Nuradis🥀(ኑርአዲስ)🥀منهج السلف
前往频道在 Telegram
ትክክለኛው ኢስላማዊ አስተምህሮ ከቁርአን ፣ከሀዲስ ፣[በሰለፎች አረዳድ] ከታማኝ ኡለማዎችና፣ከትክክለኛ ቂያስ ተጠናቅሮ ይቀርብበታል አላማዬ ሶሻል ሚዲያው ላይ ኡማውን ለማገልገል ነው! ማንኛውም አስተያዬት ሲኖራችሁ @Rebi_Zidni_Elma_N87 ላይ አስፍሩልኝ። ስህተትም ባያችሁ ጊዜ አርሙኝ ጀዛኩሙል`ሏሁ ኸይራ
显示更多1 304
订阅者
-224 小时
-77 天
-130 天
帖子存档
🔺ሁላችንም ልንቀበላቸው የሚገባ
ሶስት እውነታዎች
① ከሞት ማምለጥ የለም
② ዱኒያ ላይ እረፍት የለም
③በሰዎች የማይዘለፍና የማይተች
ማንም የለም!
እነዚህን እውነታዎች ከልቡ ያወቀና
የተቀበለ ሰው በህይወቱ ውስጥ
የሚደርሱበትን ጫናዎችና ፈተናዎችን
ተቋቁሞ ማለፍ ይችላል::
ከሞት ነቢያትም አልዳኑም ሰው ሁሉ
የተፈጠረው ሊሞት ነው ዋናው ነገር
ኻቲማ አምሮ መሞቱ ነው
ስም ማጥፋትና የሌለውን መለጠፍ
አሏህና መልእክተኞቹ ላይም ተፈጽሟል!
የሰው ልጅ ከምጥ ሰዓት ጀምሮ
በሰከራተል መውት ነፍሱ እስክትወጣ
ድረስ የተሟላ እረፍትን አያገኝም
ከሞት በኋላ ሙእሚኖች ያርፋሉ
የከሃዲያን ድካምና ስቃይ በርትቶ
ይቀጥላል...
🔹የአሏህ ባሪያዎች ሆይ፥
ረጀም ጉዞ የሚጠብቀው ሰው
በየመንገዱ ዳርቻ ላይ የቆሙ ስራ
ፈቶች አላማውን አያስረሱትም!.
,,,,የቀጠለ
➡️እህቴ ሱሪ በሻርብ መልበስ የጀመርሽው መች ነው ? ለዛውም ሻርቡ አንዳንዶቹ ጣል ብቻ ነው ሚያደርጉት
➡️ሱሪ በሻርብ እንድትለብሺ ያነሳሳሽ ነገር ምንድነው ?እነማን ሲለብሱስ አይተሽ ነው ?
➡️እና ከዛ በፊት ስትለቢሺው የነበረው አለባበስ እንዴት ነበር ላንቺ ? በዛ ሰአት በዚህ መልኩ ሲለብሱ የነበሩ እህቶች ስታዪ እንዴት ነበር ያለሽ አመለካከት ለነሱ ?
➡️መልበስ ስትጀምሪ ውስጥሽ ይነግርሽ ነበር መልበሱ ትክክል እንዳልነበረ ቀስ በቀስ ሰው እየፈራሽም ነገር ግን ያ ተግባርሽ ከጊዜያት በኃላ ኢማንሽ እያዳከመው ሄደና ከዛም ምንም አልመስል አለሽ አይደል እህቴ⁉️
➡️አሁን መቼም ኢማን በልብ ነው ከላይ ያለው አለባበሴ አይደለም እንደማትይኝ ተስፋ አደርጋለሁ,,,,!
ምክንያቱም ለዚህ ማስረጃ ያ ውዱ ነቢያችን ላንቺ ያ ሁሉ መስዋትነት የከፈሉት ነቢይ ንግግር ነው 👇
أَلاَ وَإِنَّ فِي الْجَسَدِ مُضْغَةً إِذَا صَلَحَتْ صَلَحَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، وَإِذَا فَسَدَتْ فَسَدَ الْجَسَدُ كُلُّهُ، أَلاَ وهِيَ الْقَلْبُ
አዋጅ! አካል ውስጥ ቁራጭ ስጋ አለች
እሷ ከተስተካከለች መላ አካል ይስተካከላል እሷ ከተበላሸች መላ አካል ይበላሻል። ንቁ! እሷም ልብ ነች! [አልቡኻሪይ፡ 52] [ሙስሊም፡ 1599]
እኔ ምለው ሴት እህቶቻችን ለምንድነው ሱሪ በሻብ የምትለብሱት ?
