1 091
订阅者
+324 小时
+257 天
+1730 天
帖子存档
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ " እያመረትን እናሰለጥናለን እያሰለጠንን እናመርታለን " የሚል አዲስ እሳቤ የማስጀመሪያ መርሀ-ግብር በዛሬው እለት ተካሄደ።
በድሬዳዋ አስተዳደር የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በመሰልጠን የሞያ ባለቤት ለመሆን በዚህም እራሶትንና ቤተሰቦን አልፎም ሀገሮን መጥቀምና ማገልገል ያስባሉ እነሆ ዝግጅታቸውን አጠናቀው የእርሶን መምጣት በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ!
የሰሞኑን ዝናብ ተከትሎ የወባና የደንጊ ትኩሳት በሽታ አስተላላፊ የሆኑ ትንኞች መራቢያ ሊሆኑ የሚችሉ ውሃ ያቆሮ ቦታዎችን በማፋሰስ፤ ውሃ ሊያቁሩ የሚችሉ ቁሳቁሶችን በማስወገድ ወይም ውሃ እንዳይዙ በማድረግ፤ ለተለያዩ አገልግሎቶች ለመጠቀም ያጠራቀምነውን ውሃ በመሸፈን እና አካባቢን በማፅዳት የደንጊ ትኩሳት እና የወባ በሽታዎችን እንከላከል።
የድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ
የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 ዓ.ም አዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅታቸውን ማጠናናቀቃቸውን ገለጹ።👇👇👇
‹‹ኮሌጃችን ሰልጣኞችን ተቀብሎ ከማሰልጠን በተጨማሪ በኮሌጁ ውስጥ የሚሰለጥኑ ስልጠና ለሚያጠናቅቁ ተማሪዎች ከኢንዱስትሪዎች ጋር ባለን ጥብቅ ግንኙነት የስራ ትስስር እንዲፈጠርላቸው ተግተን እንሰራለን፡፡››
የኮሌጁ ዲን
አቶ ሳሊም ኡስማን
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በቀንና በማታው መርሃ ግብር ከ2000 በላይ ሰልጣኞችን ተቀብሎ የሞያ ባለቤት ብሎም ስራ ፈጣሪ ሊያደርግ ሙሉ ዝግጅቱን አጠናቆ ሰልጣኞችን በመጠባበቅ ላይ መሆኑን አስታወቀ፡፡
በአዲስ ተማሪዎች ቅበላ ዙሪያ ላይ የኮሌጁ ዲን በጽህፈት ቤታቸው መግለጫ የሰጡ ሲሆን ዲኑ በንግግራቸው እንዳሉት ኮሌጃችን የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ከ45 ሺ በላይ ሰልጣኞችን በመደበኛ ፕሮግራሙ ከ48 ሺ በላይ ደግሞ በአጫጭር ስልጠና አሰልጥኖ ለኢንዱስትሪው ያቀረበ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ በርካቶቹ የስራ ፈጣሪ ሲሆኑ የተቀሩት ደግሞ በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ውስጥ በመግባት ለሃገራችን ኢኮኖሚ ግንባር ቀደም በመሆን እያገለገሉ ይገኛሉ፡፡
በተጨማሪም ዲኑ እንዳሉት ኮሌጃችን በዘንድሮ አመትም የምንቀበላቸው ሰልጣኞችን ከማሰልጠን በተጨማሪ በኮሌጁ ውስጥ የሚሰለጥኑና ስልጠና ለሚያጠናቅቁ ተማሪዎቻችን ከኢንዱስትሪዎች ጋር ባለን ጥብቅ ግንኙነት የስራ ትስስር እንዲፈጠርላቸው ተግተን እንሰራለን ብለዋል፡፡
እንዲሁም ኮሌጃችን በአለም ባንክና በጀርመን መንግስት ሁለት ትላልቅ ፕሮጀክቶችን እያስገነባ ይገኛል እንዚህም ፕሮጀክቶች የምድር ባቡር የልህቀት ማእከል የሚያደርገውና በICT ለምስራቅ አፍሪካ ተማሪዎችም ጭምር የሚያገልግሉ የተለያዩ ማስተማሪያ ክፍሎች እንዲሁም የማስተማሪያ ግብአቶችን በማሟላት ሰልጣኞቻችን በቂ እውቀት የሚያገኙበትን ሁኔታ በማመቻቸት ስልጠናዎችን የምንሰጥ ይሆናል፡፡ በመጨረሻም ከሌሎች ኮሌጆች የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን መርጣችሁ እንድትመዘገቡ በዚሁ አጋጣሚ ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል፡፡
በመቀጠልም ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ት/ትና ስልጠና ኃላፊ አቶ ሰላሃዲን አብዱልሃሚድ እንደገለጹት ኮሌጃችን ከ11 በላይ የትምህርት መስኮች በኮሌጁ ውስጥ የምንሰጥ ሲሆን ስልጠናዎቹም በሙሉ ያለምን ክፍያ የምንሰጥ ሲሆን በሁሉም የስልጠና መስኮች 21ኛ ክፍለ ዘመንን የሚመጥኑ የማስተማሪያ ክፍሎች የማሰልጠኛ ማሸነሪዎች እንዲሁም ስማርት ማስተማሪያ ክፍሎችን በማደራጀት እንዲሁም በቂ ልምድና እውቀት ባላቸው መምህራን ስልጠናዎችን የምንሰጥ ሲሆን በኮሌጃችን የሚሰልጥኑ ሰልጣኞች በሙሉ ከኢንዱስትሪዎች ጋር በማስተሳሰር የስራ እድሎችንም የእየፈጠርንም እንገኛለን ያሉ ሲሆን፡፡
