1 147
订阅者
无数据24 小时
-27 天
-1930 天
帖子存档
1 146
እንዴት ናችሁ።
የወንድም መላኩ ቶማ ወንድም ስላረፈ መፅናናትን እየተመኘን የቀብር ስነ-ስርዓቱ ነገ ሚያዚያ 12 ኮተቤ ካራ መድሐኒዓለም ከ5_6 ሰአት እንደሆነ እናሳውቃለን።
ነፍስ ይማርልን።
1 146
እንዴት ናችሁ።
የወንድም መላኩ ቶማ ወንድም ስላረፈ መፅናናትን እየተመኘን የቀብር ስነ-ስርዓቱ ነገ ሚያዚያ 12 ኮተቤ ካራ መድሐኒዓለም ከ5_6 ሰአት እንደሆነ እናሳውቃለን።
ነፍስ ይማርልን።እንዴት ናችሁ።
የወንድም መላኩ ቶማ ወንድም ስላረፈ መፅናናትን እየተመኘን የቀብር ስነ-ስርዓቱ ነገ ሚያዚያ 12 ኮተቤ ካራ መድሐኒዓለም ከ5_6 ሰአት እንደሆነ እናሳውቃለን።
ነፍስ ይማርልን።
1 146
+8
ሚያዝያ 09 ቀን 2017ዓ.ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ማዕድ የማጋራት መርሀ-ግብር ተካሄደ።
መጭውን የትንሳኤ በዓል ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸዉ የኮሌጁ ሰራተኞች እና ኮሌጁ ለሚያሳድጋቸው ልጆች ማዕድ ማጋራት በዛሬው ዕለት አከናውኗል።
የማዕድ ማጋራቱን ያዘጋጀዉ የተ/መ/ፖ/ቴ/ኮሌጅ ከቀድሞ የተ/መ/ተማሪዎች ሕብረት ጋር በመተባበር ሲሆን ለ 109 የኮሌጁ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸዉ ሰራተኞች እና ኮሌጁ ለሚያሳድጋቸው 9 ህጻናት የ1500.00 ብር ፣ የዶሮና እንቁላል ስጦታ ተበርክቶላቸዋል ።
በመርሃ ግብሩ ተገኝተዉ መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሀመድ የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም በበዓል ወቅት የመተሳሰብና ተካፍሎ መብላትን እንዲሁም የአብሮነት ባህልን የሚያዳብር ሲሆን በጎነት ለዛሬ ብቻ ሳይሆን በህይወት ዘመናችን ሁሉ ልንከተለው የሚገባ መርህ ነው ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
አያይዘውም በቀጣይ ኮሌጁ ላሉበት ተደራራቢና ዓበይት ጉዳዮች ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ እጅ ለእጅ ሆኖ በመስራት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት አሳስበው የጸጥታ እና ደህንነት ሁኔታውን እንዲሁም የጽዳቱን ጉዳይ በተመለከተ የጥበቃ እና የጽዳት ስራ ክፍል ሰራተኞች ትልቅ ሃላፊነት እንዳለባቸው አጽእኖት ሰጥተው ተናግረዋል።
በመጨረሻም በዕለቱ ድጋፍ ለተደረገላቸው ሰራተኞች በዓሉ የሰላም ፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሆንላቸው መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል ።
የኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+5
ሚያዝያ 8/2016ዓ.ም
የቢዝነስ ስልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና አካሄደ።
የቢዝነስ ስልጠና ዘርፍ በHuman resources mamagement የሰለጠኑ 18 ሴት እና 2 ወንድ በድምር 20 ሠልጣኞች ከደረጃ ሦስት ወደ ደረጃ አራት ለመሸጋገር ለምዘና የተቀመጡ ተቀምጠዋል። ምዘናው በትምህርት ክፍሉ ተዘጋጅቶ በስልጠና ዘርፉ ተገምግሞና ጸድቆ የሚሰጥ ሲሆን ለምዘና የተቀመጡ 20 ተመዛኞች ምዘናውን በብቃት አጠናቀው/ 100% በምዘናው ብቁ ሆነው ወደሚቀጥለው ደረጃ መሸጋገራቸውን የስልጠና ዘርፍ ተጠሪው አቶ አለማየሁ ፈንታ መረጃውን አጋርተውናል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+3
አንድ ሳምንት የቀረው የቴክኖሎጂ ስራን ለማጠናቀቅ አሰልጣኞች ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ።
👉 አሁንም በየቡድናችሁ ተገኝታችሁ ከባልደረቦቻችሁ ጋር እየሰራችሁ ያልሆናችሁ አሰልጣኞች የስራው መጓተት ምክንያት ላለመሆን በአስቸኳይ ተቀየጧቸው።
🙏🙏🙏መልካም የስራ ግዜ🙏🙏🙏
1 146
+4
ዕለተ ዓርብ ሚያዝያ 03/2017 ዓ.ም
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስልጠና ዘርፍ በከተማ ደረጃ የተዘጋጀውን ሞዴል አስመዘነ ።
ለምዘና የተቀመጡት በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስልጠና ዘርፍ በ Hardwar and Networking service የደረጃ 4 ተመራቂ ሰልጣኞች ሲሆኑ በየደረጃው የተቋም ውስጥ ምዘና በአግባቡ እየተመዘኑ ከደረጃ ወደ ቀጣይ ደረጃ እየተሸጋገሩ የመጡ መሆናቸውን ተጠቁሟል።
በትላንትናው ዕለት የተጀመረው የተግባር ምዘና 7ሴቶች እና 17ወንዶች ለምዘና የተቀመጡ ሲሆን በዛሬው ዕለትም የቲዮሪ ምዘናው እንደሚቀጥል የስልጠና ዘርፍ አስተባባሪዋ ወ/ሮ ዘውዲቱ ጸጋዬ መረጃውን አጋርተውናል ።
የዝግጅት ክፍላችን ለተመዛኞች መልካም ውጤትን ይመኛል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+6
ሚያዝያ 02/2017ዓ.ም
የ9ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ሪፖርት ቀረበ ።
በISO የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራም የተጀመረው የዛሬው መድረክ በአቀራረቡ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ ያቀረቡት የኮሌጁ የተቋማት አቅም ግንባታ ም/ዲን ዶ/ር ከበደ ባዬቻ እያዋዙና እያዝናኑ ከምን ግዜውም በላይ በግልጽ ቋንቋ የISO ምንነትና አስፈላጊነቱን እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል ።
በመቀጠልም በኮሌጁ ዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ለኮሌጁ የአስተዳደር ሰራተኞች የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ሪፖርት ቀርቧል ። በቀረበው ሪፖርት ላይ ከተሳታፊዎች ሐሳብ አስተያየት ፣ ጥያቄዎች ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
