1 063
订阅者
无数据24 小时
-77 天
+230 天
帖子存档
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ትግበራ ላይ ለሚሰሩ ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ::
በቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ስራ ሂደት የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ክፍል ስር ለሚሰሩ ነባር እና በአዲስ ለተመቡ አሰልጣኝ መ/ራን በትግበራው አፈፃፀምና በቀጣይ የስራ እንቅስቃሴ ላይ የግብዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል::
መድረኩን በንግግር ያስጀመሩት የኮሌጁ የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ዋና ስራ ሂደት ሀላፊና ም/ል ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ በ2017 በጀት ዓመት በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ትግበራው በብዙ ተግዳሮቶች ውስጥ አመርቂ ስራ ለሰሩት ነባር ባለሙያዎች ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን አክለውም በ2018 በጀት ዓመት ለሚኖረው የኢ/ኤ/አ ትግበራ በቅንጅትና በጥራት ለማከናውን እንዲረዳን ይህን የግንዛቤ መድረክ ማዘጋጀት ማስፈለጉንም ገልፀዋል::
የግንዛቤ ስልጠናውን የኢዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ኬዝቲም ሀላፊ በሆኑት አሰልጣኝ መ/ር አቤል ዘገየ አማካኝነት ለተሳታፊዎች የተሰጠ ሲሆን በዚህም የ4ቱ የትግበራ ማእቀፎች አተገባበርን በተመለከት ሰፋ ያለ ግንዛቤ መስጠት የተቻለ ሲሆን በተጨማሪም በ2018 በጀት ዓመት የኢ/ኤ/አ እቅድን በተመለከተ ከፈፃሚዎች ጋር መወያየት ተችሏል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ጥቅምት 06/2/2018 ዓ.ም
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአፍሪካ የICT ትምህርትና ስልጠና ልህቀት ማእከል ፕሮጀክት ጅማሮ ማብሰሪያ የመሰረት ድንጋይ በክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በዛሬው የማስቀመጥ ስነ-ስርዓት ተካሄደ።
ይህ በዛሬው እለት ግንባታውን ለማስጀመር የመሰረት ድንጋይ የተቀመጠው የG+4 ICT ህንፃ ግንባታን በተቀመጠለት ግዜ በማጠናቀቅ ከተማችን የጀመረችውን “ስማርት ድሬ” ኢንሸቲቭ እውን ለማድረግ ብቁ የሰለጠነ ዜጋ በማቅረቡ ረገድ ሚናው የጎላ እንደሆነ በእለቱ ተነግሯል።
ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ አጠቃላይ 3.3 ሚሊዮን ዩሮ የተመደበ ሲሆን ከዚህም ውስጥ ለግንባታው የሚፈጀው 2.3 ሚሊዮን ዩሮ ወይም 384 ሚሊዮን ብር ነው፡፡ 2 ሚሊዮን ዩሮ የሚሆነው በጀርመን ባንክ (kfw) ድጋፍ እና 300 ሺ ዩሮ የሚሆነው በአስተዳደሩ መዋጮ የሚሸፈን እንደሆነ በግንባታ ማስጀመሪያ ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡
ህንጻው በአጠቃላይ 42 ክፍሎች የያዘ ሲሆን በዋናነት ስማርት ክፍል፣ የኮምፕዩተር ላብራቶሪ፣ የምርምር ክፍል፣ መማሪያ ክፍል፣ የዲዛይን ስቱዲዮ፣ ኮንፈረንስ ክፍል፣ ዲጂታል ቤተ መጽሃፍት እና ሌሎችም እንደሚገኙበት ተገልጿል።ግንባታውን ለማጠናቀቅ 14 ወራትን እንደሚፈጅ ታውቋል።
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ጥቅምት 6/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ
You tube: Dire Dawa Polytechnic College(DDPTC)
