1 064
订阅者
-124 小时
-47 天
+530 天
帖子存档
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት የብድር አሰጣጥና አመላለስ ዙሪያ በአስተዳደሩ ብድር ዋስትና ፈንድ ወስደው በስራ ላይ ለሚገኙ ኢንተርፕራይዞች የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መድረክ አዘጋጀ፡፡
በመድረኩም በድሬዳዋ አስተዳደር ከብድርና ዋስትና ፈንድ አሰጣጥና አመላለስ ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን መድፈን እንዲያስችል ከሥራና ክህሎት ቢሮ፤ ከፍትህና ፀጥታ ቢሮ የህግ ባለሙያ እና ከድሬ ማይክሮ ፋይናንስ እንዲሁም ከሚመለከታቸው የመንግስት ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል፡፡
ከተሳታፊዎችም ከብድር ተጠቃሚዎች ምልመላ አንስቶ እስከ አመላለስ ድረስ የታዩ እና እየታዩ ያሉ ችግሮች በተለይም በብድር ተጠቃሚዎች ዘንድ ያለው ለሚያገኙት ብድርና ዋስትና ፈንድ ያላቸው አመለካከት እና ተከታትሎ በመመለስ ረገድ ያጋጠሟቸውን ተግዳሮቶች በሰፊው አንስተዋል፡፡
በማጠቃለያውም የዳይሬክቶሬቱ ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ መቅደስ ከፈለኝ እንደተናገሩት ቢሮውን ጨምሮ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት የተካተቱበት ኮሚቴ መዋቀሩን ገልጸው ብድርና ዋስትና ፈንድ የወሰዱና በተሰጣቸው ጊዜ ተመላሽ ያላደረጉ ኢንተርፕራይዞችም በአጭር ጊዜ ውስጥ ሰርተው እንዲመልሱ ከስምምነት መደረሱን ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 29/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
አዋጁ ምን ይላል?
ክፍል አንድ
ከዜጎች መብት፣ ደህንነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እስከ ሀገራዊ ተወዳዳሪነትን የሚያረጋግጠው አዋጅ ቁጥር 1389/2017
መንግስት ለሀገር ውስጥ ሥራ ዕድል ፈጠራ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ይገኛል፡፡ ፈጠራና ፍጥነትን ማዕከል ባደረገው የሥራ አቅጣጫም የሥራ ዕድል ፈጠራ ስነ-ምህዳሩን ምቹ በማድረግ የዜጎችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ የህግና የአሰራር ማዕቀፎች እንዲዘጋጁ ተደርጓል፡፡
በኢንተርፕሪነርሺፕ እሳቤ የተለወጠ የሥራ ባህል በሥራ ዕድል ፈጠራ መስኩ ያለውን ሀገራዊ ፍላጎት ለማሟላት ሁሉን አቀፍ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡ ተጨባጭና ተስፋ ሰጪ ውጤቶችም ተገኝተውበታል፡፡
መንግሥት በሀገር ውስጥ የሥራ ዕድል ፈጠራ ላይ እያደረገ ያለው ጥረት እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ወደ ውጭ ሀገር ሄደው ለመሥራት ፍላጎትና ብቃት ያላቸው ዜጎች ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ ሰፊ ሪፎርም ሲያደርግ ቆይቷል።
በዚህ መነሻነትም መንግስት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪትን በበላይነት የሚመራበትንና የሚቆጣጠርበትን አዲስ አዋጅ ቁጥር 1389/2017 አውጥቷል። ይህ አዋጅ በዋናነት ትኩረት የሚያደርግባቸው 6 ቁልፍና አንኳር ጉዳዮች ናቸው፡፡ እነዚህም፡-
1️⃣የዜጎች መብት፣ ደህንነትና ሁለንተናዊ ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ
✅የቀድሞውን አሰራር ክፍተቶችን በመድፈን፣ ዜጎች በተለያዩ ሀገራት ባላቸው ችሎታና አቅም ሲሰሩ ሰብአዊ ክብራቸውና መብታቸው እንዲሁም ሁለንተናዊ ተጠቃሚነታቸው እንዲጠበቅ ቀዳሚ ትኩረት ይሰጣል።
2️⃣ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን መግታት
✅አዋጁ ከመዳረሻ ሀገራት ጋር በሚደረጉ የሁለትዮሽ ስምምነቶች ላይ ብቻ የተመሰረተ ስምሪትን ያበረታታል። ይህም በዜጎች ሕይወት ላይ አደጋ የሚደቅኑ ሕገ-ወጥ ደላሎችንና አዘዋዋሪዎችን ለመቆጣጠር የሚያስችል ጠንካራ መሣሪያ ነው።
