5killo Jem'a official Channel
前往频道在 Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
显示更多1 159
订阅者
-124 小时
无数据7 天
-130 天
帖子存档
📚✨ Applied Mathematics Tutorial is Back! ✨📚
Aselamu Aleykum Werahmetu'llahi Weberekatuh!
Alhamdulillah, after our semester break, the academic sector of 5k muslim jemea is excited to resume Applied Mathematics tutorial sessions! 🙌
🗓 Day: Wednesday
⏰ Time: 10:20 LT
📍 Location: To be announced
Let’s come together again to strengthen our understanding, support one another, and stay consistent in our learning. Don’t miss out — your حضور (presence) matters!
Bring your questions, notes, and positive energy☄️
See you all on Wednesday, inshaAllah!!
Let's grow together in deen and education!
📌 Don’t miss out!
📌 Invite your classmates too!
🔗 Join our Telegram channel for updates:
👉 t.me/fivekjemaa
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿مَا كَانَ الْفُحْشُ فِي شَيْءٍ إِلَّا شَانَهُ ، وَمَا كَانَ الْحَيَاءُ فِي شَيْءٍ إِلَّا زَانَهُ﴾
“ብልሹ የሆነ ፀያፍ ነገር በአንድ ነገር ውስጥ አይገባም፤ የሚያበላሸው ቢሆን እንጂ። ሐያአ እፍረት ማድረግ በአንድ ነገር ውስጥ አይኖርም ያሳመረው ቢሆን እንጂ።”
📚 ቲርሚዚ ሶሂህ ብለውታል፡ 1974
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች ለNBC ካስገቡት ደብዳቤ፦
"ሚዲያዎች ከተቋቋሙበት አላማ መካከል ለፍትሕ በመወገን በሕዝቦች ላይ የሚደርሱ በደሎችን በማጋለጥ ለተሻለ፣ እኩልነት እና ነፃነትን ለሚያሰፍን ከባቢ አስተዋፅዖ ማድረግ ነው።
መሠል የመብት ጥሰቶች ከሀገራችን አልፎ ለአፍሪካ አርዓያ በሆነ የልሕቀት ማዕከል ውስጥ መፈፀሙ አግባብነት የሌለውን ልማድ ከመፍጠሩም ባሻገር ይለወጥ ዘንድ እየተጋንለት ያለውን የትምህርት ስርዓት ስለሚጎዳው ሚዲያችሁ ተማሪዎች እየተፈፀመባቸው ስላለው የመብት ጥሰት እንዲያቀርቡ፤ የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌም በእርሳቸው አመራር እየተፈፀመ ስላለው የመብት ጥሰት ከተማሪዎች እየቀረበ ላለው አቤቱታ ቀርበው ምላሽ እንዲሰጡ በማድረግ ሀገራዊ ሀላፊነቱን ይወጣ ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን።"
ጥያቄ አለን __ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
وَحَدَّثَنِي عَنْ مَالِكٍ، عَنْ عَطَاءِ بْنِ أَبِي مُسْلِمٍ عَبْدِ اللَّهِ الْخُرَاسَانِيِّ، قَالَ قَالَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم " تَصَافَحُوا يَذْهَبِ الْغِلُّ وَتَهَادَوْا تَحَابُّوا وَتَذْهَبِ الشَّحْنَاءُ " .
Yahya related to me from Malik from Ata ibn Abi Muslim that Abdullah al-Khurasani said, "The Messenger of Allah, (ﷺ), said, 'Shake hands and rancour will disappear. Give presents to each other and love each other and enmity will disappear.' "
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዶክተር ሳሙኤል አመራር በወጣው መመሪያ ምክንያት እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በመገኘት ድምፃቸውን አሰሙ ! ! !