Facebook: https://web.facebook.com/Dire Dawa Polytechnic College Regional Flagship TVET Institute
Telegram: https://t.me/diredawapolytechniccollege
TikTok: tiktok.com/@diredawapolytechnicollege
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ከተለያዩ ፋብሪካዎች ለተወጣጡ አሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማዘጋጀት በኢንዱስትሪ ሰላም፤ በስራ ሁኔታ እና በሙያ ደህንነትና ጤንነት ላይ ስልጠና ሰጠ።
በዚህም ስልጠና በዋናነት መሰረታዊ የሥራ ሁኔታ በአሰሪና ሰራተኛው መሃል ያሉ ጠቅላላ ግንኙነቶች የሰራተኛውን የቅጥር ሁኔታ፣ የስራ ሰዓት እና የሰራተኛውን ጥቅማጥቅም የሚመለከቱ ጉዳዮች በአሰሪና ሰራተኛ አዋጁ 1156/2011 ላይ በተደነገገው መሠረት ከላይ የተጠቀሱት ነጥቦች ህግና ስርዓታቸው ተከብሮ የአሰሪና ሰራተኛው ግንኙነት ጤናማ የሚሆንበትና ሰላማዊ የስራ ከባቢ እንዲኖረው ግንዛቤ የሚፈጥርላቸው ሆኗል፡፡
በተጨማሪ የሥራ ቦታዎች ምቹ፣ ጤናማና ከአደጋ የተጠበቁ እንዲሆኑ በማስቻል ምርታማነትን ከማረጋገጥ አኳያ ከሙያ ደህንነት እና ጤንነት አጠባበቅ አንፃር ስልጠና የተሰጠ ሲሆን በዚህም ለግንዛቤ ያክል የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ላይ በተመለከተው መሰረት የሙያ ደህንነትና ጤንነትን በተመለከተ አሠሪዎች፡-
🔑 ሠራተኞች የሚሰሩት ሥራ ሊያስከትልባቸው ስለሚችለው አደጋ እንዲሁም በጤንነት ላይ የሚደርስ ጉዳትን ለማስወገድ ስለሚያስፈልገው ጥንቃቄ ተገቢውን እርምጃ ይወስዳሉ፣
🔑 የአደጋ ተከላካይ ሠራተኛ ይመድባሉ፤ የሙያ ደኅንነትና ጤንነት ኮሚቴ ያቋቁማሉ፣
🔑 ለሠራተኞች የአደጋ መከላከያ መሣሪያ ልብስና ሌሎች ቁሳቁሶችን ያቀርባሉ፤ ስለአጠቃቀሙም መመሪያ ይሰጣሉ፣
🔑 በሥራ ምክንያት የሚመጡ በሽታዎችንና አደጋዎችን ይመዘግባሉ፤ ለሥራ ሁኔታዎች መቆጣጠሪያ አገልግሎት ያሳውቃሉ፣
🔑 እንደሥራው ጠባይ አዲስ ለሚቀጠሩ ሠራተኞች በራሳቸው ወጪ የጤና ምርመራ እንዲካሄድላቸው ያደርጋሉ፣
🔑 በአደገኛ ሥራ ላይ የሚሰሩ ሠራተኞች እንደአስፈላጊነቱ የጤና ምርመራ እንዲያገኙ ያደርጋሉ፣
🔑 ሆኖም ይህ ምርመራ ኢትዮጵያ ያፀደቀችው የዓለም አቀፍ ስምምነት ካላስገደደ በስተቀር የኤች.አይ.ቪ/ ኤድስ ምርመራን አይጨምርም፤
🔑 የድርጅቱ የሥራ ቦታና ግቢ በሠራተኞች ደኅንነትና ጤንነት ላይ አደጋ የማያስከትል መሆኑን ያረጋግጣሉ፣
🔑 በድርጅቱ ልዩ ልዩ የሥራ ሂደት በሚገኙ ፊዚካላዊ፣ ኬሚካላዊ፣ ባዮሎጂካዊ፣ ኢርጎኖሚካዊና ሥነ ልቦናዊ ምንጮችና ምክንያቶች ሳቢያ በሠራተኞች ደኅንነትና ጤንነት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ተገቢውን ጥንቃቄ የማድረግ ግዴታ አለባቸው፡፡
በመሆኑም የሠራተኞችን የሙያ ደህንነትና ጤንነት በማረጋገጥ ጤናማ አምራች ዜጋ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለፁት በቢሮው የአሠሪና ሠራተኛ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መሐመድ ኢብራሂም ይህ ስልጠና በብዙ መልኩ አሠሪና ሠራተኛው አዋጁ ባስቀመጠው የሙያ ደህንነትና ጤንነት መብትና ግዴታቸውን ተረድተው የሚያከብሩበትንና የሚያስከብሩበትን ብሎም የጋራ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በመውሰዳቸው በቀጣይ ደህንነትና ጤንነቱ የተጠበቀ ሙያተኛ፣ ምርታማና ሰላሙ የተጠበቀ ኢንዱስትሪ መፍጠር ያስችላቸዋል ብለዋል ፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 6/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+8
