1 084
订阅者
无数据24 小时
+227 天
+1330 天
帖子存档
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ የህይወት ክህሎት ስልጠና ላይ ተሳትፈው ስልጠናውን ላጠናቀቁ ከ80 በላይ ወጣቶች ኢንዱስትሪ ፓርክ ከሚገኝ ሃን ፕላስት ማኑፋክቸሪንግ ጋር የስራ ትስስር ፈጸመ፡፡
በወጣቶቹ የስራ ትስስር ጉዳያ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እንዳሉት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ዋና አላማ ሰልጣኞችን ተቀብሎ በእውቀት፣በክህሎትና በአመለካከት የተቀረጹ ትውልዶችን ማፍራት ብቻ ሳይሆን ወጣቱን በተለያዩ ስልጠናዎች በሚያገኙት እውቀት መሰረት በተለያዩ ፋብሪካዎች ስራ እንዲያገኙና ከራስ አልፎ ለሃገር መጥቀም የሚችሉ ወጣቶችን ማፍራት ነው፡፡
በዚህ መሰረት ኮሌጃችን በሳለፍነው አመት አቅዶበት ሲሰራበት የነበረውና በእቅዱ መሰረት በርከት ያሉ ሰልጣኞችን የስራ እድል ሲፈጥር ቆይቷል፡፡ዛሬም ሃን ፕላስት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ጋር በተስማማነው መሰረት በብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ የህይወት ክህሎት ስልጠና ላይ ተሳትፈው ስልጠናውን ላጠናቀቁ ከ80 በላይ ወጣቶች ወደ ስራ አስገብተናል ብለዋል፡፡ም/ዲኑ በንግግራቸው በያዝነው አመት በርከት ያሉ ሰልጣኞች በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የስራ ትስስር የምንፈጽም መሆናችንን ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል፡፡
በተያያዘ ዘገባ ዛሬ የስራ ትስስር የተፈጸመበት ሃን ፕላስት ማኑፋክቸሪንግ በኮሌጁ ማኑፋክቸሪንግ ትምህርት ክፍል አማካኝነት winding Bering Holder ፣ Heat Exiting Duct እንዲሁም Chiller Machine Assembly and installation የሚባሉ የማሽነሪ ስፔር ፓርት አምርቶ እንዲሁም ገጥሞ ፋብሪካውን በመለዋወጫ እጥረት ምክንያት የሚፈጠርበትን ክፍትት መሙላቱ ይታወሳል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 01/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች የረመዳን ፆምን በማስመልከት የኢፍጣር መርሀ-ግብር አካሄዱ::
ይህ መርሃ-ግብር ድሬዳዋን በተለየ መልኩ የሀይማኖት አብሮነትና መደጋገፍ ያለባት ከተማ እንደሆነች የሚያጠናክር እንደሆነ የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም በዚህ በረመዳንና በዐቢይ ፆም ወቅት ያሳየነውን መደጋገፍና አብሮነት በስራችን ላይም በማጠናከር ውጤታማነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ አስታውሰው የዛሬውን የኢፍጣር መርሀ-ግብር ላዘጋጁና ለተሳተፉ የኮሌጁ ማህበረሰብ ምስጋናቸውን አቅርበዋል ።
በኢፍጣር መርሃ-ግብሩ ላይም የኮሌጁ አመራሮች፣ አሰልጣኝ መምህራንና አስተዳደር ሰራተኞች እንዲሁም ከተቋሙ ጋር በጋራ የሚሰሩ ባለድርሻ አካላትን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳታፊ ሆነዋል ።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 28/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
ከለውጡ በኋላ የተገኘውን ድልና ስኬት ለማስቀጠል ያለመ ታላቅ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በድሬዳዋ አስተዳደር በድምቀት በዛሬው እለት የተካሄደ ሲሆን ኮሌጃችን የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች ዛሬ በተደረገው የድጋፍ ሰልፍ ላይ ተሳታፊ ሆነዋል::
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