በተጨማሪም ም/ዲኑ በንግግራቸው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሁሉንም አካታች እንደ መሆኑ መጠን በስልጠናው ሂደት ላይ የሴቶች ተሳትፎ እንዲጎለብትና ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማድረግ የተለያዩ ማበረታቻዎችን በመስጠት ስልጠናው ላይ በቂ እውቀት እንዲኖራቸው ከመቼውም ጊዜ በላይ የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ም/ዲኑ እንዳሉት ኮሌጃችን የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በክረምቱ መርሃ ግብር ‹‹ክረምትን በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ›› በሚል መሪ ቃል በርከት ያሉ ሰልጣኞችን በተለያዩ የሞያ መስኮች እያሰለጠነ ቆይቷል በዚህም ሰልጣኞቹ ቴክኒክና ሙያ ምን እንደሚሰራና ለማህበረሰቡ በጣም ጠቃሚ መሆኑን ለማወቅ ችለዋል ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥቅምት 16/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
የኢትዮ-ጣልያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 ዓ.ም የስልጠና ዘመን አዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማሰልጠን ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገለፀ::
ኮሌጁ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም የዘንድሮ አዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማሰልጠን ኮሌጁ መጠነ ሰፊ ዝግጅት ማድረጉን ገልፀው ወጣቶች እንደ ሀገር የትኩረት ዘርፍ የሆነውና ለወጣቱ ብዙ እድሎችና አማራጮችን ወደያዘው የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በመቀላቀል ራሳቸውንም ሆነ ሀገርንም መጥቀም ሚችሉበት መልካም አጋጣሚ የተፈጠረ በመሆኑ በተለይ የ2015 ዓ.ም የ12 ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱ ወጣቶች ይህን መልካም እድል በአግባቡ እንዲጠቀሙም መልዕክት አስተላልፈዋል::
የኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤልያስ መሀመድ በበኩላቸው ኮሌጅ በ2016 ዓ.ም የስልጠና ዘመን በዘጠኝ የሙያ ዘርፎች(ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ፣ አውቶሞቲቭ፣ ማኑፉክቸሪንግ፣ ውድ ዎርክ፣ አይ.ሲ.ቲ፣ኮንስትራክሽን፣ ሆቴልና ቱሪዝም፣ ድራፍቲንግና ሰርቬይንግ፣ አካውንቲግ) ስልጠን ለመስጠት እንደተዘጋጁ ጠቅሰው በተጨማሪም ኮሌጁ ዘንድሮ እስከ 2000 አዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ተቀብሎ የማሰልጠን አቅም እንዳለውና ለዚህም ወጣቶችን በሰፊው እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ገልፀዋል::
ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ጥቅምት 15/2016 ዓ.ም
''በጎነት ለኢትዮጰያ ከፍታ''
በድሬዳዋ አስተዳደር የ2015 ዓ.ም በክረምት በጎ ፍቃድ ተግባራት ማጠቃለያ የዕውቅናና የምስጋና መርሀ ግብር ላይ የስራ፣ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮና ተጠሪ ተቋማት በአዲስ አስገንብቶ ለአቅመ ደካሞች ባስተላለፋቸው 4 ቤቶች የዋንጫና የምስጋና ወረቀት ተበርክቶለታል።
እንኳን ደስ አላችሁ!!
