ch
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

前往频道在 Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

显示更多
3 309
订阅者
-224 小时
-97
-3630
帖子存档
#መድሎተ_ጽድቅ ቅጽ ፫ [የእውነት_ሚዛን] #በመምህረ መምህራን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተሰናዳው ይኽ በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው መድሎተ ጽድቅ ቅጽ ፫ ታትሟል የመምህራችንን የአገልግሎት ዘመን ይባ
#መድሎተ_ጽድቅ ቅጽ ፫ [የእውነት_ሚዛን] #በመምህረ መምህራን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተሰናዳው ይኽ በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው መድሎተ ጽድቅ ቅጽ ፫ ታትሟል የመምህራችንን የአገልግሎት ዘመን ይባርክ፤ ያርዝምልንም ከክታብም አያናውጽብን፤እያልን....እነኾ በግዮን ደግሞ እንደተለመደው በልዩ ቅናሽ ተዘጋጅቷል...!

#በመምህር አቤል ካሳሁን ✨በቅርብ ቀን 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913
#በመምህር አቤል ካሳሁን ✨በቅርብ ቀን 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

✨ ዜና መጽሐፍ 📖"ቃለ አብ ሕያው"📖 #እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ዓለምን ያዳነበት ጥበቡ ድንቅ ነው፡፡ አዳም በተስፋ ይጠብቀው የነበረው እግዚአብሔር ቃል ሥጋ የኾነበት መንገድ
✨ ዜና መጽሐፍ 📖"ቃለ አብ ሕያው"📖 #እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ዓለምን ያዳነበት ጥበቡ ድንቅ ነው፡፡ አዳም በተስፋ ይጠብቀው የነበረው እግዚአብሔር ቃል ሥጋ የኾነበት መንገድ ለዲያብሎስ እና ለሠራዊቱ ኅቡዕ ቢሆንም ነቢያት ግን ሱባኤ እየቆጠሩ ጠብቀውታል። እግዚአብሔርም ይህን ዓለም ለማዳን በሥጋ ማርያም ተገለጠ። መላእክትም ከላይ በአርያም ሳይጎድል ከታች በምድርም ሳይጨመር የእግዚአብሔርን በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተወስኖ መገለጡ ድንቅ ነገር ስለሆነባቸው "ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ሥምረቱ ለሰብእ' ብለው ከእረኞች ጋር የተባበረን ምስጋና አቀረቡ። ይህን ድንቅ ምስጢረ ሥጋዌን በሚገባ ለማስረዳት ነገረ ማርያምን እና ነገረ ክርስቶስን በጥልቀት መመርመር ይገባል። ከልዩ ልዩ መጻሕፍት በማሰባሰብ ረቂቁን የሥጋዌ ምስጢር ለማስረዳት መምህር ሠናይ ጊዜ ይህን "ቃለ አብ ሕያው" የሚል ድንቅ መጽሐፍ አበርክተውልናልና እንጠቀምበት፡፡ #ዲያቆን መልካሙ በየነ #ይነበብ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