-------------------------------------------
መጋቢት 25 / 2018 ዓ.ል
-------------------------------------------
በአራዳ ክ/ከተማ ለሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት የብልፅግና እጩ ሆነው የቀረቡት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ሙስሊም ተማሪዎች እና ፍትሕ ፈላጊ ሁሉ ያወጡትን ጨቋኝ መመሪያ በማስተካከል የሰብዓዊ መብት ጥሰታቸውን እንዲያቆሙ ቢጠይቅም፤ ውይይት የጠየቀውን ተማሪያቸውን እንዲያወያይ ጥሪ ቢያቀርብም ምላሽ ሳይሰጥ እና መፍትሔ ሳይቀመጥ እስካሁን አለ።
ይህ በግልፅነት፣ ተጠያቂነት እና ፍትሐዊነት ሊመራ የሚገባውን ዩኒቨርስቲያችንን ስም የሚያጎድፍ ተግባር በመሆኑ ማስተካከያ ተደርጎ ሁሉም በመስመሩ ይሆን ዘንድ ለማስቻል ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በእንቅስቃሴ ላይ ናቸው። በዛሬው እለትም በአማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን በመገኘት የእርሳቸው አመራር እየፈፀመ ስላለው የመብት ጥሰት ድምፅ ይሆን ዘንድ ጠይቀዋል።
ጥያቄ አለን __ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
+3
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በኢትዮጵያ ፕሬስ ኤጀንሲ በመገኘት ድምፃቸውን አሰሙ ! ! !
-------------------------------------------
መጋቢት 25 / 2018 ዓ.ል
-------------------------------------------
ሀገር ብዝሐ ሀይማኖት ባሏቸው ዜጎች የምትሰራ፣ የምታድግ እና የምትለማ የጋራ ቤት ሲሆን የዜጎች ነፃነት፣ እኩልነት እና ፍትሕ የቤቱ ምሰሶ እና ማገር ናቸው። ነፃነት ሲገፈፍ አቤት በማለት፤ ፍትሕ ሲጣስ ድምፅ በመሆን ለጋራ ሀገር ማደግ አስተዋፅዖ ማድረግ ከምንም እና ከማንም በላይ በሀገር ሀብት የተገነቡ ተቋማት እና የዜጎች ላብ ደመወዛቸው የሆኑ መሪዎች ሀላፊነት ነው። ይህ ሆኖ ሲታይ የሁላችን የሆነችዋ ኢትዮጵያ ተስፋ ይለመልማል።
"ኒቃብ የለበሰች ሴት አትማርም!" - የሚልን መመሪያ አውጥቶ በቅኔ መልክ ሙስሊም ተማሪን ላስተምር አልችልም የሚልን መልዕክት በማስተላለፍ በጋራ ሀገር በጋራ ሀብት የተገነባን የጋራ ተቋም ስም እና ግብር እያበላሹ ያሉ አመራሮችን በመቃወም ሰብዓዊ መብታቸውን ለማስከበር ንቅናቄ የጀመሩት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሴቶች ቅፍለት ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ከትሞ ነበር። እዚያም እየደረሰባቸው ስላለው የመብት ጥሰት በመናገር ተቋሙ የደረሰውን በደል በማጋለጥ ሀገራዊ ሀላፊነቱን ይወጣ ዘንድ ጠይቀዋል።
ንቅናቄያችን ፍትሕ እስኪሰፍን ይቀጥላል። እንቅስቃሴያችን ሰብዓዊ መብታችንን የሚጥሰው መመሪያ እስኪሻሻል ይቀጥላል። ፍትሕ ቀባሪዎቿን ትቀብራለች።
