ch
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

前往频道在 Telegram
1 084
订阅者
无数据24 小时
+227
+1330
帖子存档
photo content
+6

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ  "ብቃት" የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ሁለተኛ ዙር ትግበራ ለሁለት ተከታታይ ዙሮች የህይወት ክህሎት ስልጠና ሰልጥነው ያጠናቀቁ ሁለት ሺ የሚጠጉ ሰልጣኞች የምርቃት መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት በድምቀት ተካሂዷል በዚህ የሰልጣኞች የምርቃት ፕሮግራም ላይ  የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ክቡር ሀርቢ ቡህ በመገኘት ለተመራቂዎች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። አቶ ሀርቢ ተመራቂዎችን በቀጣይ በተለያዩ  ፋብሪካዎችና አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ በምትቀላቀሉበት ወቅት በስነ-ምግባር የታነፃችሁና በታታሪነት የምታገለግሉ መሆን ይገባቹሀል በማለት የመከሩ ሲሆን፤ ለዚህ መርሀ ግብር መሳካትም አስታዎፆ ላበረከቱ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ  አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው ለተመራቂዎች እንኳን ደስ አላችሁ በማለት በስልጠናው ወቅት ያሳዩትን የስራ ተነሳሽነትና ስነ-ምግባር በቀጣይም እንዲያጠናክሩት ተናግረዋል። በተለይም አሁን ላይ በድሬዳዋ ኢንደስትሪ እየተስፋፋ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ወጣቱም አስፈላጊውን ስነ-ግባርና ክህሎት አግኝቶ ዘርፉን እንዲቀላቀል እንደነዚህ አይነት ስልጠናዎች ከፍተኛ ሚና አንዳላቸው የገለፁት ደግሞ  የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ ዳንኤል ተሬሳ ናቸው። አቶ ዳንኤል አያይዘውም ብቃት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ የወጣት ስራ አጦችን ቁጥር በመቀነሱ ረገድ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ጠቁመዋል። ተመራቂዎች በበኩላቸው በስልጠና ቆይታቸው በርካታ ክህሎት እንዳገኙ ገልፀው ለስልጠናው አዘጋጆችም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ©️ የድሬዳዋ አስተዳደር መንግስት ኮምኒኬሽን

በክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የሥራና ክህሎት ሚንስቴር ዴኤታ የሚመራ የሱፐርቪዥን ቡድን በዛሬው ዕለት በነበረው የመጨረሻ የጉብኝት መርሃግብር በድሬዳዋ አስተዳደር የተገነቡና እየተገነቡ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ፤ በጉብኝቱም የአስተዳደሩን የሥራ አመራር ኢንስቲትዩት የተቋማት አቅም ግንባታን ለማገዝ የሚያስችሉ ስራዎች፤ የወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ዘርፉን ለማቃቃት የተሰሩ የአካዳሚ ግንባታ እና የስቴዲየም ደረጃውን የማሻሻልና የማሳደግ፤ በቀጣይ ስድስት ወራት ተጠናቆ ወደ ስራ የሚገባው ባለ አምስት ፎቅ የቢሮ ህንጻ፤ ለቢሮና ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውል የአስተዳደሩን ሲቪክ ማዕከል ጨምሮ የድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽንን የለውጥ እንቅስቃሴዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፤ የሱፕርቪዥን ቡድኑ በአስተዳደሩ በተመለከቷቸው የልማት ስራዎች መገረማቸውን ተናግረው ለሌሎች ክልሎችና አስተዳደሮች አርዓያ ሚሆኑና በተጨባጭ ውጤት በአጭር ጊዜ ለማስመዝገብ የሚያስችል ነው ብለዋል በተያያዘ በነገው ዕለት የድጋፍና ክትትሉ አጠቃላይ ግብረመልስ ለቢሮው ቀርቦ በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮች ቀርበው ሰፊ ውይይት የሚደረግበት ይሆናል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 12/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የሥራና ክህሎት ሚንስቴር ዴኤታ የሚመራ የሱፐርቪዥን ቡድን በዛሬው ዕለት በነበረው የመጨረሻ የጉብኝት መርሃግብር በድሬዳዋ አስተዳደር የተገነቡና እየተገነቡ ያሉ የልማት ፕሮጀክቶችን ጎበኙ፤ በጉብኝቱም የአስተዳደሩን የሥራ አመራር ኢንስቲትዩት የተቋማት አቅም ግንባታን ለማገዝ የሚያስችሉ ስራዎች፤ የወጣቶችና ስፖርት ኮሚሽን ዘርፉን ለማቃቃት የተሰሩ የአካዳሚ ግንባታ እና የስቴዲየም ደረጃውን የማሻሻልና የማሳደግ፤ በቀጣይ ስድስት ወራት ተጠናቆ ወደ ስራ የሚገባው ባለ አምስት ፎቅ የቢሮ ህንጻ፤ ለቢሮና ለተለያዩ አገልግሎቶች የሚውል የአስተዳደሩን ሲቪክ ማዕከል ጨምሮ የድሬዳዋ ፖሊስ ኮሚሽንን የለውጥ እንቅስቃሴዎች ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፤ የሱፕርቪዥን ቡድኑ በአስተዳደሩ በተመለከቷቸው የልማት ስራዎች መገረማቸውን ተናግረው ለሌሎች ክልሎችና አስተዳደሮች አርዓያ ሚሆኑና በተጨባጭ ውጤት በአጭር ጊዜ ለማስመዝገብ የሚያስችል ነው ብለዋል በተያያዘ በነገው ዕለት የድጋፍና ክትትሉ አጠቃላይ ግብረመልስ ለቢሮው ቀርቦ በቀጣይ ትኩረት ሊሰጣቸው የሚገቡ ጉዳዮች ቀርበው ሰፊ ውይይት የሚደረግበት ይሆናል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 12/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር እየተገነባ የሚገኘው የEASTRIP ፕጀክት የ Railway ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ህንጻ ግንባታ ያለበትን ደረጃ የድሬዳዋ አስተዳደር የብልጽግና ጽ/ቤት ኃላ
+5
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር እየተገነባ የሚገኘው የEASTRIP ፕጀክት የ Railway ምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ህንጻ ግንባታ ያለበትን ደረጃ የድሬዳዋ አስተዳደር የብልጽግና ጽ/ቤት ኃላፊና የኮሌጁ የቦርድ ሰብሳቢ ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ በተገኙበት የአንድ ወር እንዲሁም አጠቃላይ የግንባታ አፈጻጸም ግምገማ በትናንትናው እለት ተደረገ፡፡ በግምገማው ላይ የልህቀት ማእከሉ ያለበትን ደረጃ በአማካሪ ድርጅቱ ተወካይ ዮሀንስ እቁባይ እንዲሁም ግንባታውን ለመገንባት ውል የገባው የአተም ኮንስትራክሽ ድርጅት ተወካይ በኩል ቀርቧል፡፡ በሪፖርቱ መሰረትም የተለያዩ ውይይቶች የተደረገ ሲሆን  በመጨረሻም ክቡር አቶ ኢብራሂም ዩሱፍ እንዳሉት የህንጻው ግንባታው በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለታለመለት አላማ እንዲውልና ሀገራችን ኢትዮጵያ እንዲሁም ከተማችን ከማእከሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሁሉም አካላት በጋራ እና በርብርብ መስራት እንደሚገባ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ሚያዝያ 12/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በገጠር የስራ እድል ፈጠራ ዘርፍ ተደራጅተው የስራ አጥነትን ችግር ለመፍታት  ከስራ ጠባቂነት ወደ ስራ ፈጣሪነት በመሸጋገር ለሌሎች ስራ ከመፍጠር ባሻገር ለአርሶና አርብቶ እደር የግብርና ልማት እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክት ዘንድ በዚህም የገጠሩን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በከተማው የስራ እድል ፈጠራ ዘርፍ የተመዘገበውን ውጤት በቀጣይ ሁለቱንም ዘርፎች አጣምሮ በማቀናጀት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ይገኛል፤ በክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የሥራና ክህሎት ሚንስቴር ዴኤታ የሚመራ የሱፐርቪዥን ቡድን በዛሬው ዕለት በነበረው የጉብኝት መርሃግብር ቢሮው ሁለቱንም ዘርፎች በአንድ ላይ እንዲመራ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በአስተዳደሩ ገጠር ክፍል በግብርናው ዘርፍ ተደራጅተው ለሌሎች አርአያ በመሆን እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ የገጠር ስራ እድል ፈጠራ በዘርፉ የተሰማሩ አንቀሳቃሾችን ተዟዙረው ጎብኝተዋል፤ ግብርናና ገጠር ልማት የሰብልና እንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባና በዚህም የአርሶና አርብቶ አደሩን ማህበረሰብ የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽል የድጋፍና ክትትል ሥርዓቱን በማጠናከር የግብርና ልማትን የእሴት ሰንሰለት መሠረት ያደረገ የኢንተርፕራይዝ ልማት ሥራ በግብአት አቅርቦትና የገበያ ትስስር ከፋይናንስ አቅርቦት ችግርን ለመፍታት የተቀናጁ ስልቶችን መዘርጋት ጋር ቢሮው በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 11/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በገጠር የስራ እድል ፈጠራ ዘርፍ ተደራጅተው እና መንግስት የስራ አጥነትን ችግር ለመፍታት  ከስራ ጠባቂነት ወደ ስራ ፈጣሪነት በመሸጋገር ለሌሎች ስራ ከመፍጠር ባሻገር ለአርሶና አርብቶ እደር የግብርና ልማት እድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክት ዘንድ በዚህም የገጠሩን ፍትሃዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በከተማው የስራ እድል ፈጠራ ዘርፍ የተመዘገበውን ውጤት በቀጣይ ሁለቱንም ዘርፎች አጣምሮ በማቀናጀት የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ይገኛል፤ በክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የሥራና ክህሎት ሚንስቴር ዴኤታ የሚመራ የሱፐርቪዥን ቡድን በዛሬው ዕለት በነበረው የጉብኝት መርሃግብር ቢሮው ሁለቱንም ዘርፎች በአንድ ላይ እንዲመራ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በአስተዳደሩ ገጠር ክፍል በግብርናው ዘርፍ ተደራጅተው ለሌሎች አርአያ በመሆን እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ የገጠር ስራ እድል ፈጠራ በዘርፉ የተሰማሩ አንቀሳቃሾችን ተዟዙረው ጎብኝተዋል፤ ግብርናና ገጠር ልማት የሰብልና እንስሳት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ሰጥቶ መስራት እንደሚገባና በዚህም የአርሶና አርብቶ አደሩን ማህበረሰብ የኑሮ ሁኔታ የሚያሻሽል የድጋፍና ክትትል ሥርዓቱን በማጠናከር የግብርና ልማትን የእሴት ሰንሰለት መሠረት ያደረገ የኢንተርፕራይዝ ልማት ሥራ በግብአት አቅርቦትና የገበያ ትስስር ከፋይናንስ አቅርቦት ችግርን ለመፍታት የተቀናጁ ስልቶችን መዘርጋት ጋር ቢሮው በቀጣይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 11/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