‹‹ሰኔ 30›› በዚህች ቀን የጌታን መንገድ ጠራጊው ፤ሐዋርያው ፤መጥምቁ ፤መምህሩ ፤ነብዩ ሰማዕቱ ቅዱስ ዮሐንስ የልደት ቀኑ ነው። ጨካኝ ሄሮድስ የቤቴልሔም ህጻናትን ሲጨፈጭፍ መጥምቁ ዮሐንስ ከአናቱ
‹‹ሰኔ 30›› በዚህች ቀን የጌታን መንገድ ጠራጊው ፤ሐዋርያው ፤መጥምቁ ፤መምህሩ ፤ነብዩ ሰማዕቱ ቅዱስ ዮሐንስ የልደት ቀኑ ነው። ጨካኝ ሄሮድስ የቤቴልሔም ህጻናትን ሲጨፈጭፍ መጥምቁ ዮሐንስ ከአናቱ ከቅድስት ኤልሳቤጥ ጋር ወደ ሲና በርሃ ተሰደደ። ኤልሳቤጥ በጣም አርጅታ ነበር ያን በርሃ ታዲያ እንዴት ቻለችው ያውም ልጅ አዝላ ልጅ ተሸክማ ረዳት ሳይኖራት ብቻዋን፤አባቱ ዘካርያስ በምኩራብ በመሰዊያው ፊት ልጅህን አምጣ ብለው አንገቱን ቆርጠው ገደሉት። ኤልሳቤጥም ሲና በርሃ ላይ ሞተች ህጻኑ ዮሐንስ ብቻውን ቀረ፤ የእናቱን በድነ ስጋ አቅፎ አለቀሰ፤ሁሉን ቻይ ሁሉን የሚያይ፤ ሁሉን የሚመረምር ጌታችን መድኀኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ለእመቤታችን እናቴ ሆይ ዘመድሽ ኤልሳቤጥ በበርሃ አርፋለች እንቀብራት ዘንድ እንሂድ አላት ደመና ጠቅሰው ዮሴፍና ሰሎሜን አስከትለው ሄደዋል ገንዘውም ቀብረዋታል። ከዚህ በኃላ እመቤታችን ልጄ ወዳጄ ሆይ ዮሐንስን ይዘነው እንሂድ አለችው የለም እናቴ ፤እርሱ እዚው ይቆያል መንገዴን ጠራጊ ነው፤ ኑሮው በዚሁ በርሃ ነው፤ጊዜው ሲደርስ ወደ ዮርዳኖስ ይመጣል ያጠምቀኝማል ያኔ አንድነቴ ሶስትነቴ ይገለጣል አላት፤ ትተውት ተመለሱ። ከመሞቱ በፊት እናቱ ያሰፋችለትን የግመል ቆዳ አገልድሞ አንቦጣ የሚባል ቅጠልና የበርሃ ማር እየበላ በበርሃ ኖረ 30 ዓመት ከ 6 ወር ሲሆነው፤ “የጌታን መንገድ አዘጋጁ ጥርጊያውንም አቅኑ” እያለ ከበርሃ ወጣ ሉቃ 3፤3። የመጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ምልጃና በረከት ይደርብን

❝አዎን አቤቱ አምላካችን አንተን ደስ ከማያሰኝኽ ሐሳብ እንለይ ዘንድ መለየቱን ስጠን....🙏❞ [ቅዳሴ እግዚእ] መልካም ዕለተ ሰንበት ወበዓለእገዚአብሔር ወልድ!
❝አዎን አቤቱ አምላካችን አንተን ደስ ከማያሰኝኽ ሐሳብ  እንለይ ዘንድ መለየቱን ስጠን....🙏❞ [ቅዳሴ እግዚእ] መልካም ዕለተ ሰንበት ወበዓለእገዚአብሔር ወልድ!

#አንቺ_ሴት፦ እንደ አስቴር ለእውነት ለመቆም ደፋርና ጀግና እንደ ሩት ለግንኙነቶችሽ ሁሉ ታማኝ እንደ ሊዲያ በርሽ ክፍት፣ እጅሽ ለጋስ እንደ ሐና ያለማቋረጥ የምትጸልይ እንደ ማርያም ታዛዥና ትሁት
#አንቺ_ሴት፦ እንደ አስቴር ለእውነት ለመቆም ደፋርና ጀግና እንደ ሩት ለግንኙነቶችሽ ሁሉ ታማኝ እንደ ሊዲያ በርሽ ክፍት፣ እጅሽ ለጋስ እንደ ሐና ያለማቋረጥ የምትጸልይ እንደ ማርያም ታዛዥና ትሁት እንደ ዶርቃ የሰዎች የፈገግታ ምንጭ እንደ አቢጋኤል ብልህና ለውሳኔዎቿ ጠንቃቃ ሁኚ!! #ትምህርተ_ሺኖዳ መጽሐፍ #አቡነ_ሺኖዳ_መልስ_አላቸው መጽሐፍ

