋውያን እና አካል ጉዳተኛ ዜጎችና ተጋላጭ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመደገፍ በሚደረገወ ርብርብ ተወላጅ ባለሃብቶች፣ የልማት ማህበራትን እንዲሁም የረጂ ድርጅቶች እገዛቸውን ማጠናከር እንዳለባቸው አስገንዝበው፤
በመድረኩ የተቋማት የልማት እቅድ ባለሙያ፣
የዜጎች ቻርተር እና የህዝብ ክንፍ አባላት ተሳትፈዋል።
የጉራጌ ዞን አስተዳደር የተለያዩ ሹመቶችን ሰጠ
ሚያዚያ 21/2018(ወልቂጤ)፦የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ላጫ ጋሩማ የተጓደሉ የአመራር ቦታዎችን መነሻ በማድረግ በሽግሽግና በምደባ የተለያዩ ሹመት ሰጥተዋል!!
በዚህም መሰረት፦
1. አቶ ናስር ሀሰን ፦የጉራጌ ዞን የመንግስት ዋና ተጠሪና የብልፅግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ
2. አቶ ደሳለኝ ፈቀደ ፦ የጉራጌ ዞን ረዳት የመንግስት ተጠሪና የብልፅግና ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ
3)አቶ ደሳለኝ ገብሬ ፦የአስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል!!
የጉራጌ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን መምሪያ ለተሿሚዎች መልካም የስራ ጊዜ እንዲሆንላቸው ይመኛል!!
ሚያዚያ 19/2018 ዓ/ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም ተጠቃሚ ለሚሆኑ የጎምራ ቀበሌ ነፍሰ-ጡርና አጥቢ እናቶች እንዲሁም የስርዓተ ምግብ ጉድለት ላለባቸው ህፃናት 500 ዶሮ ድጋፍ ተደረገላቸው።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በሰቆጣ ቃል ኪዳን ፕሮግራም አማካኝነት በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ በጎምራ ቀበሌ በተመረጡ ሞዴል መንደሮች በአምስት መቶ ሺህ ብር በጀት በመመደብ
ለ50 እናቶች ለእያንዳዳቸወ 10 ዶሮ በድምሩ 500 ዶሮ ተሰራጭቷል።
የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ እና
የግብርና ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ እና የእንስሳት ዘርፍ አስተባባሪ አቶ ፈድሉ ኡስማን በድጋፉ ወቅት ተገኝተዋል።
መረጃው የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ነው።
