943
订阅者
+424 小时
+357 天
+16330 天
帖子存档
†
🌼 [ አዘክሪ ድንግል ! ] 🌼
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
“ አዘክሪ ድንግል ንግደቶ ዘምስሌኪ እንዘ ትጐይዪ ምስሌሁ እምሀገር ለሀገር በመዋዕለ ሄሮድስ ንጉሥ ፤ አዘክሪ ድንግል ረኀበ ወጽምዐ ምንዳቤ ወሐዘነ ወኲሎ ዐጸባ ዘበጽሐኪ ምስሌሁ…”
[ ድንግል ሆይ ፦ ርጉም በኾነ በሄሮድስ ዘመን ከርሱ [ከልጅሽ] ጋራ ካገር ወደ አገር ስትሸሺ ካንቺ ጋር መሰደዱን አሳስቢ ፤ ድንግል ሆይ ረኀቡና ጥሙን ፣ ችግሩንና ጒዳቱን ከርሱ ጋራ የደረሰብሽን ጸዋትወ መከራ ኹሉ አሳስቢ ፤ ድንግል ሆይ ከዐይኖችሽ የፈሰሰውንና በተወደደ ልጅሽ ፊት የወረደውን መሪር እንባ አሳስቢ ፤ ጥፋትን ያይደለ ይቅርታን አሳስቢ መዐትን ያይደለ ምሕረትን አሳስቢ ፤ ለጻድቃን ያይደለ ለኃጥኣን አሳስቢ ፤ ለንጹሓን ያይደለ ለተዳደፉት አሳስቢ ]
[ አባ ሕርያቆስ ]
† † †
🌼 🍒 🌼
ታላቅ በሆነው እምነትሽ
ታላቅ በሆነው እምነትሽ ታመንኩኝ
ካለሽበት ገስግሼ መጣሁኝ
እናቴ ክብርሽን አንግሼ
ሆንኩኝ እንደ ህፃን ታድሼ
እናቴ ቅድስት አርሴማ
ዝናሽ ለዓለም ተሰማ
ስመጣ ባልጋ ነበረ
ተስፋዬም የተሰበረ
በእምነትሽ በፀበልሽ
ሰው ሆኜ ቆምኩኝ ደጅሽ
ልናገር ዝናሽን ላውራ
ይደነቅ የአምላክሽ ሥራ
ተጋድሎሽ የእምነትሽ ፅናት
ሆኖኛል የእምነቴ መብራት
ደምግባት ከንቱ ብለሽ
ለሰማይ ክብር ታጭተሽ
የእምነቴ አሰረ ፍኖት
በምልጃሽ አለሁ በህይወት
የልቡን ለነገረሽ
ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ
ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል
የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል
እርዳታሽ የደረሰለት
ያመጣል የልቡን ስለት
ላመኑሽ ፈውስሽ ቅርብ ነው
ባንቺ አፍሮ የሄደው ማነው
የልቡን ለነገረሽ
ፈጥኖ ይደርሳል መልስሽ
ዘንባባሽ ህይወት ይዘራል
የጠራሽ ማን አፍሮ ያውቃል
🕊 ▬▬ † ▬▬ 🕊
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ❝ የጠፋውን በግ የሚሻ ጠባቂ እርሱ ነው ❞ ]
🕊
አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ !
❝ ቀድሞ የተወለደው ልደት ለርሱ ብቻ በርሱ ያለ ነው ፤ ኋላ ሰው የሆነበት ልደት ግን ስለ እኛ ተደረገ ፤ አምላክ እንደመሆኑ ታምራትን አደረ ፤ ሰውም እንደመሆኑ ከባሕርዩ ሳይለወጥ ወዶ ሕማምን ገንዘብ አደረገ ፤ ከባሕርዩ ሳይለወጥ ሰው ሆኖዋልና።
በቸርነቱ ሰው ሆነ ነፍስን ሥጋን ነሥቶ ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ ፤ በእውነት የአዳም ልጅ ተባለ ፤ መርቶ ወደ ቅዱስ አባቱ የሚያደርስ የእውነት ጐዳና ነው ፤ ተድላ ነፍስ ወዳለበት የሚያገባ በር ነው። [መዝ.፹፭፥(፹፬)፥፯-፲፫ ዮሐ.፫፥፲፫ ፣ ፲፬፥፮]
የጠፋውን በግ የሚሻ ጠባቂ እርሱ ነው ፥ ስለ ዓለሙ ሁሉ የተሠዋ ዓለሙን ሁሉ ከኃጢአት ያነፃ በግ እርሱ ነው። [ኢሳ.፵፥፲፩ ። ፶፫፥፯ ። ማቴ.፲፰፥፲፪-፲፬ ። ዮሐ.፩፥፳፱ ። ፲-፲፩-፲፮]
ሰው ሆኖ የሠራውን ሥራ በምን ምሳሌ እንመስለዋለን ? መለኮቱ መለወጥ የሌለበት ነው ፤ በባሕርዩ አምላክ ነው ፤ ሰው በሆነበትም ግብር ሊቀ ካህናት ነው። [ዕብ.፬፥፲፬ ። ግብ.ሐዋ.፲፯፥፳፬-፴፪]
ከእኛ በሚለይበት ልደት እናት የለውም። የእኛን በሚመስለው ልደትም አባት የለውም። በፊትም በኋላም የሆነውን ልደቱን ሊናገር የሚችል ማንም የለም።
በሰማይም በምድርም የሌለበት አይነገርም ፤ አይመረመርም ፤ በቦታው ሁሉ ምሉ ነው። ሞት እንዳይሠለጥንባቸው ስለእነርሱ ነፍስን ሥጋን ልቡናን ነሣ። ❞
[ ቅዱስ ኤራቅሊስ ]
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
† † †
💖 🕊 💖