📖ነፍሴ የወደደችውን አያችሁን?📖 ....✍️"እስቲ የሰው ነፍስን እንመልከታት፡፡ የሰው ነፍስ በኃጢአት ውስጥ በሆነች ጊዜ ጥቁር ነፍስ ናት፤በሰዎች ዓይን ፊት ጥቁር ነፍስ ናት፡፡ ከኃጢአት ሁሉ በ
📖ነፍሴ የወደደችውን አያችሁን?📖 ....✍️"እስቲ የሰው ነፍስን እንመልከታት፡፡ የሰው ነፍስ በኃጢአት ውስጥ በሆነች ጊዜ ጥቁር ነፍስ ናት፤በሰዎች ዓይን ፊት ጥቁር ነፍስ ናት፡፡ ከኃጢአት ሁሉ በሚያነጻው #በኢየሱስ_ክርስቶስ ደም ፊት ግን ውብ ናት፡፡ እርሷ ያለችው አሁን ጥቁር ነኝ፤በኋላ ግን ውብ እሆናለሁ ነው፡፡ በኃጢአት ውስጥ ስሆን እኔ ጥቁር ነኝ፤በንስሓ ውስጥ ስሆን ግን ውብ ነኝ፡፡" #ይነበብ! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

"ተክለሃይማኖት" ማለት ‹‹ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ›› ማለት ነው፡፡ ውልደታቸው በቡልጋ ደብረ ጽላሎሽ ነው። አባታቸው ቅዱስ ጸጋ ዘአብ፤ እናታቸው እግዚእ ኀርያ ይባላሉ። ቅዱሳ
"ተክለሃይማኖት" ማለት ‹‹ተክለ አብ፣ ተክለ ወልድ፣ ተክለ መንፈስ ቅዱስ›› ማለት ነው፡፡
ውልደታቸው በቡልጋ ደብረ ጽላሎሽ ነው። አባታቸው ቅዱስ ጸጋ ዘአብ፤ እናታቸው እግዚእ ኀርያ ይባላሉ።   ቅዱሳን ከሆኑት ጸጋ ዘአብ እና እግዚእ ኃርያ ቅዱስ ጋብቻ አቡነ ተክለ ሐይማኖት መጋቢት 29 ተፀንሰው ታህሳስ 24 ተወለዱ። በወላጆቻቸው  ፍስሐ ጽዮን ተብለው ነበር የተሰየሙት፤ትርጓሜውም የጽዮን ደስታ፣ ተድላ ማለት ነው፤ ኋላ ነው ተክለሀሃይማኖት የተባሉት። አባታችን ጻድቁ ተክለሃይማኖት ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋር ሃያ አምስተኛ ሆነው የእግዚአብሔርን መንበር አሐዱ አብ ቅዱስ፣አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ ብለው አጥነዋል። የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ምልጃና ጸሎት አይለየን። 23/10/2017 ዓ.ም!

ስለ እርሱ አንብቡ "እግዚአብሔር በአሳባችሁ ውስጥ እንዲኖር ስለ እርሱ አብዝታችሁ "አንብቡ ። እርሱን ለማወቅ ስለ እርሱ "አንብቡ ። እርሱን ካላወቃችሁት እንዴት እርሱን ልትወዱት ትችላላችሁ ? ስለ
ስለ እርሱ አንብቡ "እግዚአብሔር በአሳባችሁ ውስጥ እንዲኖር ስለ እርሱ አብዝታችሁ "አንብቡ ። እርሱን ለማወቅ ስለ እርሱ "አንብቡ ። እርሱን ካላወቃችሁት እንዴት እርሱን ልትወዱት ትችላላችሁ ? ስለ እርሱ "አንብቡ ስታነቡ ግን በሳይንሳዊ ወይም በፍልስፍና ጠባይ አታንብቡ ወይም ደግሞ ስለ እርሱ ጥናታዊ ጽሑፍ ወይም ትምህርት ለመስጠት አታንብቡ ። ነገር ግን ወደ እርሱ ጥልቀት ለመግባት ወይም እርሱ ወደ እናንተ ጥልቀት እንዲገባ "አንብቡ። ለነፍሳችሁ ውድ የሆኑትን የእርሱን ባሕርያት ለማወቅ ስትሉ "አንብቡ ይህ እውቀት አሳባችሁ ከእርሱ ጋር እንዲጣበቅና ፍቅሩ ከእናንተ ልብ ጋር እንዲቀናጅ ያደርግላችኋልና ። ስለ ስምምነቱ ስትሉም "አንብቡ ። ከወደዱት ሰዎች ጋር ስላለው ግንኙነት በጠላቶቹ ላይ ስላለው አቋም ስትሉ "አንብቡ ! "እግዚአብሔር ቸር እንደ ሆነ ቀምሳችሁ ታዩ ዘንድ ስለ እርሱ "አንብቡ ። ታዲያ ንባባችሁ ለልባችሁ ምግብ እንዲሆን እንጂ እንዲሁ ተራ ንባብ እንዲሆን አትፍቀዱ ። ስለ እግዚአብሔር ብዙ ካነበባችሁ በእርሱ ዘንድ ያለውን ፍጹምነት በሙሉ ታገኛላችሁ ። ከወደዳችሁት ስለ እርሱ ማንበባችሁን ትቀጥላላችሁ ። እግዚአብሔር ስለ እርሱ የሚያነቡትን ስለ እርሱ ዜና የሚጠይቁትን ከእርሱ ታሪኮች መካከል አንዱን ለማወቅ የሚናፍቁትንና እርሱን የሚያደንቁትን ሰዎች ይወዳቸዋል ። ስለ እርሱ ከመጽሐፍ ቅዱስ ወይም ከአባቶች ብሒሎች ወይም ከቤተክርስቲያንና ከቅዱሳን ታሪክ ልታነቡ ትችላላችሁ ። በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ የእግዚአብሔር እጅ ለመዳሰስ ስትሞክሩ በጥበቡ በኃይሉና በርኅራኄው ውስጥ እንደምትወዱት ታውቃላችሁ ። - አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ

📖#ትምህርት_በእንተ_ምክንያተ_ሐውልታት📖 .....ገብረ እግዚአብሔር ኪደን የማመሰግነው ይህን ሊቅ በራሳችን ቋንቋና ዘይቤ ዳግም እንዳውቀው ስላደረገኝ ነው፡፡ የትርጓሜው ወደረኛ ቋንቋና ውበት ሊቁ
📖#ትምህርት_በእንተ_ምክንያተ_ሐውልታት📖 .....ገብረ እግዚአብሔር ኪደን የማመሰግነው ይህን ሊቅ በራሳችን ቋንቋና ዘይቤ ዳግም እንዳውቀው ስላደረገኝ ነው፡፡ የትርጓሜው ወደረኛ ቋንቋና ውበት ሊቁን የራሳችን ትውፊትና የሕይወት ዘይቤ አካል አድርገን እንድንቈጥር ይጠቁመናል ሳይኾን ያስገድደናል፤ እኔ ተገድጄበታለሁ! ➮ይህን መጽሐፍ አንብቦ ትውፊቱን ከጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ትውፊት ለማነጻጸር፣ ሕይወቱን፣ ነባራዊውን የአገራችንን አኗኗር፣ የአገሩን ካህናት አገራዊ ሚና፣ ክርስቲያናዊ ምግባሩን ... ለመፈተሸ የማይገደድ አንባቢ ካለ ከሸንጎ ፊት ያቅርበኝ!በማለት የመጽሐፉን ግሩምነት የመሰከሩት #ደብተራና የሕግ ባለሞያ የኾኑት በአማን ነጸረ እኛም አንብበን ተጠቃሚዎች እነኾን ዘንድ ብሎም ራሳችንን እንድንፈትሽበት ያሳሰቡ ሲኾን #በግዮን_መጻሕፍት ደግሞ በልዩ ቅናሽ የተዘጋጀ ሲሆን ግዜ ሳንሰጥ መጽፏን ገዝተን ብንመገባት መልካም ነው እንላለን! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን  በDHL ,በEMS እንዲሁም የ delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። 📱ይደውሉልን ፦0913083816 Telegram https://t.me/GhionBookStore1623

