ch
Feedback
ግጥም ቤት✍

ግጥም ቤት✍

前往频道在 Telegram

ግጥም የምትጥም ፤ እንደ ዶሮ ቅልጥም.....

显示更多
1 112
订阅者
无数据24 小时
-27
+930
帖子存档
በአዲስ አበባ ወንዶች ምክንያት ከአፍሪካ በውበት ሶስተኛ ሆነናል። እንደውም መኪና የሌላት ሴት አናገባም!! @getembate @getembate
በአዲስ አበባ ወንዶች ምክንያት ከአፍሪካ በውበት ሶስተኛ ሆነናል። እንደውም መኪና የሌላት ሴት አናገባም!! @getembate @getembate

<<<<<<<<98>>>>>> [መለያየት] ተረሳና ውዱ ጊዜ ፥ ባንችልበት ወርቁን ማየት፣ እልፍ አስበን እንዳልነበር ፥ መንገድ ሆነ መ
<<<<<<<<98>>>>>> [መለያየት] ተረሳና ውዱ ጊዜ ፥ ባንችልበት ወርቁን ማየት፣ እልፍ አስበን እንዳልነበር ፥ መንገድ ሆነ መለያየት። እጅ ለእጅ ተያይዞ ፥ እንደማለፍ ከርሞ ዳግም መሻር በደቂቃ ፥ ለመራመድ ተፈራርሞ። ባይኖር እንኳ አስታራቂ ፥ የሚያስማማ ብናጣ ሰው፣ መለያየት ፋሽን ሆኖ ፥ አብሮነትን ብንበጥሰው። ህልማችንን ውሃ በላው ፥ ተስፋችንም ቀረ ባጭር፣ ልቦቻችን እንዲሳሳብ ፥ ጠፍቶ ባገር ፍቅር ሚጭር። በአንድ ለሊት ፥ በአንድ ጀንበር ቃልን አጥፎ ፥ ኪዳን መስበር። እያዳር ሰፍቶ እርቀታችን ፥ እንስሳ እስኪበልጠን፣ ምን ጠቀመን ብቸኝነት ፥ ነፃነትስ መቼ ሰጠን። ዘመን ሲሰለጥን ፥ እኛ ግራ ገብቶን፣ ጎጇችን ፈረሰ ፥ ኩራት ትዕቢት ሰቶን። @keysopia @getembate @getembate

ፋክ [keysopia] &lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;97&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt; ‎ገፍትር በየተራ ፥ ግፋ ባቅምህ ልክ ‎ለጥቅ እንደንፋስ ፥ አቡነው ሲጥልክ። ‎ባህ
ፋክ [keysopia] <<<<<<<97>>>>>>> ‎ገፍትር በየተራ ፥ ግፋ ባቅምህ ልክ ‎ለጥቅ እንደንፋስ ፥ አቡነው ሲጥልክ። ‎ባህሩን አተራምስ ፥ ቅደድ ደልዳላውን ‎ተራራውን ግመስ ፥ ስለብ ቀውላላውን። ‎ ‎ማጣትህ ላይ ቀልድ ፥ ኪሳራን ሳቅበት ‎መከራን መርቀው ፥ ሞት እንዲጠራበት። ‎ፍርሃት ውስጥ ተመቻች ፥ ይላኝታህ ስር ተኛ ‎ለክፋት ቀድሰህ ፥ ምሰል መተተኛ። ‎ ‎ፓንት የሌለው ሱሪ ፥ በቀዳዳ ሸሚዝ ‎ፆታህን ቀይረህ ፥ እንደጄደን ስሚዝ። ‎እብዶች መናሃሪ ላይ ፥ ጥርስህን እየፋክ ‎እንደ ጉንፋናም ሰው ፥ አክታ እተፋክ፣ ‎በናቁህ ፊት ቆመህ ፥ በላቸው አንተም ፋክ። ‎ ‎@getembate@getembate