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ30 ሰልጣኝ ተማሪዎች ኢንዱስትሪ ፓርክ ከሚገኝ አንድሪያ ሹ ጫማ ፋብሪካ ጋር የስራ ትስስር ፈጸመ፡፡
በሰልጣኝ ተማሪዎች የስራ ትስስር ጉዳያ ላይ ማብራሪያ የሰጡት የኮሌጁ ም/ዲንና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እንዳሉት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ዋና አላማ ሰልጣኞችን ተቀብሎ በእውቀት፣በክህሎትና በአመለካከት የተቀረጹ ትውልዶችን ማፋራት ብቻ ሳይሆን በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሰለጠኑ ሰልጣኞችን ስራ ፈጣሪ ብሎም ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ጋር በመስማማት የስራ እድል በመፍጠር እራሳቸውን እና ሀገራቸውን የሚጠቅሙ ትውልዶችን ማፍራት ነው፡፡
በዚህ መሰረት ኮሌጃችን በሳለፍነው አመት አቅዶበት ሲሰራበት የነበረውና በእቅዱ መሰረት በርከት ያሉ ሰልጣኞችን የስራ እድል ሲፈጥር ቆይቷል፡፡ዛሬም በአንድሪያ ሹ ጫማ አምራች ኢንዱስትሪ ጋር በተስማማነው መሰረት ቴክስታይል ሌዘርና ፋሽን ዲዛይን ትምህርት ክፍል ሰልጥነው የጨረሱ 30 ሰልጣኞችን ወደ ስራ አስገብተናል ብለዋል፡፡ም/ዲኑ በንግግራቸው በያዝነው አመት በርከት ያሉ ሰልጣኞች በተለያዩ ኢንዱስትሪዎች የስራ ትስስር የምንፈጽም መሆናችንን ለመግለጽ እወዳለሁ ብለዋል፡፡በመጨረሻም በያዝነው የስልጠና ዘመን በርከት ባሉ የሞያ ዘርፎች በቀንና በማታ እንዲሁም በአጫጭር ስልጠና ሰልጣኞችን ተቀብልን የምናሰለጥን ሲሆን ለእንዚህም ሰልጣኞች ስልጠናቸውን እንዳጠናቀቁ ወደ ስራ አለም የሚሰማሩበትን እድል ለማመቻቸት ከተለያዩ ኢንዱስትሪዎች ጋር በቅርበት የምንሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡
በተያያዘ ዘገባ ዛሬ የስራ ትስስር የተፈጸመበት አንድሪያ ሹ የጫማ ፋብሪካ ምርቶቹን ወደ ተለያዩ አውሮፓ ሀገራት የሚልክ ሲሆን ከተቋቋመበት አመት አንስቶ ለሀገራችን ኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሬ በማምጣት ግንባር ቀደም ፋብሪካ ሲሆን ይህ ፋብሪካ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ከድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር እንደሚሰራ ይታወቃል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥቅምት 14/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
ከፌደራል ቴክኒክና ሙያ ኢንትቲቲዩት(FTI) የEASTRIP ፕሮጀክት አስፈጻሚ ቡድን አባላት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ ልውውጥና የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በመስክ ጉብኝቱ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ ዲን እና የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ሃለፊ አቶ ሰልሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በንግግራቸውም እንኳን ወደ በረሀዋ ንግስትና የፍቅር ከተማ ወደ ሆነችው ድሬዳዋ ከተማ እንዲሁም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ወደ ሆነው የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በደህና መጣችሁ ፡፡ ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ ብዙ ሺህ ወጣቶች የሙያና የክህሎት ባለቤት ያደረገ ኮሌጅ ነው ኮሌጁ አሁን ለደረሰበት ስኬትም የከተማ አስተዳደሩ እንዲሁም የኮሌጁ ማህበረሰቦችና ባለድርሻ አካላቶች የማይተካ ሚና አላቸው ያሉ ሲሆን ኮሌጁ በቀጣይ የባቡር ምህንድስና የልህቀት ማእከል እንደመሆኑ መጠን ለድሬዳዋ መመስረት ምክንያት የሆነውን የባቡር ቴክኖሎጂ ለማዘመንና አሁን ያሉትን ባለሞያዎች የሚረከቡ ባለሞያዎችን እያፈራ የሚገኝ ተቋም ነው፡፡