ኮሌጃችን እና የመልካም ተግባር እሴቶቹ
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ማህበረሰብና የኮሌጁ የጤና ቡድን በድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በመገኝት በአብይ ጾም ስርዓተ ቅዳሴ ለተሳተፉ የክርስትና እምነት ተከታዮች የተለያዩ ምግቦች እና የታሸጉ ውሃዎችን በማቅረብ ማእድ የማጋራት መርሃ ግብር አካሄዱ፡፡
ፍቅር አንድነትና መከባበር ጎልተው ከሚታይባቸው መስሪያ ቤቶች መካከል የድሬዳ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል፡፡
በመሆኑም በዛሬው እለት ከፍተኛ የሆነ ጸሀይንና ሙቀትን በመጋፈጥ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ማህበረሰብና የኮሌጁ የጤና ቡድን በድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በመገኝት በአብይ ጾም ስርዓተ ቅዳሴ ለተሳተፉ የክርስትና እምነት ተከታዮች የተለያዩ ምግቦች እና የታሸጉ ውሃዎችን በማቅረብ ማእድ በማጋራት ምእመኑን አስተናግደዋል፡፡
በቀጣይም አብሮነታችን ፍቅራችን እና የአንድነት አሴቶቻችን ይበልጥ ለማጠናከር እና ለማስቀጠል የኮሌጁ ማኔጅምት፣ የኮሌጁ ማህበረሰብ እንዲሁም የጤና ቡድኑ ጠንክሮ የሚሰራ ይሆናል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መጋቢት 27/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
በአጫጭር ስልጠና ዘርፍ በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት ለሚሰጡ ተቋማት የ2016 ዓ.ም የስድስት ወር የትምህርትና ስልጠናዉን ጥራት ስታንዳርድ ለማስጠበቅ ክትትልና ድጋፍ ግብረ-መልስ ስልጠናዊ መድረክ ተካሄደ፤
በዚህም የድጋፍና ክትትል ግብረ-መልስ ስልጠናዊ መድረክ የአጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማት የስልጠና ፍቃድ በተመለከተ በተሰጠው ፈቃድ ልክ እየሰሩ ስለ መሆናቸውና ህጋዊ ፈቃድ ሳይኖር ስልጠና የሚሰጥበት የሥልጠና ዘርፍ ላይ ማስተካከያ ለማድረግ በሚቻልበት እንዲሁም በዕቅድ በመመራት ማሰልጠኛ ማንዋሎችና መሳሪያዎች በሚገባ መኖራቸውን ጨምሮ የአጠቃላይ ሰልጣኞችን መረጃ በማደራጀት ሰርተፍኬት የሚያገኙበትን አግባብ ተመልክቷል፡፡
በድጋፍና ክትትሉ ወቅትም ከተቋማቱ ለኤጀንሲው የሚቀርቡ ቅሬታዎች፤ የሚሻሻሉ አሰራሮችና አሰተያየቶች የተሰጡ ሲሆን በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ እንደተናገሩት ይህ የድጋፍና ክትትል ልክ መደበኛ ስልጠና እንደሚሰጡ ተቋማት ሁሉ አጫጭር ስልጠና የሚሰጡ ተቋማትም ዜጎችን በማሰልጠን የሚያበቁ ናቸው ስለሆነም ትምህርትና ስልጠናው ጥራት ስታንዳርድ ለማስጠበቅ በቅርበት በመከታተል መደገፍ አስፈላጊነቱ ቀላል የማይባል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 27/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች በዛሬው እለት በለገሐር አደባባይ ''ሰላም ለሁሉም ሁሉም ለሰላም '' በሚል መሪ ቃል የተካሄደውን የድጋፍ ሰልፍ አካሄዱ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ አመራሮችና ሰራተኞች ቢሮው ከሚገኝበት እስከ ለገሐር አደባባይ ከለውጡ በኋላ የተገኘውን ድልና ስኬት ለማስቀጠል ታልሞ የተዘጋጀውን የድጋፍ ሰልፍ አካሄዱ፡፡
ለውጡ…
• የሁሉም ኢትዮጵያውን መስዋዕትነት እና የጋራ ትግል ያመጣው ነው፤
• አሮጌ አስተሳሰቦችንና ተግባራትን በአዲስ ትርክት የተካ ነው፤
• የሁሉም ኢትዮጵያዊ አሻራ ያረፈበት ነው፤
• የይቅርታና ምህረት ዕሳቤ ተግባራዊ ያደረገ ነው፤
• በፈተናዎች የማይንበረከክ በብልሃትና በጥበብ እያለፈ ነው፤
ለሰላማችን ዘብ እንቆማለን ለውጡን እናፀናለን!!!