3️⃣የግሉ ዘርፍ ተሳትፎ ማሻሻል
✅አዲሱ አዋጅ የግሉ ዘርፍ በሥራ ስምሪቱ ላይ ያለውን ሚና በሕግ ይወስናል፤ በተመሳሳይ መንግሥት በኤጀንሲዎች ላይ ያለውን የክትትልና የቁጥጥር አቅም በማጠናከር ተጠያቂነትን ያሰፍናል።
4️⃣ዘመናዊና በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት መስጠት
✅ከምልመላ እስከ ስምሪት ያለውን ሥራ ከሰው ንክኪ ነፃ በማድረግና የዜጎች እንግልትን በማስቀረት፣ አገልግሎቱን ቀልጣፋ፣ ግልጽና ፍትሃዊ የሚያደርግ ዲጂታል አሰራር የሕግ ማዕቀፍ እንዲኖረው አድርጓል።
5️⃣ሀገራዊ ተወዳዳሪነትን ማሳደግ
✅የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ የትምህርት ዝግጅት የሌላቸውንና በልምድ የተገኘ ክህሎት ያላቸውን ሠራተኞች ከማሰማራት ባሻገር የሰለጠኑና በከፊል የሰለጠኑ ባለሙያዎችን ማሳተፍ የሚያስችል ግልጽ አሰራርን በመዘርጋት፣ ኢትዮጵያ በዓለም የሥራ ገበያ ያላትን ተወዳዳሪነት ያረጋግጣል።
6️⃣ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ አሰራርን እውን ማድረግ
✅አዋጁ ኢትዮጵያ የተቀበለቻቸውን ዓለም አቀፍ የሠራተኛ መብት ስምምነቶች ጋር የተናበበ በመሆኑ፣ ስምሪቱ በዓለም አቀፍ መመዘኛዎች ተቀባይነት ያለው እንዲሆን አስችሏል።
ስለ አዋጁ ዝርዝር መረጃ በሁሉም ይፋዊ የማህበራት ትስስር ገፆቻችን በተከታታይ የሚወጡ ይሆናል፡፡
📣ለማንኛውም አስተያየትና ጥቆማ
👉 በ9138 ነፃ የሥልክ መስመርን ወይም
👉ኢሜይል:- info@mols.gov.et ላይ ያድርሱን
ህጋዊና ደህንነቱ የተጠበቀ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት፤ ለሁለንተናዊ ተጠቃሚነት!
#SafeMigration #Proclamation1389/2017
ጥር 29/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPt
በ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የድጋፍና ክትትል ፕሮግራም በአምስት የግል ኮሌጆች እና በሶስት የመንግስት ኮሌጆች እንዲሁም በሀያ አራት አጫጭር ስልጠና መስጫ ተቋማት በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
ይህም የድጋፍና ክትትል በቢሮው የሚገኙ ባለሙያዎች በሁለት ቡድን ተዋቅረው እያካሄዱ የሚገኝ ሲሆን በቀንና በምሽት በኮሌጆቹ በአካል በመገኘት በዋናነትም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጥራትን ለማስጠበቅና ለማረጋገጥ የተደረገ ያለውን ጥረት በድጋፋዊ ሱፐርቪዥን የሚያግዝ መሆኑም ታውቋል፡፡
በዚህም በየተቋማቱ የሚካሄደው የስልጠና ፕሮግራም ሁሉም አሰልጣኝ መምህራን የሚሰጡት ስልጠና በዕቅድ ላይ ተመስርተው ስለመስጠታቸው፤ እያንዳንዱ የስልጠና ፕሮግራም በተቀመጠው መመሪያና አላማ መሰረት እየተሰጠ ስለመሆኑና ተያያዥ ለስልጠና አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶች መሟላታቸውንና የስልጠና ቦታዎች አመቺነትና ጥራት ላይ ተገቢው ቁጥጥር መደረጉን ተመልክቷል፡፡
የድጋፍና ክትትል ፕሮግራሙ እንደተጠናቀቀም ለቢሮውና ሁሉም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆቹ በተገኙበት ውጤቱ በሪፖርት የሚቀርብ መሆኑን በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 29/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
ስራ ፈጣሪና የቴክኖሎጂ ባለቤት የሚሆኑ ወጣቶችን ለማፍራት ሁሉም ባለድርሻ አካለት በጋራ በመሆን ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከተለያዩ የአንደኛ ደረጃና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ የሳይንስ ትምህርቶች ላይ ዝንባሌና የፈጠራ ሃሳብ ላላቸው ወጣቶች በSTEM ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በዛሬው እለት አከናወነ፡፡
የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶችን በማስገንዘብ የፈጠራ ሃሳባቸውን በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ እንዲያዳብሩ በማድረግ ለሃገር የሚጠቅሙ ዜጎችን መፍጠር ያስፈልጋል ለዚህ ደግሞ ኮሌጁ ቀን ከሌት እየሰራ ይገኛል ያሉት በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲን ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ አያይዘውም ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ወጣቶችን በእውቀት በክህሎት በአመለካከት ከማሰልጠን ውጪ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች በመቀበል እንዲሁም ሊሰሩት ያሰቡትን ቴክኖሎጂ ወደ መሬት አውርደው ለራሳቸው ብሎም ለሃገራቸው የሚተርፍ ቴክኖሎጂዎችን እንዲፈጥሩና ሃሳባቸውን ወደ ቢዝነስ እንዲቀይሩ የተለያዩ ድጋፎችን ያደርጋል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ም/ዲኗ እንደገለጹት ስራ ፈጣሪና የቴክኖሎጂ ባለቤት የሚሆኑ ወጣቶችን ለማፍራት ሁሉም ባለድርሻ አካለት በጋራ በመሆን ሊሰሩ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በመድረኩ ላይ በኮሌጁ ውስጥ ተማሪዎች ቢመጡ በምን አይነት መንገድ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶቻቸውን ማደበር እንደሚችሉ ግንዛቤ የተፈጠረ ሲሆን በመቀጠልም በተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ጉብኝት በማድረግ የመድረኩ ፍጻሜ ሆኗል፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 27/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
ስራ ፈጣሪና የቴክኖሎጂ ባለቤት የሚሆኑ ወጣቶችን ለማፍራት ሁሉም ባለድርሻ አካለት በጋራ በመሆን ሊሰሩ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከተለያዩ የአንደኛ ደረጃና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ የሳይንስ ትምህርቶች ላይ ዝንባሌና የፈጠራ ሃሳብ ላላቸው ወጣቶች በSTEM Power ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በዛሬው እለት አከናወነ፡፡
የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶችን በማስገንዘብ የፈጠራ ሃሳባቸውን በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ውስጥ እንዲያዳብሩ በማድረግ ለሃገር የሚጠቅሙ ዜጎችን መፍጠር ያስፈልጋል ለዚህ ደግሞ ኮሌጁ ቀን ከሌት እየሰራ ይገኛል ያሉት በመድረኩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ም/ዲን አቶ ወ/ሮ ትግስት በዙ ኢሆኑ አያይዘውም ኮሌጁ ከተመሰረተበት ጊዜ አንስቶ በርካታ ወጣቶችን በእውቀት በክህሎት በአመለካከት ከማሰልጠን ውጪ የፈጠራ ሃሳብ ያላቸውን ወጣቶች በመቀበል እንዲሁም ሊሰሩት ያሰቡትን ቴክኖሎጂ ወደ መሬት አውርደው ለራሳቸው ብሎም ለሃገራቸው የሚተርፍ ቴክኖሎጂዎችን እንዲፈጥሩና ሃሳባቸውን ወደ ቢዝነስ እንዲቀይሩ የተለያዩ ድጋፎችን ያደርጋል ብለዋል፡፡
በተጨማሪም ም/ዲኗ እንደገለጹት ስራ ፈጣሪና የቴክኖሎጂ ባለቤት የሚሆኑ ወጣቶችን ለማፍራት ሁሉም ባለድርሻ አካለት በጋራ በመሆን ሊሰሩ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
በመድረኩ ላይ በኮሌጁ ውስጥ ተማሪዎች ቢመጡ በምን አይነት መንገድ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶቻቸውን ማደበር እንደሚችሉ ግንዛቤ የተፈጠረ ሲሆን በመቀጠልም በተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ጉብኝት በማድረግ የመድረኩ ፍጻሜ ሆኗል፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 27/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+9
