ch
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

前往频道在 Telegram
1 065
订阅者
-124 小时
-47
+530
帖子存档
ለሥራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያ በተለያዩ የውጭ አገራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ለምትፈልጉ ዜጎች የኢትዮጵያ መንግስት ከአገራቱ ጋር በፈጠረው ስምምነት እድሉ ተመቻችቷል። በዚህም እስከ ሚያዚያ 2
ለሥራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያ በተለያዩ የውጭ አገራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ለምትፈልጉ ዜጎች የኢትዮጵያ መንግስት ከአገራቱ ጋር በፈጠረው ስምምነት እድሉ ተመቻችቷል። በዚህም እስከ ሚያዚያ 26/2018 ዓ.ም ባሉት የሥራ ቀናት በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እና በሁሉም የአስተዳደሩ ወረዳ የሥራና ክህሎት ማስተባበሪያዎች በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ለሥራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያ በተለያዩ የውጭ አገራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ለምትፈልጉ ዜጎች የኢትዮጵያ መንግስት ከአገራቱ ጋር በፈጠረው ስምምነት እድሉ ተመቻችቷል። በዚህም እስከ ሚያዚያ 2
+2
ለሥራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያ በተለያዩ የውጭ አገራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ለምትፈልጉ ዜጎች የኢትዮጵያ መንግስት ከአገራቱ ጋር በፈጠረው ስምምነት እድሉ ተመቻችቷል። በዚህም እስከ ሚያዚያ 26/2018 ዓ.ም ባሉት የሥራ ቀናት በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እና በሁሉም የአስተዳደሩ ወረዳ የሥራና ክህሎት ማስተባበሪያዎች በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና የተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት በአስተዳደሩ የሚገኙ የግል ኮሌጆች ላይ ኢንስፔክሽን ማካሄዱ ተገለጸ። በዚህም ኢንስፔክሽን ኮሌጆች የሚሰጡትን ትምህርትና ስልጠና ደረጃውን በጠበቀ መልኩ እየተሰጠ ስለመሆኑና ጥራትን ለማስጠበቅ የተደራጁ የውስጥ የጥራት ኮሚቴዎች ስለመቋቋማቸው እና ጦራትን ለማስጠበቅ ያከናወኗቸውን ተግባራት ለመገምገም ለመደገፍ የሚታዩ ችግሮችን ደግሞ በአጭር ጊዜ በማስተካከል እርማት እንዲወስዱ ታሳቢ ያደረገ ነው። የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ ስለ ኢንስፔክሽኑ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠናን ጥራት ለማምጣት ይህ ለአገራችንና ለከተማችን እድገት አስፈላጊ በመሆኑ ጉዳዩ ከሚመለከታቸው አካላትና ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራና በቅንጅት  ሴክተሮችን ባሳተፈ መልኩ እየተካሄደ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዝያ 19/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ምዝገባ ብቻውን በቂ አይደለም ! የባዮሜትሪክ ምዝገባዎን አጠናቅቀው የሰራተኛ መለያ(Labor ID) ማግኘትዎ የመጀመሪያው እና ትልቁ እርምጃ ነው። ነገር ግን ስራ ለማግኝት በእነዚህ አማራጮች መጠቀም