#ሕንጸተ_ቤተ ክርስቲያን ዘእግዝእትነ ማርያም። #ሰኔ_21 .... ✍#ጌታችን በዐረገ በስምንተኛው ዓመት ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ወደ ፊልጵስዩስ ገብተው በክርስቶስ ስም አሳምነው ብዙ አሕዛብን
#ሕንጸተ_ቤተ ክርስቲያን ዘእግዝእትነ ማርያም። #ሰኔ_21 .... ✍#ጌታችን በዐረገ በስምንተኛው ዓመት ቅዱስ ጳውሎስና ቅዱስ በርናባስ ወደ ፊልጵስዩስ ገብተው በክርስቶስ ስም አሳምነው ብዙ አሕዛብን ካጠመቁ በኋላ ቤተ ክርስቲያን ሊሠሩላቸው ወደዱ፡፡ በዚህ ጊዜ ርእሰ ሐዋርያት እያለ እኛ መሥራት አይገባንም ብለው በሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስ መልእክት ላኩበት፡፡ እርሱም ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር መጥቶ ከቅዱስ ጳውሎስ እና ቅዱስ በርናባስ ጋር በኢየሩሳሌም ተገናከጽንት በዚያም በአንድነት ሱባዔ ይዘው ከቆዩ በኋላ ጌታችን የሞቱትን አስነሥቶ፣ ያሉትንም ጠርቶ ቅዱሳን ሐዋርያትን #በፊልጵስዩስ አገር ሰብስቦ ‹‹በእናቴ በድንግል ማርያም ስም ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚሠራዉን የአብያተ ክርስቲያናት ሥራ ላሳያችሁ፤ ሥርዓቱንም ላስተምራችሁ ሰብስቤአችኋለሁ›› ብሎ ወደ ምሥራቅ ይዟቸው ወጣ፡፡ #በዚያም_ሥፍራ የነበሩትን ሦስት ድንጋዮችንም የተራራቁትን አቀራርቦ፣ ጥቃቅኑን ታላላቅ አድርጎ ቁመቱን በ፳፬፤ ወርዱን በ፲፪ ክንድ ለክቶ ለቅዱሳን ሐዋርያት ሰጣቸው፡፡   ከዚህ በኋላ ቅዱሳን ሐዋርያት ሰም እሳት ሲያገኘው እንዲለመልም፣ ድንጋዩ በእጃቸው ላይ እየተሳበላቸው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን ሠርተው ፈጽመዉታል፡፡ #ሕንጻ_ቤተ_ክርስቲያኑ የተሠራዉም ጌታችን በዐረገ በ፲፱ኛው ፤ እመቤታችን በዐረገች በ፬ኛው ዓመት ሰኔ ፳ ቀን ሲኾን፣ በ፳፩ኛው ቀን (በማግሥቱ) ኅብስት ሰማያዊ፣ ጽዋዕ ሰማያዊ ወደ ቤተ ክርስቲያኑ ወረደ፡፡ ጌታችንም ከእመቤታችን ጋር ከሰማየ ሰማያት መጥቶ እመቤታችንን ታቦት፤ ሐዋርያትን ልዑካን አድርጎ፣ እርሱ ሠራዒ ካህን ኾኖ ቀድሶ ካቈረባቸው በኋላ “ከዛሬ ጀምሮ እናንተም እንደዚህ አድርጉ “ ብሎ አዝዟቸው በክብር በምስጋና ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡ [መጽሐፈ ስንክሳር] #እንኳን አደረሰን🙏🙏

📚📚📚 📖#የበረሃው_ምሥጢር 📖#ገድለ_ምንኩስና ውድ '#ግዮናውያን' እነዚህ ኹለት ተወዳጅ መጻሕፍት ስጠይቁን የነበራችኹ ውስን ፍሬዎች ብቻ አግኝተናል እንዳያልቅባችኹ....! 📚ግዮን መጻሕፍት
+1
📚📚📚   📖#የበረሃው_ምሥጢር 📖#ገድለ_ምንኩስና ውድ '#ግዮናውያን'  እነዚህ ኹለት ተወዳጅ መጻሕፍት ስጠይቁን የነበራችኹ ውስን ፍሬዎች ብቻ አግኝተናል እንዳያልቅባችኹ....! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