photo content

&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;96&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt; ለእናቴ! ፍጡር ብቻ አይደለሽ ፥ የሞት ሲሳይ ቀማሽ ህይወት ነሽ ፣ ለሰማሽ ብፁህ አን
<<<<<<<<<96>>>>>>>> ለእናቴ! ፍጡር ብቻ አይደለሽ ፥ የሞት ሲሳይ ቀማሽ ህይወት ነሽ ፣ ለሰማሽ ብፁህ አንቺነትሽ ፥ ስጋ ለበስ ፍጡር ሰውነት ላይ ፀንቷል ፥ በኖርሽበት ቁጥር። ያለ ምስራቅ ጀንበር ፣ ያለ ሰማይ ኮከብ ማዕበል ላይ የሚጓዝ ፥ ታምረኛ መርከብ። ካማጥሽኝ አንስቶ ፥ እስከ ጡትሽ ወተት ድግምት የማይሰብረው ፥ ይዞኝ አንድ መተት። እንደ ዛፍ አደኩ ፥ እንደ አበባ ፈካሁ ከእቅፍሽ ስር ነቃሁ ፥ በሌላም ተተካሁ። ምስኪን ነበርሽ.... ከመከራሽ ጋራ የምትታገዪ አይኖቼ ስር ገብተሽ ብርሃን የምታዪ ምስኪንማ ነበርሽ.... ሁሉም የሚሰብርሽ ካንቺ ደስታ በላይ ፥ ስቃይ የሚቀርብሽ። ወድቄ እንዳልቀር ፥ መኖር ከኔ ገዝፋ ከህመም ባታስጥዪኝ ፥ ሰተሽኛል ተስፋ። እማዬ አለሜ ፥ እማ የልቤ ወዳጅ ጦር ሜዳ ዘምታለው ፥ አንቺን መውደድ ቢሆን ፥ የአላማዬ ግዳጅ።
እናቴ ስለሆንሽ እኮራለሁ!!!!
@ከkeysopia @getembate @getembate

&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;95&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt; [ባንቺ በኩል] ያልተቋጨ ውዝፍ ዕዳ &nbsp;&nbsp; አስመዝኜ በዕድሜዬ መጠን፣ እንጥልጥል ውስጥ ተዘፍቄ &
<<<<<<<95>>>>>> [ባንቺ በኩል] ያልተቋጨ ውዝፍ ዕዳ    አስመዝኜ በዕድሜዬ መጠን፣ እንጥልጥል ውስጥ ተዘፍቄ     ፍርሃት ደዌዬን ስታጠን። ድቅድቅ ያለ ተስፋ   ዘግቶ የልቤን በር፣ ባንቺ በኩል ገባ   ደርሶ አዲስ ጀንበር። @keysopia @getembate @getembate

የሺህ ዘመን ተስፋ ፥ ባንድ ቃል ፈርሶ፣ ‎ሁሉም ከጨከነ ፥ የደም በቀል ወርሶ። ‎ከደናግል መሀል ፥ እርጉዝ ሴት ተነስታ፣ ‎ለምድር ጭፍሮች ፥ የሞት አክሊል ነስታ። ‎ ‎ጭጋጉ ስር ሸሽታ ፥ እንደም
የሺህ ዘመን ተስፋ ፥ ባንድ ቃል  ፈርሶ፣ ‎ሁሉም ከጨከነ ፥ የደም በቀል ወርሶ። ‎ከደናግል መሀል ፥ እርጉዝ ሴት ተነስታ፣ ‎ለምድር ጭፍሮች ፥ የሞት አክሊል ነስታ። ‎ ‎ጭጋጉ ስር ሸሽታ ፥ እንደምትኖር መንፈስ፣ ‎ደስታ ሳትል ሀዘን ፥ እንደልቧ ስትፈስ። ‎ጭንቅ ምጧ መቶ ፥ ጊዜ ወርቋን ንዶ፣ ‎ጭኗን አስከፈተው ፥ ሰው መሳዩ ዘንዶ። ‎ ‎ድምፅ አልባው ጅረት ፥ በንፋስ ዳንስ ስር፣ ‎ሀሳብ ልቡን ቃኝቶ ፥ እልፍ አለሙን ሲያስር። ‎የሸለቆ ታላቅ ውበት ፥ እንደመፍካት ባዲስ ፋና፣ ‎አክ ተብሎ እንደምራቅ ፥ እመንገድ ላይ ተተፋና። ‎ዳግም ክንፍ አብቅሎ ፥ ባይችል ጎጆ መስራት፣ ‎ጎዳናው ላይ አንቀላፋ ፥ ህልሙ ውስጥ ሊኖራት። ‎ ‎@keysopia ‎ ‎@getembate@getembate ‎ ‎

ድምፃዊ ሰማኸኝ በለው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል። ነፍስ ይማር😔 @getembate @getembate
ድምፃዊ ሰማኸኝ በለው ባደረበት ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል። ነፍስ ይማር😔 @getembate @getembate