ጥያቄ አለን __ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
+3
"ምንም በማናውቀው አስከሰሳችሁን። ሴኩሪቲዎች መጥተው አነጋግረውናል። ሲጀመር የእኛ ስራ ይሄ አይደለም። መብታችሁ ከተጣሰ ሌላ ቦታ ሂዱ።" - በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሰብዓዊ መብት ማዕከል
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴቶች በአደባባይ በለቀቀው ወረቀት ስለ ሰብዓዊ መብት እንደሚቆም ካስታወቀው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሰብዓዊ መብት ማዕከል በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት አቤት ለማለት ከሁለት ቀን በፊት ሄደው ነበር። በወቅቱ የነበሩት የማዕከሉ ሀላፊዎች ሙስሊም ተማሪዎች ላይ የደረሰው የሰብዓዊ መብት ጥሰት አግባብነት እንደሌለው በመግለፅ ይስተካከል ዘንድ እንደሚሰሩ በመግለፅ ከሁለት ቀን ቡሃላ ከጧቱ 4:00 ሰዓት ላይ እንደሚጡ እና ከበላይ ሀላፊዎች ጋር እንደሚገናኙ ገልፀውም ነበር። ሆኖም ይህ በሆነበት ሰዓት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጥበቃ ሀላፊዎች ከቦታው በመምጣት የተማሪዎችን ID ከመቀማት ጀምሮ እስከ 9:00 ሰዓት የደረሰ ማዋከብ ፈፅመውባቸው ነበር።
ሙስሊም ተማሪዎቹ ቀጠሮውን በማክበር በሰዓቱ የደወሉ እና ሊገኙ የሄዱ ቢሆንም የማዕከሉ ተወካይ "ምንም በማናውቀው አስከሰሳችሁን። ሴኩሪቲዎች መጥተው አነጋግረውናል። ሲጀመር የእኛ ስራ ይሄ አይደለም። መብታችሁ ከተጣሰ ሌላ ቦታ ሂዱ።" በማለት መልስ ሰጥተዋል።
ይህ አግባብነት የሌለው አካሄድ ነው። ስለ ሰብዓዊ መብት የተቋቋመን አካል ተማሪዎችን አወያያችሁ ብሎ መወንጀል፤ ለሰብዓዊ መብት የተቋቋመም ማዕከል ተወነጀልኩ ብሎ ከፍትሕ ማፈግፈግ የተቋማቶቻችንን የቁልቁለት ጉዞ የሚያፋጥን ነውና ሁሉም ተስተካክሎ ወደ መስመር ይገባ ዘንድ ጥሪያችን ነው።
ጥያቄ አለን __ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
©aaumsu
@fivekjemaa
"የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች መገፋት እና ተግዳሮቶች!" - የጉዳያችን ፖድካስት የመጀመሪያ ርዕስ ሆኗል። ጥሪውን በዘመቻ ላቀረባችሁ ተማሪዎቻችን፤ ጥሪውንም ለሰማው የጉዳያችን ፖድካስት አዘጋጅ ወንድም ዲኑ ዓሊ ምስጋናችን የላቀ ነው።
ሀላፊነቱ የሁሉም ቢሆንም ግብር ከፍለን በራሳችን ሀብት የተቋቋመው ዩኒቨርሲቲያችን ገፊ ሆኖ በቀረበበት፤ አንዳንድ የሀገራችን ሚዲያዎች እና አካላት ፈጣን መልስ ለመስጠት ባልተነሱበት መልስ የሰጠውን ወንድም አመስጋኝ ነን።
ጉዳያችን በመጀመሪያው ፕሮግራም " ስለእህቶቻችን መብት፤ የአለባበስ ነፃነት እና እየደረሰባቸው ያለው ጫና በጥልቀት ይዳሰስበታል። ድምፅ ለሌላቸው ድምፅ የምንሆንበት ልዩ ቆይታ ይኖረናል።" - ብሎናል።
ወደ ተግባር!
እያንዳንዷ እንቅስቃሴ ለሚመጣው ለውጥ አስተዋፅዖው የጎላ ነውና ትኩረት እንስጥ!!
ጥያቄ አለን!
መልስም እንፈልጋለን!!
©aaumsu
@fivekjemaa
"የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች መገፋት እና ተግዳሮቶች!" - የጉዳያችን ፖድካስት የመጀመሪያ ርዕስ ሆኗል። ጥሪውን በዘመቻ ላቀረባችሁ ተማሪዎቻችን፤ ጥሪውንም ለሰማው የጉዳያችን ፖድካስት አዘጋጅ ወንድም ዲኑ ዓሊ ምስጋናችን የላቀ ነው።
ሀላፊነቱ የሁሉም ቢሆንም ግብር ከፍለን በራሳችን ሀብት የተቋቋመው ዩኒቨርሲቲያችን ገፊ ሆኖ በቀረበበት፤ አንዳንድ የሀገራችን ሚዲያዎች እና አካላት ፈጣን መልስ ለመስጠት ባልተነሱበት መልስ የሰጠውን ወንድም አመስጋኝ ነን።
ጉዳያችን በመጀመሪያው ፕሮግራም " ስለእህቶቻችን መብት፤ የአለባበስ ነፃነት እና እየደረሰባቸው ያለው ጫና በጥልቀት ይዳሰስበታል። ድምፅ ለሌላቸው ድምፅ የምንሆንበት ልዩ ቆይታ ይኖረናል።" - ብሎናል።
ወደ ተግባር!
እያንዳንዷ እንቅስቃሴ ለሚመጣው ለውጥ አስተዋፅዖው የጎላ ነውና ትኩረት እንስጥ!!
ጥያቄ አለን!
መልስም እንፈልጋለን!!
©aaumsu
@fivekjemaa
اَلسَّلَامُ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَةُ اللّٰـهِ وَبَرَكاتُهُ👋👋
💥 የደርስ ማስታወሻ::::::::::::::::::
✅ ኢንሻአላህ የኡምደቱል አህካም ደርሳችን ዛሬም የሚቀጥል ይሆናል።ከመጝሪብ እስከ ኢሻ ባለው ስአት በ4 ኪሎ የተማሪዎች መስጂድ እንገናኝ። 🕌
«በሱ ውስጥ እውቀትን ለመፈለግ ብሎ መንገድ የጀመረ ሰው አላህ የጀነትን መንገድ ያገራለታል» ነብዩ ﷺ✨
⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻
https://t.me/Qirat4k/479
📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ📱
https://t.me/Qirat4k
⏰ :- ከመግሪብ - ኢሻ
🕌 4ኪሎ ተማሪዎች መስጅድ
© aau4kilomsj
@fivekjemaa
ዱዓ
رَبَّنَا وَاجْعَلْنَا مُسْلِمَيْنِ لَكَ وَمِن ذُرِّيَّتِنَا أُمَّةً مُّسْلِمَةً لَّكَ وَأَرِنَا مَنَاسِكَنَا وَتُبْ عَلَيْنَا ۖ إِنَّكَ أَنتَ التَّوَّابُ الرَّحِيمُ
"ጌታችን ሆይ! ለአንተ የታዘዝን (ሙስሊሞች) አድርገን፤ ከዘሮቻችንም ለአንተ የታዘዘችን ሕዝብ (አድርግ)፤ የአምልኮታችንንም ሥርዓት አሳየን፤ በእኛም ላይ ተውበትን ተቀበል፤ አንተ ተውበትን ተቀባዩ አዛኙ ነህና።"
(ሱረቱ አል-በቀራህ፡ 128)
የዱዓ ሰዓት 🤲🏽
رَبَّنَا وَاجْعَلْنَا مُسْلِمَيْنِ لَكَ وَمِن ذُرِّيَّتِنَا أُمَّةً مُّسْلِمَةً لَّكَ وَأَرِنَا مَنَاسِكَنَا وَتُبْ عَلَيْنَا ۖ إِنَّكَ أَنتَ التَّوَّابُ الرَّحِيمُ
"ጌታችን ሆይ! ለአንተ የታዘዝን (ሙስሊሞች) አድርገን፤ ከዘሮቻችንም ለአንተ የታዘዘችን ሕዝብ (አድርግ)፤ የአምልኮታችንንም ሥርዓት አሳየን፤ በእኛም ላይ ተውበትን ተቀበል፤ አንተ ተውበትን ተቀባዩ አዛኙ ነህና።"
(ሱረቱ አል-በቀራህ፡ 128)
የዱዓ ሰዓት 🤲🏽
رَبَّنَا وَاجْعَلْنَا مُسْلِمَيْنِ لَكَ وَمِن ذُرِّيَّتِنَا أُمَّةً مُّسْلِمَةً لَّكَ وَأَرِنَا مَنَاسِكَنَا وَتُبْ عَلَيْنَا ۖ إِنَّكَ أَنتَ التَّوَّابُ الرَّحِيمُ