በተጨማሪም በኮሌጁ እየተተገበረ ያለው ይህ የEASTRIP ፕሮጀክት መሳካት የከተማችን አስተዳደር እንዲሁም የአስተዳደሩ የስራና ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ፕሮጀክቱ ከግብ እንዲደርስ ማቺንግ ፈንድ በመመደብ ለሌሎች ከተሞች አርአያ የሆነ ተግባር ፈጽመዋል ይህም ፕሮጀክቱ ከግብ እንዲደርስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ማሳያ ነው፡፡ በተጨማሪም የኮሌጁ ማኔጅመንት ቁርጠኛ ሆኖ ለሚያጋጥሙ ችግሮች ሁሉ ፈጣን ምላሽ በመስጠት ፕሮጀክቱ ከግብ እንዲደርስ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ በመስክ ጉብኝቱ እና በልምድ ልውውጡ ወቅት ለተሳተፉ የFTI ልኡክ ቡድን ገለጻ አድርገዋል ፡፡
በመስክ ምልከታውንና በልምድ ልውውጡ መሰረት በማድረግም የልኡካን ቡድኑ ጋር በነበረው የጋራ ውይይት ወቅት ተሳታፊዎቹ እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር እየወሰደ ያለው ቁርጠኝነት ለሌሎች ከተሞች አራያ መሆን የሚችል ነው ብለዋል፡፡በተጨማሪምፕሮጀክቱ በሚተገበርበት ወቅት በከተማ አስተዳደሩና በኮሌጁ ማኔጅመንት የሚወሰዱት የመፍትሄ እርምጃዎች ለሌሎች ኮሌጆች እንደ መልካም ተሞክሮ የሚወሰድ ነው ብለዋል፡፡
በመስክ ጉብኝቱ እና በልምድ ልውውጡ ወቅት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የEASTRIP ፕሮጀክት እንዲሁም የአዲሱ የSIFA ፕሮጀክት አፈጸጸም እንዲሁም የልህቀት ማእከሉ የግንባታ ሂደት እስካሁን የደረሰበት ደረጃ በአቶ መሳይ ጥላሁን የቀረበ ሲሆን በልምድ ልውውጡ ወቅት የተሳቱ አካላት ለሚያነሱዋቸው የተለያዩ ጥያቄዎች የኮሌጁ የፕሮጀክት ማስፈጸሚያ ቡድኑ አባላት ለተሳታፊዎቹ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን በመቀጠልም በኮሌጁ እየተገነባ ያለውን የልህቀት ማእከል ግንባታ ሂደት ጉብኝት ተደርጓል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥቅምት 12/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ
ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን የተባለ ድርጅት በወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ ላይ የሚሰራ ፕሮጀክት ለመተግበር በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ከአስተዳደሩ ከንቲባ ጋር ውይይት አካሄዱ
የካናዳ ድርጅት የሆነው ማስተር ካርድ ፋውንዴሽን በ2006 በፈረንጆች አቆጣጠር የተመሰረተ ሲሆን በዋናነት ፋወንዴሽኑ አላማ አድርጎ የተነሳው በ2030 በአፍሪካ 30 ሚሊዮን ለሚሆኑ ወጣቶችን አመርቂ እና ጥራት ያለው ሥራን እንዲያገኙ ማስቻል ነው፡፡
“ወጣት አፍሪካ በስራ ላይ” ከወጣቶች ፣ ፖሊሲ አውጭዎች ፣ እና ስራ ፈጣሪዎች ጋር በመመካከር የዳበረ ሲሆን በአፍሪካ 30 ሚሊዮን በኢትዮጵያ ደግሞ 10 ሚሊዮን ወጣቶች ሥራን እንዲያገኙ ለማስቻል የተነደፈ ስትራቴጂ ነው።
የድሬደዋ አስተዳደር ከቡር ከንቲባ ከድር ጁሀርም በውይይቱ ሲገልጹ ከአስተዳደሩ እድገት ጋር በተያያዘ በተለይም ነጻ ንግድ ቀጠና ደረቅ ወደብ መጀመርን ተከትሎ ከፍተኛ የንግድ እንቅስቃሴ የሚካሄድበት በመሆኑ እንዲሁም ከአጎራባች ክልሎች የሚፈልሱ ዜጎች መተላላፊያ ከተማ በመሆኗ የስራ ፈላጊ ዜጎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱን ገልጸው ድርጅቱ በአስተዳደሩ የስራ ፈላጊ ዜጎች ቁጥርን ለመቀነስ ለሚያደርገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል፡፡
ለሴቶች እና ለወጣቶች የስራ እድል መፍጠር የአስተዳደሩን ኢኮኖሚያዊ ፣ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎችን በማፋጠን ረገድ የሚኖረው ሚና ከፍተኛ ነው ያሉት ከንቲባው ፋውንዴሽኑ ለሚያደርገውን ደጋፍ አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል፡፡
የማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ካንትሪ ዳይሬክተር አቶ ሳሙኤል ተድላ በውይይቱ እንደገለጽት ድርጅቱ በ7 ሀገራት ቅርንጫፉን ከፍቶ እየሰራ ሲሆን ዋና አላማው ወጣቶችን ከእድሎች ጋር ማገናኘት ነው ያሉት ሃላፊው በተጨማሪም የግል ዘርፉን እድገት ለማሻሻል እንዲሁም የዲጂታል ኢኮኖሚውን በማልማት በርካታ የስራ እድሎችን መፍጠር ነው ብለዋል፡፡
በሰላም ለማ
ፎቶ፡- ይድነቃቸው አብርሀም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
