1 068
订阅者
+224 小时
无数据7 天
+230 天
帖子存档
በድሬዳዋ አስተዳደር የተዘጋጀው፥ የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ውድድር ዛሬም ቀጥሎ ተካሄደ።
ይህ ውድድር በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ እንዲሁም በሳይንስ፥ ቴክኖሎጂ እና ኢኖቬሽን ኤጀንሲ የጋራ ትብብር የተዘጋጀ ነው።
የተለያዩ የቴክኖሎጂ ፈጠራዎችን በማበልፀግ በአስተዳደሩ ጥቅም ላይ እንዲውሉ ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ፥ ይህ የፈጠራ ስራዎች ውድድር ጉልህ አስተዋፅኦ የሚያበረክት ይሆናል።
እየተካሄደ ባለው የቴክኖሎጂ ፈጠራ ስራዎች ውድድር ላይ ከአስተዳደሩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎችና መምህራን እየተካፈሉ ይገኛሉ።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 25/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
+5
#ዜና| የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጋር በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ በዛሬው እለት በቢሾፍቱ ተፈራረመ::
የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱ በዋነኝነት ሁለቱ ተቋማት በምህንድስናው ዘርፍ ለሚያደርጉት ቀጣይ ግንኙነት መሰረት የሚጥል መሆኑን በዩኒቨርሲቲው በኩል የስምምነት ሰነዱን የፈረሙት የዩኒቨርሲቲው ኘሬዝዳንት ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ ረጋሳ ገልፀዋል፡፡
ብርጋዴር ጄኔራል ከበደ አያይዘውም በቴክኖሎጂ እና ምህንድስናው ዘርፍ በጋራ የፈጠራ ስራን የሚያዳብሩ ትብብሮችን ስምምነቱ ከመፍጠሩ ባሻገር፤ የዩኒቨርሲቲው መምህራን የሰሯቸው የምርምር ስራ ውጤቶች ለፖሊ ቴክኒክ ኮሌጁ በአማራጭ ግብዓትነት እንዲቀርቡ የሚያስችል መሆኑን አመላክተዋል፡፡ ይህም ለሁለቱም ተቋማት የገበያ ትስስርን እንደሚፈጥርም ኮማንዳንቱ ጠቁመዋል፡፡
የኢንጅነሪንግ ኮሌጅ አዛዥ ኮሎኔል ኢዶሳ ቱፋ በበኩላቸው በኮሌጁ በምርምሩ ዘርፍ በርካታ የምርምር ስራዎችን ያበረከቱ መምህራን የሚገኙበት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
የመግባቢያ ስምምነቱ በሁለቱ ተቋማት ያለውን ሀብት በጋራ ለመጠቀም የሚያስችል ነው ሲሉም አዛዡ አክለዋል፡፡
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኩል የመግባቢያ ስምምነት ሰነዱን የፈረሙት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው በጋራ ለመስራት ላሳየው መልካም ፈቃድ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
ተግባር ተኮር ለሆኑ የምህንድስና ዘርፍ የትምህርት መስኮች ዩኒቨርሲቲው አስተዋፆው የጎላ እንደሆነም የኮሌጁ ዲን ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ መከላከያ ዩኒቨርሲቲ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
እንኳን ደስ አላችሁ!!
በድሬዳዋ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ በኩል በአስተዳደር ደረጃ ከተማ አስተዳደሩን ሊወክሉ የሚችሉ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን፤
በዚህም ውድድር ላይ በተለይም በኮሌጆች ላይ በአሰልጠኝ መምህሩ የሚነሱ ጥያቄዎች እና በሰልጣኝ ተማሪዎች ላይ የሚስተዋሉ መፍትሄ የሚሹ ጉዳዮች ማለትም አውቶሜትድ የተማሪዎች አቴንዳንስ ማኔጅመንት ሲስተም፣ ከጤና እና ደህንነት አጠባበቅ፣ የቢዝነስ ፕላን ጥራትና ውጤት ማሻሻል፣ የተሽከርካሪ የቴክኒክ ብቃት ምርመራ(ቦሎ) እና የማህበረሰብ ድጋፍ ላይ ትኩረታቸውን ያደረጉ ጥናቶች ቀርበው ውድድር የተካሄደ ሲሆን በዚህም ውድድር የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን የወከሉት ተወዳዳሪዎች 1ኛ እና 2ኛ እንዲሁም 4ኛ ደረጃን በማግኘት ውድድሩን በአሸናፊነት ጨርሰዋል፡፡
በተያያዘ ዜና በትናንትናው እለት ሲካሄድ በነበረው በከተማ አስተዳደር ደረጃ የከተማ አስተዳደሩን የሚወክሉ ተወዳዳሪዎችን ለመምረጥ በተዘጋጀው የክህሎት ውድድር ኮሌጃችንን በመወከል የተሳተፉ ሁሉም ተወዳዳሪዎች ከሌሎች ተወዳዳሪዎች ልቀው በመገኘት በአንደኛ ደረጃ ውድድሩን አጠናቀዋል፡፡ በዚህም የከተማ አስተዳደሩን በመወከል አዲስ አበባ በሚደረገው ውድድር ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ይሆናል፡፡
