ch
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

前往频道在 Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

显示更多
3 291
订阅者
+224 小时
+127
+10030
帖子存档
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የሴቶች አገልግሎት መምሪያ የመሪዎችና አገልጋዮች ሥልጠና በሆሳህና ከተማ አካሂዷል። ጎጂ ባህላዊ ልምምዶችን እና ህገወጥ የሰው ልጅ ዝውውርን መከለካል ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለሲኖዶስ አመራሮች እና ከተለያዩ ሰበካዎች ለተወጣጡ አገልጋዮች ከታህሳስ 9-10, 2018 ዓ.ም በሆናህና ከተማ ተሰጥቷል። በስልጠናው ሶስት የሥራ ዘርፎች የተካፈሉ ሲሆን የሲኖዶሱን ጽሕፈት ቤት በሆሳህና ከተማ ያደረገው ማዕከላዊ ደቡብ ሲኖዶስ፣ አርባ ምንጭ እና ምዕራብ ጊቤ ሲኖዶሶች ተካፍሏል። ስልጠናውም ጎጂ ባህላዊ ድርጊቶችን እና በከፍተኛ ደረጃ እየተስተዋለ የሚገኘውን ህገወጥ የሰዎች ሀገር አቀፍ እና አለም አቀፍ ዝውውሮችን ምዕመናን መከላከል እንዲችሉ በአገልጋዮቻቸው በኩል ግንዛቤን የማስጨበጥ አላማ ያደረገ ሥልጠና መሆኑን የመምሪያው ዳይሬክተር ቄስ ታገሰች ዳኘው ገልጸዋል።

የ"ድንቅ መካር" የመዝሙር አልበም ምርቃት ጥሪ በልዩ የዝማሬ አገልግሎቱ የምናውቀው የኮተቤ መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን አገልጋይ የሆነው ዘማሪ ታማኝ ሙሉነህ ከሁለት አመት በላይ በዝግጅት ላይ የነበረውን ሁለተኛ ቁጥር አልበሙን ያስመርቃል። "ድንቅ መካር" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው አልበም በውስጡ 13 ዝማሬዎችን የያዘ ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን አባላት እና መላው የወንጌል አማኞች በተጋበዙበት መርሃ ግብር የፊታችን ቅዳሜ ታህሳስ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ጀምሮ በኋልዎት አማኑኤል አጥቢያ የአምልኮ አዳራሽ በድምቀት ይመረቃል። ሙሉ ሥነ-ሥርዓቱም በተለያዩ የሚድያ አማራጮ በቀጥታ ሥርጭት የሚተላለፍ መሆኑን ዘማሪው አስታውቋል።

በ21ኛው የቤተ ክርስቲያኒቱ ካውንስል ለተመረጡ የሥራ መሪዎች ኦፊሴላዊ የአገልግሎት ስምሪት ተሰጠ። * * * * * * * ለመጪው ዓራት የአገልግሎት አመታት ቤተ ክርስቲያኒቱን የወንጌል ተልዕኮ እና ቲኦሎጂ መምሪያ ዳይሬክተር በመሆን እንዲያገለግሉ ለተመረጡት ቄስ ጥላዬ ከበደ እና የአስተዳደርና ፋይናንስ ዳይሬክተር እንዲሆኑ ለተመረጡት ወ/ሮ ሰብለ ገመችስ በቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የአገልግሎት ስምሪት ተሰጥቷቸዋል። የሥምሪቱም ሥነ ሥርዓት በኮተቤ መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን ዛሬ ታህሣሥ 19 ቀን 2018 ዓ.ም በዕሁድ የማለዳ ፕሮግራም ላይ የተካሄደ ሲሆን የማህበሯ ምዕመናን፣ አገልጋዮች፣ ሥምሪቱን የተቀበሉ አገልጋዮች ቤተሰቦችና ወዳጅ ዘመዶች ተገኝተዋል። ከመጪውም ሳምንት ጀምሮ አገልጋዮቹ ቤተ ክርስቲያኒቱ በሰጠቻቸቸው የሥራ መደቦች በአገልግሎት ስፍራቸው ላይ በመገኘት ተሰማርተው በሙሉ ስልጣን አገልግሎቶቻቸው ማከናወን የሚጀምሩ ይሆናል። አገሎጋዮቹም በሥርዓተ ሥምሪታቸው ወቅት በእግዚአብሔር እና በምዕመናን ፊት በገቡት ቃለ መሃላ መሠረት ትጉና ታማኝ አገልጋዮች ይሆኑ ዘንድ ቤተ ክርስቲያን በፀሎት ታስባቸዋለች። መልካም የአገልግሎት ዘመን።