ይሄንን ሀላል የሚያደርግ የቁርአን አንቀፅ ወይም ሐዲስ አግኝታችሁ ነውን ?
ካልሆነስ የማንን ሱና ነው እየተከተልሽ ያለሽው ?
كتاب الداء والدواء لابن قيم الجوزية , الشيخ عبد الرزاق البدر
ሸይኽ ዐብዱረዛቅ ስለ« አድ-ዳእ ወድ-ደዋእ» ኪታብ
الوالدة زينة البيوت !
«እናት የቤት ጌጥ ናት !
🎙فضيلة الشيخ
عبد الرزاق البدر حفظه الله
منقول
✅የሸሪዓ እውቀት ሙዝ ልጦ እንደመጉረስ አይደለም።
➡️ይልቅ መሬት አርሶ፣ ስንዴ ዘርቶ፣ ሲደርስ አጭዶ፣ ወቅቶ፣ አበጥሮ አስፈጭቶ፣ አብኩቶ፣ ኩፍ እስኪል ጠብቆ ከዛ ጋግሮ ሲበስል እንደ መብላትና ከዛም በላይ ነው!።
➡️ቀደምትና የዘመናችንም ትክክለኛ የዕውቀት ባለቤቶችም 10... 20 እና 30 አመታትን ዕውቀት ፍለጋ ላይ ያሰልፉ የነበረው ለዚህ ነው።
➡️ጥቂት ኪታቦችን በመማር ወይም በማንበብና ሙሓደራዎችን በማዳመጥ ብቻ በቂ ዒልም አግኝቻለሁ ብሎ ማሰብና ከዛም አልፎ ሌሎችን ለማስተማር በቅቻለሁ ማለት የዒልምን ምንነት አለመረዳትና ደረጃውንም አቅልሎ ማየት ነው።
➡️ዛፍ ስለተከሉ ብቻ ፍሬና ጥላ ማግኘት አይቻልም፤ ዒልምም መፅሐፍትን ስላነበቡ ብቻ አይገኝም፤ ፊት ለፊት ያገኙትን ቴምር አንስቶ፣ ወይም ሙዝን ልጦ እንደመጉረስም ቀላል አይደለም።
የዕውቀት ባለቤቶች ጋር ለረጅም ጊዜ መማር፣ የተማሩትን ሁሌም ደጋግሞ ማጥናት፣ በወቁት መስራት፣
ቁርኣንና ሐዲሥን ለመረዳት የሚያስፈልጉ የተለታዩ የትምህርት ዓይነቶችን ማጥናትና ያገኙትን ዕውቀት ለሌሎች ለማስተላለፍ አረዳድና ግንዛቤያችን ትክክል መሆኑንና ለሌሎች ለማድርስ የምንከተለው መንገድም ልክ መሆኑን ማረጋገጥ ይጠበቅብናል።
➡️በዘመናችን ዒልም ተደራሽነቱ የቀነሰበትና ያለውም በረካ ያጣበት አንዱ ምክንያት የዒልም ሐቁ፣ አደብና ቅደም-ተከተሉ አለመጠበቁ ነው።
Repost from Nuradis🥀(ኑርአዲስ)🥀منهج السلف
ቁርአን ላይ የምትፅፋ ሰዎች ታቀቡ። አይቻልምና ተጠንቀቁ።
قال الشيخ ابن باز -رحمه الله :
" لا يجوز أن يكتب شيء ، المصحف لا يكتب فيه شيء ، مجرد إلا من كلام الله - جل وعلا ، لا يكتب حواشي ، ولا علامات تجويدية ولا غير ذلك ؛ لأن المصحف يجب أن يجرده ، ويكون خالصاً لكلام الله - عز وجل ".
فتاوى نور على الدرب | 📚.
Repost from Nuradis🥀(ኑርአዲስ)🥀منهج السلف
🥀ምንኛ ያማረ ቲላዋ ነው ❗️
[ فمن زحزح عن النار وأدخل الجنة فقد فاز ] أعظم فوز ما تيسر من آل عمران
للقارئ الشيخ د.ياسر_الدوسري
@Nuradis53 @Nuradis53
┈┅•● 📘📕📗 ●•┉┈
ወላሂ እንደዚህ ንግግር የሚያስደነግጥ ነገር የለም👇
▪️قال العلامة المحدث مقبل بن هادي الوادعي رحمه الله:
نخشى أن أقواماً يتعلمون عندنا، ويدخلون الجنة
ونحن عند الأبواب، أو نحن - والعياذ بالله - قد أُخذ بنا إلى مكان آخر.