ኮሌጁን በመወከል ይህን አመርቂ ውጤት ላመጡትና ውጤቱ እንዲመጣ ቀን ከሌት ለሰሩት በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ፡፡
የኮሌጁ ኮምኒከሽን
መጋቢት 24/2017 ዓ.ም
+9
በድሬዳዋ አስተዳደር ''የመጋቢታዊያን የለውጥ ፍሬዎችና የነገ ተስፋዎች!'' ህዝባዊ የውይይት መድረክ በምስል።
Mariin Paanaalii Jijjiiramaa Ji'a Bitootessaa fi Abdii Boruu Mata-duree jedhuun Gaggeefamaa jiru suuraan
Madal halku dhig looga dhigay mudhihii isbedelka iyo rajooyinka ee ka curtay bisha cuur ama megabit aya lagu qabtay ismamulka Dir dhabe
የኩባንያ ውስጥ ስልጠና የኢንዱስትሪዎችን አቅም ከመገንባት ባሻገር በተቋማቱ መካከል መልካም ግንኙነትና ትብብርን ማጠናከሩ ተገለጸ፤
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴ/ሙያ/ት/ስ ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ከመንግስት ኮሌጆች ጋር በመተባበር የኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሰሩ ባለሙያዎችን የአሰራር፤ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምና የአገልግሎት አሰጣጥ ክፍተቶችን በመለየት በስራ ቦታቸው ላይ ለማብቃት የሚያስችል የኩባንያ ውስጥ ስልጠና መሰጠቱን አስታወቀ።
በዚህም በአስተዳደሩ ከሚገኙ ለትብብር ስልጠና መስጫነት በተመረጡ ኩባንያዎች በ3 የሙያ ዘርፎች ፤በማኑፋክቸሪንግ፤ ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ፤ እንዲሁም በአውቶሞቲቭ ዘርፎች በተመረጡ አሰልጣኞች በ4 ኩባንያዎች (ኒው ዌቭ ኢንዱስትሪያል ፒ ኤል ሲ፣ አርከን የጆንያ ፋብሪካ፣ ፍሬህይወት ጋራዥ፣ እንዲሁም አብሬ ጋራዥ) በድምሩ 60 ሰራተኞች ያለባቸውን የክህሎት ክፍተት በመለየት በስልጠና የማብቃት ስራ ተሰርቷል፡፡
የኩባንያ ውስጥ ስልጠና ዋና አላማ በኢንዱስትሪ ውስጥ ተሰማርተው የሚገኙ ባለሙያዎች በተሰማሩበት የስራ መስክ ያሉባቸውን የሙያ ክፍተት በመለየትና በማብቃት፤ የቴክኖሎጂ ክፈተቶችን በመሙላት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ሲሆን በተጨማሪም በትብብር ስልጠና ሂደት ሊያጋጥሙ የሚችሉ የጥራት ችግሮችን ከወዲሁ ለመፍታት ማስቻል ነው ሲሉ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ጀማል አደን ገልጸዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 23/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ ሲካሄድ የቆየው የክህሎት ውድድር ተጠናቀቀ፤
በአገር አቀፍ ደረጃ የክህሎት በዘርፉ ሰልጣኞች ዘንድ የውድድርና የተነሳሽነት መንፈስ ለመፍጠር የዘርፉን ገጽታ ለመገንባት ማስፈጸሚያ ዕቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መገባቱ ይታወሳል፡፡
የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ማዕከላት ኢንዱስትሪውን ተወዳዳሪ የሚያደርግ ምርጥ ቴክኖሎጂ በማቅረብና በማሽጋገር ምርታማ የሆነ ዜጋ በመፍጠር በአጠቃላይ የዘርፉን ተዋናዮች በማነቃቃት እና በገጽታ ግንባታ ረገድ የክህሎት ውድድር ማድረግ ወሳኝ በመሆኑ በአስተዳደሩ የሚገኙ ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች፤ በክላስተር ደረጃ እንዲሁም በክልል ደረጃ አስተዳደሩን የሚወክሉ ተወዳዳሪዎች የተለዩበት ሆኖ ተጠናቋል፤
በፌደራል ደረጃ ለሚካሄደው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የተለዩ ተወዳዳሪዎች በውድድሩ ከሚያገኙት ማበረታቻ በተጨማሪ የአጠቃላይ አሸናፊዎች በአህጉር እና በአለምአቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ ውድድሮች ላይ ሀገርን ወክለው የመሳተፍ ዕድል እንደሚመቻች ተገልጿል፡፡
በውድድሩ ማጠናቀቂ የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና የኢፌዲሪ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የጥናትና ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሀብታሙ ሙሉጌታ ውድድሩን ተመልክተው ተወዳዳሪ ሰልጣኞችንም ያበረታቱ ሲሆን በሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች የተሰሩ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 23/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በአስተዳደር ደረጃ የ2017 ዓ.ም የቴክኖሎጂና የሥራ ፈጠራ ውድድር መካሄድ ጀመረ፤