ምዝገባ ብቻውን በቂ አይደለም ! የባዮሜትሪክ ምዝገባዎን አጠናቅቀው የሰራተኛ መለያ(Labor ID) ማግኘትዎ የመጀመሪያው እና ትልቁ እርምጃ ነው። ነገር ግን ስራ ለማግኝት በእነዚህ አማራጮች መጠቀም ይኖርብዎታል ፦ 1. lmis.gov.et ድረ-ገጽ ላይ በመግባት National Job portal ላይ በየቀኑ የሚወጡ በመቶዎች የሚቆጠሩ አዳዲስ ስራዎችን በመመልከት ለእርስዎ ተስማሚ የሆነው ስራ ላይ ያመልክቱ። 2.ማህበራዊ ገጾቻችንን በመጎብኘት እንዲሁም የምንለጠፋቸውን የስራ ዕድሎች በንቃት በመከታተል ከማስታወቂያው ጋር ተያይዞ በተቀመጠው ማስፈንጠርያ አማካኝነት ማመልከቻዎን ያስገቡ። 3.SMS መልዕክቶችን ይከታተሉ በስልክዎ ከ E-LMIS ወይም ከ MoLS (ስራና ክህሎት ሚኒስቴር) የሚላኩ መልዕክቶችን በየጊዜው ያረጋግጡ። የቃለ መጠይቅ ጥሪዎች እና ጠቃሚ መረጃዎች የሚደርስዎት በዚህ መንገድ ነው። https://lmis.gov.et/

ለወጣቶችና ሴቶች አዲስ የሥራ ዕድል የከፈተው የግብርና ኢንተርፕራይዞች ልማት ፕሮጀክት የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የግብርና ኢንተርፕራይዞችን ለማዘመንና የእሴት ሰንሰለቱን የተከተለ የሥራ ዕድል ለወጣቶችና ሴቶች ለመፍጠር ያለመ ፕሮጀክት ተግባራዊ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ፣ ሥራ ሥምሪትና ገበያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ሰለሞን ሶካ ከክልል ቢሮ ኃላፊዎች ጋር በፕሮጀክቱ አፈጻጸም እና የቀጣይ አቅጣጫዎች ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ ሚኒስትር ዴኤታው በዙም (Zoom) ባደረጉት ውይይት እንደገለጹት፤ ፕሮጀክቱ ግብርናውን ከባህላዊ አሰራር በማውጣት ወደ ዘመናዊ የንግድ ሥራ (Agri-Business) ለመቀየር አቅም ሰንቆ የተነሳ ነው። ፕሮጀክቱ ለሚቀጥሉት አምስት ዓመታት የሚዘልቅና ዘንድሮ ወደ ትግበራ የገባ መሆኑን ገልጸው አፈጻጸሙን ውጤታማ ለማድረግና የታለመለትን ግብ እንዲመታ ክልሎች ፕሮጀክቱን በልዩ ትኩረት የቅርብ ክትትል በማድረግ እንዲደግፉ አሳስበዋል፡፡ ፕሮጀክቱ በግብርና ዘርፍ የወጣቶችንና የሴቶችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ዘላቂ ምህዳር መፍጠሪያ በመሆኑም በባለቤትነት ስሜት አፈጻጸሙን መከታተል እንደሚገባ ጨምረው ገልጸዋል እያንዳንዱ አካባቢ ያለውን የግብርና ምርት አቅም መለየት ለሥራ ዕድል ፈጠራው ስኬት መሠረት ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው ይህም በየአካባቢው ያለውን ጸጋ መሠረት ያደረገ እሴት ሰንሰለትን የተከተለ የሥራ ዕድል መፍጠር እንደሚያስችል ገልጸዋል፡፡ በግብርና ኢንተርፕራይዝ የሚሳተፉ ዜጎች የሳይኮሜትሪክ ፈተና (Psychometric Test) እንዲወስዱ በማድረግ ብቃታቸውን መሰረት ያደረገ ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግ ይገባል ብለዋል፡፡ ፕሮጀክቱ የዘርፉ ተቋማትን የማስጸም አቅም የሚገነባ ሲሆን ለኢንተርፕራይዞች ደግሞ ቴክኒካዊ ስልጠናዎች፤ የንግድ ልማት ምክር አገልግሎት፤ የፋይናንስ አቅርቦት እና የተሳለጠ የገበያ ትስስር ድጋፍ ያደርጋል። ሚያዚያ 12/2018 ዓ.ም፤ ©️ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

ለመላ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! **** የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ
ለመላ የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል! ****       የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ

"መጋቢት 24 የድሬዳዋን ልዕልና አረጋግጧል!" ሀገራዊ ለውጡ እውን የሆነበትን 8ኛ ዓመት የሚዘክር ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ በድሬዳዋ አስተዳደር  ተካሂዷል። የሰልፉ ተሳታፊ የሆኑ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች እንዳሉት መጋቢት 24  የሃገራችን ተምሳሌታዊ ጉዞ እና የተመዘገቡ ስኬቶች መነሻ ነዉ፤ በለውጡ መንግሥት እየተከናወኑ ያሉ የልማት ተግባራትን በመደገፍ፣ በቀጣይም የተሻለ ስራ እንዲሰራ ከመንግሥት ጋር በትብብር እንደሚሰሩ የሚያረጋግጡ መልዕክቶችነም አስተላልፈዋል። ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሃገር! የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሚያዚያ 1/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የሥራ ማዕከላት ሶስተኛ ሩብ አመት የሥራ አፈጻጸም እና የሶስተኛ ዙር ብቃት ቅጥርን በተመለከተ ከወረዳ ሥራ ማዕከላት አመራሮች እና ባለሙያዎች ጋር የውይይት እና የግምገማ መድረክ  ተካሄደ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ በውስጡ ከሚገኙ ዘርፎች የስራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አንዱ ሲሆን ለዜጎች የስራ እድልን በመፍጠር አሁን ያለውን የሥራ አጥ ቁጥር ለመቀነስና የስራ ባህልን በማጎልበት የሚያስፈልጓቸውን የሙያና የክህሎት ስልጠናዎች ወስደውና ወደ ስራ እንዲሰማሩ በማመቻቸትና ራሳቸውን ከስራ አጥነት እንዲያላቅቁ በማድረግና በመተግበር ላይ ይገኛል፡፡ በዚህም የሚመለከታቸው የቢሮው አመራርና ባለሙያዎች እንዲሁም የወረዳ ሥራ ማዕከላት አመራሮችና ባለሙያዎች በተገኙበት በ2018 በጀት አመት ሶስተኛ ሩብ አመት አጠቃላይ የስራ ዕድል ፈጠራ በተለይም በብቃት ፕሮግራም የተሰሩ ስራዎች አፈጻጸም ላይ ሁሉም የወረዳ ሥራ ማዕከላት አፈጻጸማቸው ቀርቦ ሰፊ ውይይት በማድረግ በቀጣይ በአጭር እና በረጅም መሰራት በሚገባቸው ስራዎች ላይ መወያየትና መግባባት መፍጠር ተችሏል፡፡ በመድረኩም ላይ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ በቢሮ እና በሥራ ማእከላቱ መናበብ የተሰሩ መልካም ስራዎችን አበረታተው በቀጣይ በተለይ የአካባቢ ፀጋዎችንና ዕድሎችን በየሴክተሩ የመለየት ሥራ በአስተዳደሩ ውስጥ በሶስቱ ዋና ዋና የስራ እድል የመፍጠሪያ የስራ ዘርፎች ማለትም በግብርና በኢንዱስትሪ እና በአገልግሎት ዘርፍ ስራ ፈላጊዎችን ከማሰማራት አንጻር የአካባቢ ጸጋ ናቸው ተብለው የታመነባቸውን የጸጋ አይነቶች እና የመስሪያ ቦታዎችን የመለየት ስራን አጠናክሮ በመስራት ተጨባጭ ስራዎችን በይበልጥ ማስፋትና መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 30/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለኢንተርፕራይዞች ስኬትና ዘላቂነት፦ የጀማሪ ኢንተርፕራይዞችን አቅም በመገንባት ውጤታማና ተወዳዳሪ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግርና እንዱስትሪ ኤክስ
+6
ለኢንተርፕራይዞች ስኬትና ዘላቂነት፦ የጀማሪ ኢንተርፕራይዞችን አቅም በመገንባት ውጤታማና ተወዳዳሪ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግርና እንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በአስተዳደሩ ከተለያዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ:: ለኢንተርፕራዝ አንቀሳቃሾች የአቅም ግንባታ ስልጠናውን የሰጡት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ሀላፊ አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ የስልጠናው ዋና አላማ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ውጤታማ፣ ተወዳዳሪና ዘላቂነት እንዲኖራቸው ለማስቻል የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከትንሽ ተነስተው ትልቅ ቦታ ለመድረስ ያላቸውን ራዕይ አጠናክረው በቁርጠኝነት ሊተጉ እንደሚገባም ተናግረዋል:: በእለቱ ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠናው በዋናነት..... - የንግድ ስነ-ምግባር.. - የገበያ ጥናት.. - የፋይናንስ አያያዝ.. - የቴክኖሎጂ ሽግግርና ካይዘን.. - የስራ ፈጠራና የንግድ ኢንኩቤሽን እና.. - የደንበኞች አያያዝ ላይ ያተኮረ ስልጠና በሰፊው ግንዛቤ የተሰጠበት መድረክም ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መጋቢት 30/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኮሌጁን የቀጣይ 15 አመታት እቅድ ወደ ተግባር ለመቀየር የኢንዱስትሪውና የባለድርሻ አካላት ትልቁን ሚና ሊወስዱ እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የEASTRIP ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ዩኒት አዘጋጅነት ከመጋቢት 23 - 25 ቀን 2026 የሚቆየው በEASTRIP ፕሮጀክት የሚደገፋ የ6 ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች የቀጣይ 15 አመት እቅድ የደረሰበትን ግምገማ እና መሪ እቅድ ልማት አውደ ጥናት መርሀ ግብር የተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት መከናወኑ የሚታወስ ነው፡፡ በዚህ መሰረትም በአውደ ጥናቱ ላይ የተገኙ ግብአቶችን በመጠቀም ከኢንዱስትሪውና ከተለያዩ ባላድርሻ አካላት በሰነዱ ላይ ሃሳብ እና ግብዓት ለማሳባሰብ የሚረዳ መርሃ ግብር በዛሬው እለት ተከናወነ፡፡ በዛሬው እለት ለባድርሻ አካላት የቀረበው ሰነድ ተግባራዊ ሲደረግ በባቡር ኢንዱስትሪ ዘርፍ ኮሌጁን የልህቀት ማእከል የሚያደርግ ስለሆነ ይህንንም አላማ ለማሳካት ኢንዱስትሪውና የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ከኮሌጁ ጋር በቅርበት ሊሰሩ እንደሚገባ የሚታመን ነው፡፡ የኢንዱስትሪን ትስስርን ለማሳደግ የኮሌጁ የኢንዱስትሪ አማካሪ ቦርድን ኮሚቴን 50 ፐርሰንት ከኢንዱስትሪው እንዲሆንና ኢንዱስትሪው በቴክኒክና ሙያ ላይ የባለቤትነት ስሜት እንዲፈጠርና ኮሌጁ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ላይ አንድ እርምጃ ለማሳደግ ይረዳናል ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ የኮሌጁ ዲን አያይዘውም ኮሌጁ የሚያሰለጥናቸው ሰልጣኞች ከማስመረቅ በዘለለ ኢንዱስትሪውን ማንቀሳቀስ የሚችሉና የፈጠራ ባለቤት እንዲሆኑ እንዲሁም ኮሌጁ በገቢ እራሱን የቻለ ተቋም እንዲሆን ከኢንዱስትሪወው ጋር ያለን ግንኙነት ማሳደግ ያስፈልጋል፡፡ይህ በዛሬው እለት የሚቀርበው እቅድም ኢንዱስትሪዎች ከኮሌጁ ጋር የሚኖረው ግንኙነት የተሸለ እና ጠንካራ እንዲሆን ያደርገናል ብለወል፡፡ በዛሬው እለት በተከናወነው አውደ ጥናት ላይ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በቀጣይ 15 አመታት ሊደርስበት ያሰበውን የልህቀት ማእከልነት ለኢንዱስትሪና ለተለያዩ ባለ ድርሻ አካላት ያቀረበ ሲሆን በመድረኩ የተገኙ ባለድርሻ አካላትም ኮሌጁ እስካሁን ሲሰራቸው የነበሩና በቀጣይ በስፋት ሊሰራቸው ያሰባቸው ስራዎች ወሳኝና ኮሌጁን በተለየ አይነት መልኩ ወደፊት ሊያራምዱ የሚችሉ ስራዎች በግብአትነት ሰጥተዋል፡፡ በመድረኩ ላይም የሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እና የቢሮው ዳይሬክተሮች፣የኮሌጁ የኢንዱስትሪ አማካሪ ቦርድ አባላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 30/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa - Telegram 频道 @bolsdd 的统计与分析