Repost from N/a
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች የዐቢይ ፆምን ምክንያት በማድረግ ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር አካሄዱ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች በድሬዳዋ ሳባ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በመገኝት በዐቢይ ጾም ስርዓተ ቅዳሴ አከናውነው ለሚመለሱ የክርስትና እምነት ተከታዮች የተለያዩ ምግቦች እና የታሸጉ ውሃዎችን በማቅረብ ማእድ የማጋራት መርሃ ግብር አካሂደዋል፡፡ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሚያዝያ 11/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

Repost from N/a
photo content
+9

photo content
+9

በተያያዘ ዜና በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ ኢንደስትሪዎችና ኤጀንሲዎች ጉብኝት የተደረገ ሲሆን የሥራ ቦታዎች በተገቢው ሊሟሉ የሚገቡ የሴፍቲ ቁሳቁሶች መሟላታቸውና ጥቅም ላይ መዋላቸውን ከማረጋገጥ አንጻር የታዩ ጥሩ አፈጻጸሞችን ማስፋት እና ክፍተት የሚታይባቸውን ኢንደስትሪዎች ጊዜ ሳይሰጡ ማስተካከያ እንዲያደርጉም በጉብኝቱ ወቅት የሥራና ክህሎት ሚንስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ አሳስበዋል፤ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 10/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የሥራና ክህሎት ሚንስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን አምስተኛ ቀን ውሎ ከኢሠማኮ እና ከአሰሪ ኮንፈደሬሽን ተወካዮች ጋር ውይይት አካሄደ፡፡ በዚህም ውይይት የኢንዱስትሪ ሰላም በዋናነት የአሰሪና ሠራተኛ ግንኙነትና የሙያ ላይ ደህንነትና ጤንነት ጉዳዮችን በማንሳት በተለይም አሰሪና ሰራተኞች በህብረት ድርድር እና በህብረት ስምምነት አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ትግበራና አፈጻጸም ምን እንደሚመስል ለመመልከት ተችሏል በቀጣይም ማህበራቱ ከቢሮው ጋር ያላቸውን ቅንጅት በማጠናከር የአሰሪና ሠራተኛ ግንኙነት በአዲሱ ትርክት የመተካት አስፈላጊነት ላይ የተያዘ ግንዛቤ ይህንን መሰረት ያደረገ ድጋፍ ለሰራተኛም ሆነ ለአሰሪ ማህበራት የማስረፅ ሥራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል የሚለው ተመላክቷል የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 10/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የሥራና ክህሎት ሚንስቴር የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኘውን አጠቃላይ የሥራና ክህሎት እንቅስቃሴ ዙሪያ ንቅናቄ ለመፍጠር እንዲያስችል ክትትልና ድጋፍ የማድረግ ሥራ በዛሬው ዕለትም ቀጥሎ አንድ ማዕከላትና የኢንተርፕራይዞች ጉብኝት አካሄደ፡፡ በዚህም በአስተዳደሩ የሚገኙ የተመረጡ የወረዳ አንድ ማዕከላት ጉብኝት ሲደረግ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተቋቋመ ጊዜ አንስቶ ዘርፉ የሚመራባቸውን እሳቤ አጥርቶ በየደረጃው ለሚገኙ ባለድርሻ አካላት የተልዕኮ ግልፅነት ፈጥሮ ከመስራት አኳያ በተለይም በሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ መሠረት ያደረጉ የሪፎርም ተግባራት ላይ ያተኮረ ሆኗል፤ በመሆኑም አንድ ማዕከላቱ የክህሎት መር የሥራ ዕድል ፈጠራ ሪፎርም ተግባራዊ በማድረጉ ረገድ የሥራ ዕድል ፈጠራ ተግባራትን ከአጠቃላይ የኢኮኖሚ ልማት ሥራዎች ጋር አስተሳስሮ የመፈፀም አቅጣጫ አፈፃፀም በምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝና ከዚሁ ጋር በተያያዘ •  ከፍተኛ የማደግ አቅም ያላቸው ቢዝነሶችን ለይቶ ከመደገፍ፤ •  ፈጠራን መሠረት ያደረገ የመስሪያና የመሸጫ ቦታ ዝግጅት፤ •  የሥራ ሃሳብ መፈልፈል (Incubating business ideas)፤ •  ኢ-መደበኛ ቢዝነሶችን ወደ መደበኛ ማሸጋገር፤ •  የELMIS ምዝገባ ሂደት፤ •  የምርታማነት ምክክር መድረክ (Productivity dialogue)፤ በዋናነት ከላይ በተዘረዘሩት ጉዳዮች ላይ በአንድ ማዕከላቱ እና ኢንተርፕራይዞች በሚያመርቱበትና አገልግሎት በሚሰጡበት ቦታ በአካል በመገኘት ጉብኝት የተደረገ ሲሆን በጉብኝቱም ለታዩ ጉዳዮች በሃሳብና በቀጣይ ድጋፍ የሚደረግበትን አግባብ የተመላከተበት በጉብኝቱም የዛሬው ቀን ማጠቃለያ የአንድ ማዕከላቱ ፎረምን እንቅስቃሴ የሚያሳይ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በክቡር አቶ ዳንኤል ተሬሳ የሚመራው የሱፐርቪዥን ቡድን አባላት በተመለከቱት ነገር መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