6ትናንሽ ታሪኮች ፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣ 1 በአንድ ወቅት በአንድር መንደር የሚኖሩ ሰዎች ዝናብ በመጥፋቱ ምክንያት ፀሎት ሊያደርጉ ወሰኑ፡፡ፀሎቱ በሚያደርጉበት ቀን ሁሉም የመ
6ትናንሽ ታሪኮች ፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣   1  በአንድ ወቅት በአንድር መንደር የሚኖሩ ሰዎች ዝናብ በመጥፋቱ ምክንያት ፀሎት ሊያደርጉ ወሰኑ፡፡ፀሎቱ በሚያደርጉበት ቀን ሁሉም የመንደሩ ሰዎች ተሰባሰቡ፣አንድ ትንሽ ልጅ ብቻ ዣንጥላ ይዙ ተገኘ፡፡ (ይእምነት ይባላል፡፡) ፣፣፣፣፣፣፣፣፣ 2  ህጻን ልጅህን ወደላይ እየወረወርህ ስታጫውታት በደስታ ትፍነከነካች እንጂ አታለቅስም ፡፡ምክንያቱም መልሰህ እንደምትቀልባት ታውቃለችና!! ይህም እርግጠኝንት ይባላል፡፡ ፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣ 3  በእያንዳንዱ ምሽት ወደ አልጋችን ስንሄድ በነገው ማለዳ በህይወት እንደምንቆይ ምንም ዓይነት ማረጋገጫ ባይኖረንም አላርም(የማንቂያ ደወል) ሞልተን እንተኛለን!! ይህም ተስፋ ይባላል፡፡ ፣፣፣፣፣፣፣፣፣ 4 ወደ ፊት ምን እንደምንሆን (እንደሚሆን)እውቀት ሳይኖረን ታላላቅ እቅዶችን እንነድፋለን!!! ይህ ደሞ በራስ *,መተማማን ይባላል፡፡** ፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣፣ 5 ዓለም ላይ የሚወርደውን መከራና ስቃይ እናያለን ይሁን እንጂ አሁንም እንጋባለን ይህም ፍቅር ይባላል፡፡ ፣፣፣፣፣፣ 6 አንድ ሽማግሌ በለመበሰው ቲሸርት ላይ እንዲህ የምትል አንዲት ጉሩም ዐረፍተ ነገር ተጽፋለች “እኔ የስድሳ ኣመት ሽማግሌ አይደለሁም ፣የአርባ አራትመታት የሕይወት ልምድ ያለኝ የአስራ ስድሰት ኣመት ወጣት እንጂ” ይህ ለራሳቸእን ያለንን አመለካከት ያሳያል፡፡ ፣፣፣፣ መልካም ምሽት ይሁንላችሁ!! እምንት ፣እርግጠኝነት ፣ተስፋ ፣በራስ መተማማን ፣ ፍቅርና ለራሳችሁ ጥሩ አመለካካት ሳይለያችሁ ኑሩ !!! @getembate @getembate

ሰበበኛ ‎ ‎ባይገባት - ‎ወንድነት የከዳው ፥ ገላ ተሸክሜ፣ ‎በኑሮ ውጣ ውረድ ፥ አናቴን ኮርክሜ። ‎ክፉ አትዪ ብዬ ፥ ሀዘኔን ብደብቅ፣ ‎ጠላኝ ብላ አሰበች ፥ እኔ እሷን ስጠብቅ። ‎ ‎ከተሻለ ብ
ሰበበኛ ‎ ‎ባይገባት - ‎ወንድነት የከዳው ፥ ገላ ተሸክሜ፣ ‎በኑሮ ውጣ ውረድ ፥ አናቴን ኮርክሜ። ‎ክፉ አትዪ ብዬ ፥ ሀዘኔን ብደብቅ፣ ‎ጠላኝ ብላ አሰበች ፥ እኔ እሷን ስጠብቅ። ‎ ‎ከተሻለ ብዬ ፥ ሳደርግ ነገን ተስፋ፣ ‎በማይሆን ኩነኔ ፥ ስሜን አስቀስፋ። ‎እንደ ኮብላይ ሽፍታ ፥ አርጓት ሽብር ሽብር ‎ቁጣ ቁጣ ሸቷት ፥ ስትሆን እንደነብር። ‎ ‎ንፋስ እንዳመጣ ፥ እንደቆሼ ብናኝ ‎በቅዠት ማዕበል ፥ ግራ ገብቶኝ ስናኝ። ‎ንዴት ይሁን እብደት ፥ ውስጤን እያጋለው፣ ‎መዳፌ ስር ፌቷን ፥ አሳልፎ ጣለው። ‎ ‎ያልታሰበ ጥፊ ፥ ፊቶቿ ላይ አርፎ፣ ‎ሌቱም ዳግም ነጋ ፥ ባንድነት ተኳርፎ። ‎ ‎በንቅሳት ቀለም- ‎ደረት ላይ ያተሟት ፥ የትዝታ ምስል፣ ‎በቻሏት ቁጥር- ‎ሳቆችን በርዛ ፥ ነፍሴን ስታቆስል። ‎መንፈሴ በአንድ ቃል ፥ ከቋጠረው እሳት፣ ‎እፍ አልኩባት- ‎ከህመሜ ቁራሽ ፥ እሷም እንዲደርሳት። ‎ ‎@keysopia ‎ ‎@getembate@getembate ‎ ‎ ‎ ‎ ‎ ‎