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር የህይወት ክህሎት ስልጠና ያጠናቀቁ የሰልጣኞች የምርቃት መርሃግብር ቀጥሎ በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ላይ በድምቀት ተካሄደ፡፡
በዚህም የሰልጣኞች የምርቃት መርሃግብር ላይ የቢሮው አመራሮች የተገኙ ሲሆን የኮሌጁ ምክትል ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ፕሮጀክቱን ውጤታማነት ከሚወስኑ ጉዳዮች አንዱ ሰላም መስፈኑ መሆኑን ገልጸው አንድ መቶ ሃምሳ ለሚሆኑ ሰልጣኞች ከኢንደስትሪዎች ጋር በተፈጠረው መግባባት ቀድመው ወደ ስራ የሚገቡበትን እድል ማመቻቸቱን ተናግረዋል፡፡
በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አቶ ሰኢድ አሊ በበኩላቸው ባለፉት 10 ቀናት የህይወት ክህሎት ስልጠና በኮሌጁ ውስጥ ሲሰጣቸው የቆዩ ሰልጣኞች እንደ ድሬዳዋ በርካታ አማራጮች እየተፈጠሩላቸው መሆኑን ገልጸው በቀጣይ በኢንዱስትሪዎች ላይ የሥራ ልምምድ ሲያደርጉ በሰለጠኑት አግባብ በስነምግባር ሊሆን ይገባል ብለዋል፡፡
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 26/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ዙር የህይወት ክህሎት ስልጠና ያጠናቀቁ የሰልጣኞች የምርቃት መርሃግብር በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ላይ በድምቀት ተካሄደ፡፡
በዚህም የሰልጣኞች የምርቃት መርሃግብር ላይ የቢሮው አመራሮች የተገኙ ሲሆን የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ለሰልጣኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በስልጠናው ያገኙትን እውቀት በቀጣይ በስራ ላይ ለሚኖራቸው ስልጠና እንዲጠቀሙበት በማሳሰብ የሚመጡ እና የሚገጥሟቸን ፈተናዎች በጥንካሬ በማለፍ ለራሳቸውና ለሃገራቸው የሚጠቅሙ ዜጎች እንዲሆኑ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አቶ ሰኢድ አሊ በበኩላቸው ባለፉት 10 ቀናት የህይወት ክህሎት ስልጠና በኮሌጆቹ ውስጥ ሲሰጣቸው የቆየ ሲሆን ይህንንም ሲያጠናቅቁ በመረጡት የሙያ ዘርፍ በአስተዳደሩ በሚገኙ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንደስትሪዎች ላይ የኪስ ገንዘብ እየታሰበላቸው በተግባር እየሰሩ እውቀትና ክህሎታቸውን የሚያዳብሩ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
በስልጠና ቆይታቸውም በኮሌጆቹ የህጻናት ማቆያ ቦታዎች ተዘጋጅቶላቸዋል በዚህም የልጅ እናት የሆኑ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች ስልጠናውን ሳይስተጓጎሉ እንዲወስዱ መቻሉን በማስታወስ ለዜጎች ሁሉን ተደራሽ የሚያደርግ የስራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎች በመሰራት ላይ ለመሆናቸው ይህ መርሃግብር ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 25/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጪ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት በውጭ አገር ስራ ስምሪት አዋጅ ዙሪያ እና በውጭ አገር ስራ ስምሪት አተገባበር ላይ ባሉ ተግዳሮቶች ዙሪያ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ ተካሄደ።
በዚህም አዋጁን በመረዳት የውጭ አገር ስራ ስምሪት የአንድ አካል ብቻ ስራ እንዳልሆነ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተረድተው በአተገባበር ሂደቱ ላይ ከዚህ ቀደም ሲስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን በመንቀስና ተግዳሮቶችን በመለየት በቀጣይ ውጤታማ የሆነ ስራ ለመስራት መግባባት ላይ መድረስ ተችሏል፡፡
በተያያዘም ዜጎችን በህጋዊ መንገድ ወደ ውጭ አገር ለመላክ እየተሰሩ ባሉ ስራዎች ላይ ውይይት የተደረገ ሲሆን በአስተዳደሩ የከተማ ቀበሌዎች እና ኮሌጆች ከቢሮው ጋር በማቀናጀት ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ በዳይሬክቶሬቱ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ጌታቸው በረዳ አሳስበዋል።
የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 25/2016 ዓ.ም
ድሬዳዋ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