ينبغي أن نخشى على أنفسنا من الرياء، وينبغي أن نخشى على أنفسنا من الغرور.
قمع المعاند صـ ١٤٧
ሰዎች እኛ ዘንድ ተምረው እነሱ ጀነት ሊገቡ እኛ ደግሞ በራፍ ላይ ልንሆን ወይም አላህ ይጠብቀንና ወደ ሌላ ቦታ እንዳንወሰድ እንፈራለን።
ነፍስያችን ላይ ከ ሪያ ወይም ከይዩልኝ ልንፈራ ይገባናል፤ ነፍሲያችን ላይ በራስ ከመደነቅ ልንፈራ ይገባናል።”
[ኢማም ሙቅቢል አላህ ይዘንላቸው]
✅የአሹራ ቀን ፆም በተመለከተ❗️
================
➡️አቡ ቀታዳህ አል አንሷርይ አሏህ መልካም ስራው ይውደድለትና እንዲህ አለ፦
የአሏህ መልእክተኛ ﷺ ስለ አሹራ ቀን ፆም ተጠይቀው እንዲህም አሉ፦ ያለፈውን አንድ አመት ወንጀል ያብሳል ብለዋል።
(ሙስሊም ዘግቦታል።)
➡️የሚፆመው 10ኛው ቀን ሲሆን ነገር ግን አህለል ኪታቦችን ለመኻለፍ ዘጠነኛውን ቀን መፆም የፈለገ በላጩም ይህ ነውና ነገ ረቡዕ 9ኛው ቀን ሲሆ ከነገ ወዲያ እለተ ሀሙስ ደግሞ 10ኛው ቀን ነው ስለዚህ ወር ናው ዕለተ ሐሙስ ቀን 18/10/2018 ነው።
➡️ዘጠነኛው ቀን መጨመር ያልተመቸው ደግሞ አስረኛውና አስራ አንደኛው ቀን ማለትም ሐሙስ እና ጁሙዓ መፆም ይችላል።
➡️የቻለ ደግሞ ሶስቱንም ቀን በተከታታይ መፃም ይቻላል።
➡️በዚህ መሰረት ዘጠነኛው ወይም አስአንደኛው ቀን መፃም ያልቻለ ወይም ያልተመቸው አንዳንድ ዑለሞች የተጠላ ነው ቢሉም ነገር ግን ትክክለኛው ግን የተጠላ አይሆንም ምንም ችግር የለውምና 10ኛውን ቀን ብቻ መፆም ይቻላል በዚህ ምክንያት ዋናውን ቀን እንዳያመልጣችሁ።
✅ ሸኽ ሷሊህ አልፈውዛን አሏህ ይጠብቃቸውና እንዲህ ብለዋል።
ሴት ልጅ አጭር ልብስ በልጆቿም በመህረሞቿ (በወንድሟ፣ በአባቷ፣ በአጎቷና በሌሎቹም) ፊትለፊት መልበስ አይፈቀድላትም።
በመህረሞቿም ፊት ቢሆን የምትከፍተው ፊትና የማያመጣ በተለምዶ የሚታየው (ፊቷ፣ አጆቿ፣ ፀጉሯ) ነው። አጭር ልብስ መልበስ የሚፈቀድላት ለባሏ ብቻ ነው።»
📕المُنتقى 170/3
✍️
“ሁለት ሰዎች ለትንኝ ክንፍ ብለው ተገዳደሉ።”
የሚል ወሬ ብትሰማ; የሁለቱንም አስተሳሰብ ተችተህ ታላግጥባቸው ነበር።
ታድያ……
የዓለም ህዝብ በአጠቃላይ [አላህ ያዘነለት ሲቀር] ለዛች አላህ ዘንድ የትንኝ ክንፍ ታህል እንኳ ቦታ ለሌላት ዱንያ ብሎ ሲገዳደል ምን ሊባል ነው❓
ነብያችንﷺ እንዳሉት፦
«لو كانت الدنيا تعدل عند الله جناح بعوضة ما سقى كافراً منها شربة ماء
ዱንያ አላህ ዘንድ የትንኝ ክንፍ ያህል የምትመዝን ብትሆን ኖሮ; ካፊር ከዱንያ ምንም ውሃ አይጎነጭም ነበር።»
Https://t.me/Nuradis53
Https://t.me/Nuradis53