photo content

&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;92&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt; አይደለሁም በቃ እንደ ታመነ ቃል ፤ ወተት አላፈልቅም ሀዘኔን ሸሸጌ ፥ በ
<<<<<<<<<<92>>>>>>>>> አይደለሁም በቃ እንደ ታመነ ቃል ፤ ወተት አላፈልቅም ሀዘኔን ሸሸጌ ፥ በሳቅ አልደብቅም ባይኖረኝም ዕድል ውስጤን ሸፋፍኜ ሁኔታዬ በልጦኝ ፥ ነፍሴን አላጎድል። አይደለሁም በቃ ባይሳካ ህልሜ ፥ ባይወጣልኝ መንገድ ሚዛኔ ተዛብቶ ፥ ቆሜም ብንገዳገድ ያልታሰበ ህመም ፥ ልቤን ቢያቃጥልም ትታኝ ሂደች ብዬ ፥ ቤቴ ዳስ አልጥልም። በቃ አይደለሁም ብታምኑም ባታምኑም ፥ ከሌለች የለሁም ፍርስራሽ በድኔ ፥ ቢቆም ፣ ቢቀመጥም ለእሷ ሳቅን እንጂ ፥ ሀዘንን አይመርጥም። ሁሉም ሰው ቢል ጎንበስ ጭንቁ ተሸኝቶ በደስታ ቢዳበስ ግን ለኔ ጎድሎ ላንቺ የማካፍል ፥ ካልሆንኩኝ ጠበቃ እንደምታስቢኝ ፥ አይደለሁም በቃ። @keysopia @getembate @getembatd

&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;90&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt; (የፍቅር መዘዝ) ባይችል አቅም አንሶት ፥ ለምኖም ካቃተው፣ እብደትን ይመርጣል ፥ አንቺን እንደመተው። በ
<<<<<<<<90>>>>>> (የፍቅር መዘዝ) ባይችል አቅም አንሶት ፥ ለምኖም ካቃተው፣ እብደትን ይመርጣል ፥ አንቺን እንደመተው። በእልፍ እንስት መሀል ፥ ልዩ ሆነሽበት፣ አንቺን ባየበት አይን ፥ ሌላ ባይደግምበት በዚህ ሞቃታ አለም ፥ ፍቅርሽን ደርቦ፣ ፆሙን ይውልልሻል ፥ ገላሽን ተርቦ። ናፍቆት ነፍሱን ንዶ ፥ ሀሳቡን ቢሽረው፣ ፀበል ቢሞካክር ፥ ሌላ ሰው እንዲያምረው፤ ቄሱም ጋኔን ሆኖ ፥ ለክፎት አባረረው። በጠንቋይ ፣ በላባ ፥ በኡስታዝ ፣ በፓስተር፣ መንትር ተነቦልኝ ፥ በቬዳዎች ዶክተር። ያልተፈታ ቅኔ ፥ ፈውስ የሌለው ህመም፣ ልቤ ላይ ተጋልጦ ፥ እንደ ገዳይ  ቅመም እንቢ ባልሽኝ ቁጥር ፥ ፍቅሬ እየጨመረ፣ ጨርቅ ማቄን ጥዬ  ፥ አብድልሽ ጀመረ። @keysopia @getembate @getembate