" ስለ እኛ የሚማልደው ....." 👉 " ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ " ምን ማለት ነው? 👉 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሮሜ 8፥34ን ምን ብሎ ተረጎመው 👉 "መካከለኛ" የተባለበት ምክኒያት 👉 የቅዱሳን አማላጅነት ትምህርት የኢየሱስ ክርስቶስን መካከለኛነት ይቃወማል/ይጋፋል ? +++++++++++++~~~++++++++++ ታዲያ እንዲህ ከአብ ጋር በከሃሊነትና በሥልጣን አንድ የሆነ እርሱ እኛን ለመርዳት ማላጅ መሆን እንዴት ያስፈልገዋል? እንዴት እርሱ አማላጅ ይሆናል? እንዴት ይማልዳል ይባላል? የተፈረደባቸውንና የተኮነኑትን ነጻ ያወጣቸውና ያዳናቸው እርሱ፣ ከሞት ፍርድና ከኩነኔ ነጻ ያወጣና ያዳነ እርሱ፣ ጻድቃንና ልጆች ያደረጋቸው እና እጅግ ከፍ ወዳለ ክብር ያወጣቸው እርሱ፣ ይህን ሁሉ ከፈጸመና ካከናወነ በኋላ፣ ባሕርያችንን በየማነ አብ በዘባነ ኪሩብ ካስቀመጠው በኋላ፣ በጣም ቀላል ስለሆኑት ነገሮች ማላጅ መሆን እንዴት ያስፈልገዋል? ሲዖልን በሥልጣኑ የበዘበዘ፣ ሞትን በኃይሉ የሻረ፣ ልጅነትንና ትንሣኤን የሰጠ፣ ባሕርያችንን ከራሱ ባሕርይ ጋር አዋሕዶ በሰማያት በንጉሡ ዙፋን ላይ ያስቀመጠው እርሱ፣ ስለ ጥቃቅን ነገሮች ለምን ለማኝ ማላጅ ይሆናል? (ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፣ ትርጓሜ መልእክተ ሮሜ) #መድሎተ_ጽድቅ #ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ

📖ሥርዓተ ቅዳሴና ሚስጥራዊ ማብራሪያው📖 ......#በቅዳሴ ጊዜ የሚስቅ የሚሳለቅ ቢኖር ካህን ቢሆን ተቀብሎ ውጥቶ አንድ ሱባኤ (ሰባት)ቀን ይጹም ይስገድ ሕዝባዊ ቢሆን ግን ሳይቀበል ፈጥኖ ሊወጣ
📖ሥርዓተ ቅዳሴና ሚስጥራዊ ማብራሪያው📖 ......#በቅዳሴ ጊዜ የሚስቅ የሚሳለቅ ቢኖር ካህን ቢሆን ተቀብሎ ውጥቶ አንድ ሱባኤ (ሰባት)ቀን ይጹም ይስገድ ሕዝባዊ ቢሆን ግን ሳይቀበል ፈጥኖ ሊወጣ ይገባል። **ካህኑ ተቀብሎ ይውጣ የተባለ አብነት ስለሆነ ቅዳሴውን ንቆት ወጣ ብለው ምእመናን እንዳይሰናከሉ እንዳይጠራጠሩ ነው። ሕዝባዊ ግን የወጣበትን ምስጢር ስለሚያውቁ ወጥቶ ሲሄድ እገሌ ቢስቅ ቢሳለቅ ቢናገር አስወጥተው ሰደዱት እኛንም እንደሱ አስወጥተው ይሰዱናል ብለው መቀጣጫ ያደርጉታልና ስለዚህ ነው። #ይህ ሥርዓተ ቅዳሴና ሚስጥራዊ ማብራሪያው የተሰኘው ግሩም መጽሐፍ በመደብራችን በልዩ ቅናሽ ያገኙታል። 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

እመቤቴ ሆይ “መብረቅ ሲጮህ ሰው ሁሉ እንደሚደነግጥ የአንቺን ስም ሲሰማ ዲያቢሎስ ይደነግጣል አንቺ ከተወለድሽ ጀምሮ እረፍት አላገኘምና ነው፤ በአንቺ ታመመ፤ በልጅሽ መስቀል ተሰቃየ፤ ስለሆነም ከፍጥ
እመቤቴ ሆይ “መብረቅ ሲጮህ ሰው ሁሉ እንደሚደነግጥ የአንቺን ስም ሲሰማ ዲያቢሎስ ይደነግጣል አንቺ ከተወለድሽ ጀምሮ እረፍት አላገኘምና ነው፤ በአንቺ ታመመ፤ በልጅሽ መስቀል ተሰቃየ፤ ስለሆነም ከፍጥረት ሁሉ አንቺን ይጠላል”    ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ https://t.me/GhionBookStore1623