በድሬዳዋ አስተዳደር ከስደት ተመላሽ ወገኖችን እንዲሁም ወጣቶችን በተለያዩ ሙያዎች አሰልጥኖ ወደ ስራ የማስገባት ተግባር በስፋት እየተከናወነ እንደሚገኝ ተገለፀ፡፡
መቀመጫቸውን አዲስ አበባ ካደረጉ ኢሮፒያን ዩኒየን፣ ከእንግሊዝና ከስዊድን ኤንባሲ እንዲሁም በኢትዮጵያ ከሚገኘው የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (አይ ኦ ኤም) ፅህፈት ቤት የተውጣጣ ልዑካን ቡድን ከስደት ተመላሾችን መልሶ የማቋቋም አቅምን የማሳደግ ስራዎች ላይ ከድሬዳዋ አስተዳደር ጋር ምክክር አድርጓል።
በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ ስደተኛ እና ከስደት ተመላሽ ወገኞች የስራ እድል ከመፍጠር አኳያ እንዲሁም ስደትን በዘላቂነት ከመከላከል አኳያ በአስተዳደሩ አበረታች ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙ በአካባቢው የሚገኙ ወጣቶችን በእውቀትና በክህሎት የዳበሩ እንዲሆኑ የተለያዩ ሞያዎችን በማሰልጠን ከራ አልፎ ለሃገር የሚተርፍ ስራ እያከናወነ እንዳለ በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው ተናግረዋል።
በአስተዳደሩ እንደሁም በኮሌጁ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ክቡር አቶ ሮቤል ጌታቸው ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ እንዲሁም የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን ልኡክ ቡድኑ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅን ተዘዋውሮ ከጎበኙ በኋላ ወጣቶችን ከጠባቂነት መንፈስ ተላቀው ተወዳዳሪና ክህሎት ያለው ትውልድ እንዲሆን ብሎም የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ ኢንተርፕራይዝ እንዲሆኑና በሚያገኙት ገቢም የተሸለ ነግር መፍጠር እንዲችሉ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እየተሰራ ያለው ስራ እጅግ የሚያረካና በሀገር አቀፍ ደረጃም በተሞክሮነት የሚወሰድ መሆኑን የልኡክ ቡድኑ አባላት ገልፀዋል።
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥር 27/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሰልጣኝ ልማትና የተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የአጫጭር ስልጠና እና የምዘና መሳሪያዎች ክለሳ እንዲሁም በመሰረታዊ ክህሎት ሞጁሎች ላይ ከኮሌጅ ዲፓርትመንት ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሄደ፤
በዚህም መሰረት ከሁለቱ የመንግስት ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች የተውጣጡ የዲፓርትመንት ተጠሪዎችና የስልጠና ባለሙያዎች ስራዎችን በመገምገምና ያጋጠሙ ችግሮችን በመንቀስ መሻሻል ያለባቸውን በመከለስና ተጨማሪ ቨርዥኖች ለማዘጋጀት የሚያስችል የጋራ መግባቢያ መድረክ አድርገዋል፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኮሌጆች/ተቋማት ከዘመናዊ የኢንዱስትሪ ፍላጎቶች ጋር እንዲናበቡ በዲጂታል ቴክኖሎጂ በማቀናጀት ለወደፊት የኢዱስትሪው ፍላጎትን የሚያሟሉ ምሩቃንን በጥራት በማዘጋጀት ለገበያው በማቅረብ ስራ አጥነትን ለመቀነስ ከሚሰራቸው ስራዎች አንዱ የተቋም ውስጥ የምዘና መሳሪያዎችን ባለፈው አመት አዘጋጅቶ በስራ ላይ ማዋሉን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደን አስታውሰዋል።
በተጨማሪም በፌደራል ደረጃ የተዘጋጁ 5 የመሰረታዊ ክህሎት ሞጅሎች አስፈላጊነት ላይ ወቅቱን የጠበቀ ስለመሆኑ ውይይት በማደረግ ለማውረድም ቅድመ ዝግጅት ስራዎች እንደሚሰሩ እና አሰልጣኞችን የማብቃት ስራዎች በቀጣይ ትኩረት የተሰጣቸው መሆኑን አቶ ጀማል ተናግረዋል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥር 26/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