ይህንን ያውቃሉ ??? ወደ ኤቨረስት ተራራ ጫፍ በሚወስደው መንገድ ላይ ከ200 በላይ አስከሬኖች ተቀምጠዋል። አስከሬኖቹ በከፍታ አውራጆች እንደ መለያ ሆነው ያገለግላሉ እናም... "Green Boots
ይህንን ያውቃሉ ??? ወደ ኤቨረስት ተራራ ጫፍ በሚወስደው መንገድ ላይ ከ200 በላይ አስከሬኖች ተቀምጠዋል። አስከሬኖቹ በከፍታ አውራጆች እንደ መለያ ሆነው ያገለግላሉ እናም... "Green Boots" የሚል ቅጽል ስሞች ተሰጥቷቸዋል። @getembate @getembate

ይህንን ያውቃሉ ? ኢድ አል አድሃ በዓለም ላይ ትልቁ ነጻ የምግብ ማከፋፈያ ሥርዓት የሚካሄድበት በዓል ነው! በኢድ አል አድሃ ዕለት የሚታረደው እንስሳ (በግ፣ ፍየል ወይም በሬ) ሥጋ በግዴታ በሦስት
ይህንን ያውቃሉ ? ኢድ አል አድሃ በዓለም ላይ ትልቁ ነጻ የምግብ ማከፋፈያ  ሥርዓት የሚካሄድበት በዓል ነው! በኢድ አል አድሃ ዕለት የሚታረደው እንስሳ (በግ፣ ፍየል ወይም በሬ) ሥጋ በግዴታ በሦስት እኩል ቦታ መከፈል አለበት፦ •  አንድ ሦስተኛው (1/3)፦ ለራስ ቤተሰብ •  አንድ ሦስተኛው (1/3)፦ ለዘመድ፣ ለወዳጅና ለጎረቤት (ሃይማኖት ሳይለይ) •  አንድ ሦስተኛው (1/3)፦ ምንም ለሌላቸው ድሆች እና ችግረኞች ይሰጣል። ይህ ሥርዓት በዓለም ላይ በቢሊዮን የሚቆጠር ኪሎ ግራም ሥጋ በአንድ ቀን ውስጥ ለድሆች በነጻ የሚታደልበትና በዓለም ላይ ተወዳዳሪ የሌለው ትልቁ የበጎ አድራጎት ሥርዓት ያደርገዋል። @amazing_fact_433 @getembate @getembate

ውድ ተከታዮቻችን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛ የኢድ አል-አድሃ(አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን፤ በዓሉ የሠላም ፣ የደስታ እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞታ
ውድ ተከታዮቻችን ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛ የኢድ አል-አድሃ(አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን፤ በዓሉ የሠላም ፣ የደስታ እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን፡፡    መልካም በዓል! @getembate @getembate

በ ዛቢያ &lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;&lt;90&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt;&gt; ብርሀን ጊዜ ደርሶ፥ ሲያዘቀዝቅ አይኑን ከድኖ ቀዬው ሞላ በየቤቱ
በ ዛቢያ <<<<<<<<<<90>>>>>>>>> ብርሀን ጊዜ ደርሶ፥ ሲያዘቀዝቅ አይኑን ከድኖ ቀዬው ሞላ በየቤቱ ፥ አንዱ ታሞ ሌላው ድኖ ጭንብል ለባሽ በጋሬጣው፥ አስመሳዩም ከነ ጣጣው፥ ሲኳትን ከዋለ ፥ መንገድ እንዳመጣው። በተስፋው ሳቅ በኩል እልፍ እየደከመው፣ ነገን እጅ ነስቶ ያድራል እያመመው። ምሽቱ  ልዩ ነው ፣ ህልም አላት መኝታው፣ ጎዶሎን ሞላች ፣ በቁም ያልተቻለውን  ሲጋደም አግኝታው። ደጋግሞ እያጠቃ- ልቡን ሲሰባብር፥ ጀርባ እንዳልሰጠው፣ ሀሳቡን ይገምዳል- ካለፈው መኖር ጋር ፥ ተስፋን እያማጠው። ጉልበቱ ቢዝል ፥ ንጋቱ መከራን ቢያዝል፥ አሁን ካለበት ጋር ፥ ለመሽቀዳደም፣ ውሎን ይጠይቃል ፥ ዛሬን ለመደምደም። @keysopia @getembate @getembate