#የኢትዮጵያ_ወንጌላዊት_ቤተ_ክርስቲያን_መካነ_ኢየሱስ_ለ54_አገልጋዮች_የቅስና_ሀላፊነት_ሰጠች። * * * * * * * የቤተ ክርስቲያኒቱን የቃል እና ቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎት እንዲያግዝ በማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ሲኖዶስ፣ በአዲስ አበባ ሲኖዶስ እና በፊንፊኔ ሀዋስ ሲኖዶስ ስም ለመደራጀት ጥያቄ ባቀረቡ ሰበኮች ለሚያገለግሉ አገልጋዮች የቅስና ሹመቱ ተሰጥቷል። ሲመተ ቅስናውም በቤተ ክርስቲያኒቱ ቀደምት በሆነው የአዲስ አበባ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማኀበረ ምዕመናን የተከናወነ ሲሆን የቅስና ሀላፊነቱ የመምሪያ ዳይሬክተሮች፣ የሲኖዶስ መሪዎች፣ የሰበካ ተጠሪዎች እና የእጩ ቀሳውስቱ ቤተሰቦች በተገኙበት ተካሂዷል። የቅስና ሀላፊነት የመስጠት ሥነ ሥርዓቱን ባካሄዱበት ወቅት ባስተላለፉት መልዕክ እጩ ቀሳውስቱ ወደየ ማኀበራነ ምዕመናቸው ሲመለሱ የቤተ ክርስቲያን ከፍተኛ ባለ ሥልጣን የሆነውን የእግዚአብሔር ቃል በንጽህና እና በስልጣን የሚሰበክበትን ምስባክ የመጠበቅ እና የማስጠበቅ ሀላፊነት እንዳለባቸው የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ አሳስበዋል። የእግዚአብሔር ቃል በሙሉ ስልጣን መሰበኩ ለቅዱሳት ሚስጥራቱ አገልግሎት ማለትም ለክርስቶስ ሥጋ እና ደም የሚሰጋጀን መግቢያ በር ስለሆነ ቀሳውስቱ በምስባኩ ላይ በእነርሱም ሆነ በሌሎች ስለ ሚቀርቡት ስብከተ ወንጌሎች ጥንቃቄ እንዲደርጉ እና በዚህም ረገድ ለመንጋው ልዩ ጥበቃ እንዲደረግ አክለውም አሳስበዋል። በቤተ ክርስቲያኒቱ የወንጌል ተልዕኮ አና ቲኦሎጂ መምሪያ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ባለፉት 8 የአገልግሎት ዓመታት በቤተ ክርስቲያኒቱ የቃል አና ቅዱሳት ሚስጥራት አገልግሎቶች በኩል የሚታየው ክፍተት ለመሙላት እና በፍጥነት እያደገ ለሚገኘውን የምዕመና ቁጥር ተከትሎ የሚቀርበውን የእረኝነት አገልግሎት ፍላጎቶች ምላሽ ለመስጠት በልዩ ትኩረት የበቁ አገልጋዮችን የማቀሰስ እና ወደ አገልግሎት የማሰማራቱ ስራ ውጤታማ በሆነ መልክ ተሰርቷል። በተገኙት ውጤቶችም እግዚአብሔርን እያመሰገንን ሥራው ግን ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ቤተ ክርስቲያንኒቱ ያላት የቄሶች ለምዕመናን ሥብጥር ስታትስቲካዊ መረጃዎች አሁንም ይጠቁማሉ። ለመስኩ አገልግሎት ሰራተኞች የሰጠን የአምላካች የእግዚአብሔር ስም የተመሰገነ ይሁን። ታኀሳስ 8 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ

#Ibsa_Gaddaa #የኅዘን_መግለጫ Tajaajila Waldaa Kiristiyaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesus Itiyoophiyaa keessatti seenaa guddaa abboota qaban keessaa tokko kan ta’an, abbaan keenya jaalatamoon obbo Dastaa Buubaa, dhibee isaan muudate irraa yaalamaa turanii guyyoota muraasa dura gara gooftaatti waamamuu isaanii gadda guddaadhaan dhageenyee jirra. Amantoonnii fi tajaajiltoonni Waldaa Makana Yesuus guutummaatti gadda isaanii dhageessisaa jiru. Jaallatamoo Obbo Dastaa Buubaa, Waldaa Kirisitiyaanaa Warra Wangeelaa Makaane Yesuus Itiyoophiyaa keessatti sadarkaa hoggansaa garagaraatiin tajaajiluu isaanii caalaatti, Wangeelaaf jecha gatii guddaa kan kaffalan, of kennuudhaan, gammachuu fi jaalalaan jireenya fakkeenya-qabeessa kan jiraatan, hojii gaarii isaaniitiin namoonni baayyeen kan isaan kabajan turan. Kana qofa utuu jireenyi Obbo Dastaa ofuma isaatiin mana barumsaati jechuun in danda’ama. Akka abbaattis akka hoogganaattis namoota danuu hojii Waaqayyo keessatti guddisaniiru. Keessumattuu, Sinoodoosii Giddugaleessaa bifa haaraadhaan ijaaruu fi qindeessuu akkasumas qixa inni ittiin saffisaan guddatu karoorsuun keessatti gaheen isaan taphatanii fi gatiin isaa kaffalan yeroo hundumaa yaadatamaa kan jiraatudha. Eenyummaa isaanii isa amantii fi jireenya gooftaa irratti ijaaramee namoota gara Kiristoositti hawwataa ture, isa yoomiyyuu hin dagatamneef Gooftaa in galateeffanna. Fooniin yoo nu irraa adda bahan iyyuu , hojii gaarii fi fakkeenyumman inni isaan Waldaa fi dhaloota kanaaf kaa’anii darban yeroo hundumaa seenaa ta’ee yaadatama. Maqaa gaarii qabaatanii darbanii jiru. Gooftaan Yesuus Kiristoos, ati hojjetaa amanamaa fi qajeelaa nana, gara mootummaa abbaa keetiitti gali jedhee isaan akka simate dhugaatti beekna. Waaqayyo isa nama jaallatamaa Kanaan Waldaa isaa eebbiseef galanin haa ta’u. Gaggeessitoonni fi amantootni Waldaa Kiristiyaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesus Itiyoophiyaa, maatii fi michoota abbaa keenya Obbo Dastaa Buubaa hundumaa Waaqayyo akka jajjabeessu kadhannaa keenya. ……..”Warri gooftaatti qabamanii utuu jiranii du’an, ammaa jalqabanii warra gammadaniidha…….”Eeyyee, dadhabbii isaanitti aara haa galfatan, ijji hojii isaanii immoo isaan duukaa in bu’a. (Mul’ata Yohannis 14:13) #የኅዘን_መግለጫ በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ሕይወትና አገልግሎት ሰፊ ታሪክ ካላቸው አገልጋዮች መካከል አንዱ የሆኑት እጅግ የተወደዱ አባት አቶ ደስታ ቡባ ባደረባቸው ሕመም ሲረዱ ቆይተው ከጥቂት ቀናት በፊት ወደ ጌታ የመሰባሰባቸውን ዜና በታላቅ ኀዘን ሰምተናል። አቶ ደስታ ቡባ በዚህች ቤተ ክርስቲያን በተለያዩ የአመራር ሃላፊነቶች ከማገልገላቸውም በላይ ለወንጌል ሲሉ ብዙ ዋጋ የከፈሉ፤ በብዙ መሰጠት፤ በደሰታና በፍቅር ምሳሌነት ያለውን ሕይወት የኖ፤ ለብዙዎች ዘንድ በመልካም ምግባራቸው የሚጠቀሱና የሚመሰገኑ አባት ነበሩ። በተለይም ማዕከላዊ ሲኖደስን በአዲስ መልክ በማደራጀትና በመምራት ረገድ የነበራቸው ድርሻና ለዚህም የከፈሉት ዋጋ ሁሉ ጊዜ በአድናቆት እየታወሰ የሚኖር ነው። በጌታ ስለነበራቸው እምነትና ሕይወት ምን ጊዜም ሊዘነጋ ስለማይችለው ልዩ ማንነታቸውና ምሉዕነታቸው ጌታን እናመሰግናለን። እርሳቸው በአካል ቢለዩንም ለቤተ ክርስቲያንና ለአሁኑ ትውልድ ትተው ያለፉት መልካም ተግባራቸውና ምሳሌነታቸው ሁልጊዜ እየታሰበና እየተዘከረ ይኖራል። በመልካም ስም ተሰናብተዋል፤ የትጉና ታማኝ ባሪያ ሽልማት ከጌታ ዘንድ እንደሚሆንላቸውም እምነታችን ጽኑ ነው፨ የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን አመራርና ምዕመናን በሙሉ ለአባታችን ለአቶ ደስታ ቡባ ቤተሰብና ቤተዘመድ እንዲሁም ለወዳጆቻቸው ሁሉ እግዚአብሔር መጽናናቱን እንዲያበዛ ጸሎታችን መሆኑን እንደገልጻለን። ከንግዲህ ወዲህ በጌታ የሚሞቱ ሙታን ብጹአን ናቸው---------ከድካማቸው ያርፉ ዘንድ፤ ስራቸውም ይከተላቸዋል (ራዕ 14፡13)