"ጌታችን ሆይ! ለአንተ የታዘዝን (ሙስሊሞች) አድርገን፤ ከዘሮቻችንም ለአንተ የታዘዘችን ሕዝብ (አድርግ)፤ የአምልኮታችንንም ሥርዓት አሳየን፤ በእኛም ላይ ተውበትን ተቀበል፤ አንተ ተውበትን ተቀባዩ አዛኙ ነህና።" (ሱረቱ አል-በቀራህ፡ 128)
@fivekjemaa
🎉ዛሬ ጁመዓ ነው በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋትን እናብዛ🎉
إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى
النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا
عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ﷺ
🌟🌟اللهم صل على محمد وعلى آل محمد كما صليت على إبراهيم وعلى آل إبراهيم في العالمين إنك حميد مجيد🌟🌟
۩ ከጁምዓ ቀን ሱናዎች፦
➊ መታጠብ
➋ ሽቶ መቀባት(ለወንዶች)
➌ መፋቂያ(ሲዋክ) መጠቀም
➍ ቆንጆ ልብስ መልበስ
➎ ሱረቱል ካህፍ መቅራት
"ሱረቱል ካህፍን በጁምዓ ቀን መቅራት፤ በሁለቱ ጁምዓዎች መካከል የሚበራ ብርሃን (ኑር) ይሆንልሃል/ ይሆንልሻል።"
ይህ ማለት አላህ እስከሚቀጥለው አርብ ድረስ ልብአችንን በብርሃን ይሞላዋል፣ ትክክለኛውንና ስህተቱን የምንለይበትን ጥበብ ይሰጠናል ማለት ነው።
➏ በጊዜ መስጂድ መግባት
➐ ዱዓ እና ሰለዋት ማብዛት ﷺ
‣ በመጨረሻው ሰአት (ከአስር በኋላ ) ዱዓ ማድረግ-ለዲን ሲሉ እኘታገሉ ላሉም እህት/ወንድሞቻችን በዱዓ እናስታውሳቸው!!
በውዱ ነብያችን ላይ ሶለዋት ማብዛትንም አንርሳ❤️
اللهم صلِّ وسلم وبارك على سيدنا وحبيبنا ونبينا محمد وعلى آله وصحبه وسلم تسليماً كثيراً ﷺ
🌟 መልካም ጁምአ🌟
@fivekjemaa
Repost from AAU - Muslim Students Union
ቀላል ቻሌንጅ ለመብት ጥያቄያችን
ወንድም ዲኑ ዓሊ ጉዳያችን የሚል ፖድካስት ሊጀምር የመጀመሪያው እንግዳ በድምፅ እንዲመረጥ አቅርቧል። ሕብረታችንም ስለመብት ጥያቄያችን ለሚዲያ ለማድረስ እንቅስቃሴ ላይ ያለበት ሰዓት ነውና አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በማለት የሚዲያ ዘመቻ ላይ ላለው ጀመዓችን የሚዲያ እድል እናመቻች። ሊንኩ https://www.facebook.com/100063706240231/posts/1589231966543663/?app=fbl
ነው።
ይህ ለቢላል እና ሱመያ ልጆች ትንሹ ቻሌንጅ ነው። እውን እናድርገው። የጻፋችሁትን አስተያየት ስክሪንሾት (Screenshot) በማንሳት በቦታችን @Niqab_issueBot በኩል ላኩልን።
ጥያቄ አለን!
መልስም እንፈልጋለን!!
@aaumsu
እዚህ ላይ ሐሳብ ብንሰጠው።
https://www.facebook.com/100063706240231/posts/1589231966543663/?app=fbl
ዲኑ አሊ ነው። ጉዳያችን የሚል ፖድካስት ሊጀምር ማንን ላቅርብ ብሎ ነው። ስለ ሙስሊም ተማሪዎች መፍትሔ የሚያመጣን ስለዚያ የሚያወራ ማንንም አካል ጋብዝ በሉት።
Repost from AAU - Muslim Students Union
+1
የሸገር እንግዳ !