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአፍሪካ የICT ትምህርትና ስልጠና ልህቀት ማእከል ፕሮጀክት ጅማሮ ማብሰሪያ የመሰረት ድንጋይ በክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀር በዛሬው የማስቀመጥ ስነ-ስርዓት አካሂደናል።
ይህ በዛሬው እለት ግንባታውን ለማስጀመር የመሰረት ድንጋይ ያስቀመጥነው የG+4 ICT ህንፃ ግንባታን በተቀመጠለት ግዜ በማጠናቀቅ ከተማችን የጀመረችውን “ስማርት ድሬ” ኢንሸቲቭ እውን ለማድረግ ብቁ የሰለጠነ ዜጋ በማቅረቡ ረገድ የበኩላችንን ሚና እንድንወጣ በእጅጉ የሚያግዘን ይሆናል።
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
📢 የሕዝብ አስተያየት ለማሰባሰብ የተላለፈ ጥሪ
👉 የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ማስፈፀሚያ ረቂቅ መመሪያ💬
የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ዘላቂ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅ ቁጥር 1389/2017 መውጣቱ ታወቀ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በአዋጁ አንቀፅ 84(2) መሠረት ማስፈፀሚያ መመሪያ የማውጣት ሥልጣን ተሰጥቶታል።
በዚህ መሠረት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱን ማስተግበሪያ ረቂቅ መመሪያ እየዘጋጀ ነው።
ስለሆነም ማንኛውም ዜጋ ወይም ድርጅት በተዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ላይ ያላችሁን አስተያየት እንድታቀርቡ በአክብሮት እየጠየቅን ረቂቅ መመሪያውን በሚኒስቴር መስሪያቤቱ ይፋዊ የቴሌግራም(https://t.me/FDRE_MoLSofficial)ና የዋትስአፕ ቻናል(https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y) ላይ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
🗓 ጊዜ:
👉ይህ ማስታወቂያ ከተወጣ ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት
📥 በምን መልኩ: ያላችሁን ማንኛውም አስተያየት በሚከተሉት አድራሻዎች ሊያደርሱን ይችላሉ:-
✅info@mols.gov.et ወይም
✅ molsministeroffice@gmail.com
ጥቅምት 6/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: t.me/fdre_mols
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
📢 የሕዝብ አስተያየት ለማሰባሰብ የተላለፈ ጥሪ
👉 የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ማስፈፀሚያ ረቂቅ መመሪያ💬
የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ዘላቂ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት አዋጅ ቁጥር 1389/2017 መውጣቱ ታወቀ። የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በአዋጁ አንቀፅ 84(2) መሠረት ማስፈፀሚያ መመሪያ የማውጣት ሥልጣን ተሰጥቶታል።
በዚህ መሠረት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱን ማስተግበሪያ ረቂቅ መመሪያ እየዘጋጀ ነው።
ስለሆነም ማንኛውም ዜጋ ወይም ድርጅት በተዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ ላይ ያላችሁን አስተያየት እንድታቀርቡ በአክብሮት እየጠየቅን ረቂቅ መመሪያውን በሚኒስቴር መስሪያቤቱ ይፋዊ የቴሌግራም(https://t.me/FDRE_MoLSofficial)ና የዋትስአፕ ቻናል(https://whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y) ላይ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