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምርና ስልጠና ኤጀንሲ እና የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ኤጀንሲ በጋራ ባዘጋጁት የ2017 ዓ.ም የቴክኖሎጂና የሥራ ፈጠራ ውድድር በአስተዳደሩ በሚገኙት የመንግስትና የግል ኮሌጆች በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተዋናዮች (በሰልጣኝ፣ አሰልጣኝ እና አንቀሳቃሾች እንዲሁም ተቋማት) በተጨማሪም የአጠቃላይ ት/ቤት ተማሪዎችና መምህራን የሚያሳትፍ ይሆናል፤
የውድድሩ ዋና አላማም በአስተዳደሩ የሚገኙ የፈጠራና የቴክኖሎጂ ችሎታ ያላቸውን ወጣቶችና የሙያ ባለቤቶች መካከል ከፍተኛ የውድድር ተነሳሽነትን መንፈስ በመፍጠር በመሰረታዊ የስራ ፈጠራ፤ ተግባራዊ ምርምር እና ቴክኖሎጂዎችን የመቅዳት፣ የማሻሻል፣ የመፍጠር፣ የማለማመድ እና የማሸጋገር ስራዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የጥራት ለውጥ ለማምጣት የሚያስችል አቅም እንደሚፈጥር ይታሰባል፤
በውድድሩ ማስጀመሪያ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እንደተናገሩት በዘርፉ ፖሊሲ በተመላከተው መሰረት የክህሎትና የቴክኖሎጂ አቅምን ሊያሳዩና ሊያሳድጉ የሚችሉ ውድድሮችን ማድረጉ በዘርፉ ተሳታፊ የሆኑ አካላትን ከማነቃቃት በዘለለ ከኢንደስትሪው ጋር የሚያገናኝ ድልድይ ሲሆን አስተዳደሩም የተለየ ትኩረት ሰጥቶ ድጋፍ እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡
የኢፌዲሪ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት የጥናትና ምርምር እና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሀብታሙ ሙሉጌታ ባስተላለፉት መልዕክት ቴክኖሎጂ በሀገር ደረጃ ከፍተኛ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ መሆኑን አንስተው የቴክኖሎጂ ፈጠራ ተወዳዳሪዎችን አበረታተዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መጋቢት 23/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አመራር እና ሰራተኞች 1446 ኛው የኢድ አል ፈጥር በዓልን በድሬዳዋ ህፃናት ማቆያና ማገገሚያ ማእከል ከሚኖሩ ህፃናት ጋር በጋራ አክብረዋል።
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛው ዓመተ-ሒጂራ የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
ታላቁ የረመዳን የፆም ወር በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ ትልቅ ስፍራ የሚሰጠው ወቅት ነው፡፡ በዚህ የፆም ወቅት ሕዝበ-ሙስሊሙ ራሱን ከክፉ ነገሮች በመቆጠብና ፈጣሪውን በዱአ በመለመን ፣ እንዲሁም ያለው ከሌለው ወገኑ ጋር ተካፍሎ በመብላትና ሰደቃ በማድረግ መልካምነትን የሚያሳይበት ጊዜ ነው፡፡
በተለይም በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታይ ወንድምና እህቶች በፆሙ ወቅት በተለያዩ ሥፍራዎች በተካሄዱ የኢፍጣር ሥነ ሥርዓቶች ላይ በመሳተፍ ለሙስሊም እህት ወንድሞቹ ያለዉን አጋርነት በተግባር ያሳየ ሲሆን ፤ ህብረተሰቡም እርስ በርስ የመደጋገፍ የኖረበት ባሕሉን በተጠናከረ መልክ ያስቀጠለበት እና የተቸገሩ ወገኖችንም በማገዝ በኩል ያሳየው ተነሳሽነት የሚደነቅ ነበር።
ቢሮው በዚሁ አጋጣሚ የተለያየ ድጋፍ የሚያደርግላቸውን ኢንተርፕራይዞች ከበዓላት ጋር በተያያዘ ተገቢ ያልሆነ የዋጋ መጨመር እንዳይፈጠርና በሚኖሩ የበዓል ገበያዎች የሚያቀርቧቸውን ምርትና አገልግሎቶች በጥራት በማዘጋጀት ህብረተሰቡን ተደራሽ እንዲያደርጉ በቂ ግንዛቤ የፈጠረ መሆኑን ለማስታወስ እወዳለሁ።
ይህንንም ሁሉ አቀፍ አድርገን በሌሎች ስራዎቻችን መልካም ዕሴቶቻችንን ጠብቀን በጎነትን እንድናሳይ ጥሪዬን እያቀረብኩ በ2017 ዓ.ም የሚከበረው የኢድ-አልፈጥር በዓል የሰላም፣ የጤና፣ የደስታ፣ የፍቅር፣ የአብሮነት፣ የመተሳሰብ እና የመረዳዳት በዓል እንዲሆን መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ፡፡
መልካም በዓል!
ኢድ ሙባረክ!
የድሬዳዋ አስተዳደር
ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
አቶ ሮቤል ጌታቸው
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