ስለ ሰብዓዊ መብቱ ሊጠይቅ፣ ሊሞግት፣ ሊታገል ጉዞውን የጀመረው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴቶች ቅፍለት ሌላኛው የዛሬ መዳረሻ ሸገር FM ነበር። "ስለምን? ማንን እንጠይቅልዎ?!" - በሚለው ፕሮግራማቸው ላይ "ስለ ሰብዓዊ መብታችን፤ ስለ ክብራችን፤ ስለ እምነታችን፤ ስለ ዘውዳችን፤ ስለ የሕይዎት ትርጉማችን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን፤ የዶክተር ሳሙኤልን አመራር ጠይቁልን።" - በማለት ድምፃቸውን አሰምተዋል።
ይህ በክብር ለመኖር የሚከፈል ትንሹ መስዋዕትነት ነው። ዩኒቨርሲቲውን በአግባቡ ያስተዳድራል ተብሎ የተቀመጠው የዶክተር ሳሙኤል አመራር የዩኒቨርሲቲውን ተማሪ ስለመብቱ እንዲታገል ፈርዶበታልና እህቶቻችን የትምህርት ጊዜያቸውን ሰውተው ስለ ክብር ዘውዳቸው ይለፉ ዘንድ ግድ ሆኗል። ፀሐዩ ሳይበግራቸው፤ በረዶ እየዘነበባቸው፤ ለእስክርቢቶ የተላከላቸውን ለታክሲ ከፍለው፤ የካፌ ምሳ እና እራት እያለፋቸው ይታገሉ ዘንድ ግድ ሆኗል።
የሱመያ ልጆች ትዕግስትን፣ ትግልን እና መስዋዕትነትን ከእናታቸው ተምረዋልና ደስ እያላቸው በቁርጠኝነት ከአንዱ ወደ ሌላው ሁሉንም አጀብ በሚያሰኝ መልኩ ተንቀሳቅሰዋል።
ሆኖም ግን ይህ ጅማሮው ነው። የቢላል ወራሾችም የራሳቸውን ድርሻ የሚወጡ ይሆናል። በቅንጅት እና በብልሐት በሚደረገው የመብት ጥያቄ እንቅስቃሴ መብታችንን ለፍተን፣ ጠይቀን እና ታግለን እናስከብራለን።
አይደለም ወይ?
ጥያቄ አለን !
መልስም እንፈልጋለን !!!
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኑ ዘንድ በARTs TV ቅሬታ አቀረቡ ! ! !
-------------------------------------------
መጋቢት 24 / 2018 ዓ.ል
-------------------------------------------
ከሚዲያ የመጀመሪያ ደረጃ ተግባራት መካከል በደልን ማጋለጥ፤ ለፍትሕ መትጋት እና ማህበረሰብን በእኩልነት ማገልገል ይጠቀሳሉ። የሀገር ብሌን የሆኑ የልሕቀት ማዕከላት ከፍትሕ እና ነፃነት ይልቅ በደልን እና ጭቆናን መታዎቂያ አድርገው የሀገርን ስም ሲያጠፉ ቀድሞ በመሠለፍ ስለሀገር ስም እና የነገ እድል ድምፅ መሆን ከሚዲያዎች ሀላፊነት ነው።
በዚህም ምክንያት ስለ ፍትሕ ጉዞውን የጀመረው የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች ቅፍለት ከARTs ቲቪ ከትመው ውለዋል። እየደረሰባቸው ስላለው በደል ጩኸው፤ ስለ ነፃነታቸው ጠይቀው፤ ስለ ፍትሕ ሁሉም ዘብ ይሆን ዘንድ አስገንዝበው ተመልሰዋል።
ቁጭ ብለው ያወጡትን ጨቋኝ መመሪያ ቆመን ልንታገል ግድ ሆኗልና እየተንቀሳቀስን ነው። ስለ ሀገራችን ልጆች መብት ሳያስቡ 12 አመት የለፉበትን ትምህርት ለማምከን በመመሪያ ስም ሴራ ይዘው መጥተዋልና እርሱን ማምከን ግዴታችን ሆኗል።
ነፃነት በነፃ አይገኝም የተባለው ለዚህ ነው። መብትም በትግል እንጂ ተለምኖ አይወሰድም።
ጥያቄ አለን !