🗓 ጊዜ:
👉ይህ ማስታወቂያ ከተወጣ ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት
📥 በምን መልኩ: ያላችሁን ማንኛውም አስተያየት በሚከተሉት አድራሻዎች ሊያደርሱን ይችላሉ:-
✅info@mols.gov.et ወይም
✅ molsministeroffice@gmail.com
ጥቅምት 6/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: t.me/fdre_mols
TikTok: tiktok.com/@mols_official
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y
የመሰረታዊ የስራ ሁኔታ እና የሙያ ደህንነትና ጤንነት የስራ ሁኔታ ቁጥጥር በማድረግ በአሰሪና ሰራተኛው መሀከል መግባባት በመፍጠር የስራ ቦታዎችና የኢንደስትሪ ሰላም የማስፈን ስራዎች ተጠናክረው በሰፊው እየተሰሩ እንደሆነ ተገለጸ፡፡
በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት በተሰጠው ተግባርና ሃላፊነት መሰረት የግል ድርጅቶችን መሰረታዊ የስራ ሁኔታዎች በመቆጣጠር ድጋፍና ግብረመልስ የመስጠት ተግባራትን በማከናወን የስራ ቦታዎችና የኢንደስትሪ ሰላምን የማስፈን ተግባራትን በሰፊው እያከናወነ እንደሚገኝ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ መሐመድ ኢብራሂም አስታውቀዋል፡፡
የሥራ ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 4/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ይህ ሰንደቅ ዓላማ በላባችንና በእውቀታችን ሀገራችንን ወደከፍታ ለማውጣት ለእያንዳንዳችን ኃላፊነት ይሰጠናል፤ ሀላፊነት ያጎናጽፈናል፡፡
እያንዳንዱ አርሶ አደርና አርብቶ አደር በማሳውና በጓሮው፤ አእያንዳንዱ የሕዝብ አገልጋይ በሙያው፣ በችሎታውና በክህሎቱ፤ እያንዳንዱ ወጣት በጉልበቱና በፈጠራው፤ እያንዳንዱ ምዑር ደግሞ በእውቀቱ የኢትዮጵያን የእድገት ግስጋሴ ለማሳካት የበኩሉን እንዲወጣ ሀገራዊ ጥሪዬን አቀርባለሁ፡፡
ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
"ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፤ ለብሔራዊ አንድነታችን፤ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ"
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት 18ኛው የብሔራዊ ሰንደቅ አላማ ቀን በዓል በኮሌጁ በደማቅ ሁኔታ ተከብራል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
አሰልጣኝ መምህር ፋቃዱ ላቤና በስራ ባልደረቦቹ እጅግ ተወዳጅ፣ቅን እና ሰው አክባሪ የነበረ ሲሆን ሀገሩንና ህዝቡን ለማገልገል ደከመኝ ሰለቸኝ የማይል እጅግ ታታሪ ሰው ነበር፡፡
ለአሰልጣኝ መምህሩ ወዳጆች፣የስራ ባልደረቦች እንዲሁም ቤተሰቦች ፈጣሪ እንዲያጽናናችሁ የኮሌጁ ማህበረሰብ ይመኛል፡፡
"ሠንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፤ ለብሔራዊ አንድነታችን፤ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ"
18ኛው የብሔራዊ ሰንደቅ አላማ ቀን በዓል የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እና የቢሮው አመራሮችና ሰራተኞች እንዲሁም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ በደማቅ ስነ-ስርዓት ተከበረ::
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 3/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