📖#ኃጢኣቷን_የቀበረችው_ማርያም📖 .....ማርያም ኀጥእት ማናት? በማቴዎስ ወንጌል ስለ ጌታችን ሽቱ መቀባት የተመዘገበውን የታሪክ ክፍል መነሻ በማድረግ በጊዜ ቅደም ተከተል ሽቱ የተቀባበትን መቼት
📖#ኃጢኣቷን_የቀበረችው_ማርያም📖 .....ማርያም ኀጥእት ማናት? በማቴዎስ ወንጌል ስለ ጌታችን ሽቱ መቀባት የተመዘገበውን የታሪክ ክፍል መነሻ በማድረግ በጊዜ ቅደም ተከተል ሽቱ የተቀባበትን መቼት አብራርቶ የነገረን ቅዱስ ቄርሎስ፡ ማርያም ኀጥእት፡ ኹለተኛ ሽቱ የቀባችበትን ዕለት ሐሙስ ጌታችን ረቡዕ ምሽት ስለተቀባ፡ዕለቱን ሐሙስ ብሎታል] ከማለቱ በቀር በዮሐንስ ወንጌል የግእዝና አማርኛ ትርጓሜ ላይ...... #ከውስጥ ገጽ የተቆረሰ #የተወሰነ_ቅጂ_ቀርቷል_እንዳያመልጥዎ...! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623

✨#ቅዱስ_ሚካኤል_፭ት_ነገሮችን_የፈጸመበት_እለት_ነው! እነርሱም... ፠፩. በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል፤ ፠፪. ባሕራንን ያዳነበት፤ ፠፫. የአስተራኒቆስ ሚስት ቅድስት አፎምያን ያዳነበት፤ በዓለ እረ
+1
#ቅዱስ_ሚካኤል_፭ት_ነገሮችን_የፈጸመበት_እለት_ነው!  እነርሱም...    ፠፩. በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል፤ ፠፪. ባሕራንን ያዳነበት፤ ፠፫. የአስተራኒቆስ ሚስት ቅድስት አፎምያን ያዳነበት፤ በዓለ እረፍቷም በዚሁ እለት ነው፤ ፠፬. በግብፅ ሃገር ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረበት፤ ፠፭. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ነጥቆ ወስዶ ያሳየበት፤
ት.ዳንኤል 12 ¹ በዚያም ዘመን ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤ ሕዝብም ከሆነ ጀምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል፤ በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል።
            #እንኳን_አደረሳችሁ !🙏  

💧#ዜና-መጽሐፍ 📖#ሄርማ_ኖላዊ📖 ➮#በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ረፋዱ ላይ ሄርማ በተባለ ሰው የተጻፈ ሄርማ ኖላዊ" የተሰኘው መጽሐፍ በየአገራቱ ለንባብ ይዘዋወር ነበር። ይህም መጽሐፍ
💧#ዜና-መጽሐፍ 📖#ሄርማ_ኖላዊ📖 ➮#በሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ረፋዱ ላይ ሄርማ በተባለ ሰው የተጻፈ ሄርማ ኖላዊ" የተሰኘው መጽሐፍ በየአገራቱ ለንባብ ይዘዋወር ነበር። ይህም መጽሐፍ በአንዳንድ አብያተ ክርስቲያን ዘንድ በጉባኤ ወይም በህዝብ አገልግሎት ጊዜ የሚነበብ እና ልክ የሐዲስ ኪዳን የቀኖና መጻሕፍትን ያህል ተቀባይነት ነበረው። ✨#በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው ይህ በ#መጋቤ ምስጢር ያሬድ ዘርአ-ቡሩክ የቅኔና የመጻሕፍት ትርጓሜ መምህር የተዘጋጀውን "ሄርማ ኖላዊ" እነኾ..! 📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲሁም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍት ተደራሽ እናደርጋለን። ይደውሉልን !📞፦0913083816 https://t.me/GhionBookStore1623