መልስም እንፈልጋለን ! ! !
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በአባይ ቲቪ በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ አቤቱታ አቀረቡ ! ! !
-------------------------------------------
መጋቢት 24 / 2018 ዓ.ል
-------------------------------------------
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እያደረሰ ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለሕዝብ የተቋቋሙ ሚዲያዎች እንዲያጋልጡ እና ስለ ፍትሕ ዘብ እንዲቆሙ በዩኒቨርስቲው ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ዘመቻ መጀመሩ ይታወቃል። በዛሬው እለትም ተማሪዎቹ በARTs ቲቪ ዋና ፅ/ቤት በመገኘት ሚዲያዎው ድምፅ በመሆን ተቋማዊ ሀላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ አልፎ እንደ አፍሪካ ተምሳሌት ተደርጎ የሚወሰድ የልሕቀት ማዕከል ነውና አመራሮቹ ሕግን ጥሰት ባወጡት መመሪያ መካከል ስሙ ሊጠፋ አይገባም። ስለሆነም ፍትሕ ሰፍኖ ተማሪዎች መብታቸው ተጠብቆ እስኪማሩ ድረስ በሁሉም ቦታ በሁሉም መንገድ ጥያቄያችን ይቀጥላል።
መጅሊስ፣ ሰላም ሚኒስቴር፣ የሴቶች እና ሕፃናት ጉዳዮች ሚኒስቴር፣ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ ሚዲያዎች እና ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰዎች እንደአጠቃላይ አጀንዳውን አጀንዳቸው አድርገው ለሚመጣው ፍትሐዊ ለውጥ አስተዋፅዖ ያደርጉ ዘንድ ጥሪያችን ነው።
@aaumsu
Repost from AAU - Muslim Students Union
+6
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ሴቶች በNBC TV ዋና ጽ/ቤት በመገኘት በዩኒቨርስቲው እየደረሰባቸው ስላለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት ድምፅ ይሆኗቸው ዘንድ አቤቱታ አቀረቡ ! ! !
-------------------------------------------
መጋቢት 24 / 2018 ዓ.ል
-------------------------------------------
በዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ ፕሬዚዳንትነት የሚመራው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ከ2017 ዓ.ል ጀምሮ የተማሪዎቹን ሰብዓዊ መብት የሚጥስ መመሪያ አውጥቶ በመተግበር ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል። ይህንን አድሎአዊ መመሪያ ተከትሎ ተማሪዎች በተደጋጋሚ ቅሬታቸውን ቢያቀርቡም፣ ዩኒቨርሲቲው ግን የውይይት በሮችን በመዝጋትና የተማሪዎችን ሰብዓዊ መብት ወደ ጎን በመተው በደሉን ቀጥሎበታል።
ከዚህ ቀደም በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን ድምፃቸውን ይሰማ ዘንድ ጥሪ በማቅረብ ላይ እንቅስቃሴ ላይ የሚገኙ እህቶቻችን፣ እንቅስቃሴያቸውን በማስቀጠል ዛሬ መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ል በNBC TV ዋና ጽሕፈት ቤት በአካል በመገኘት ቅሬታቸውን አቅርበዋል። የሚመለከታቸው የሚዲያ ተቋማትም በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥ እየደረሰ ያለውን የግፍ መመሪያ ለሕዝብ ይፋ በማድረግ የፍትሕ ድምፅ እንዲሆኑልን ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
መሠረታዊ መብቶቻችን ተከብረውና ጨቋኙ መመሪያ ተሻሽሎ ፍትሕ እስኪሰፍን ድረስ ሰላማዊ ትግላችንን አናቆምም!!
ጥያቄ አለን!
መልስም እንፈልጋለን!!
@aaumsu
