1 146
订阅者
-224 小时
-47 天
-1930 天
帖子存档
1 146
+7
መጋቢት 26/2017ዓ.ም
በISO 21001:2018 Educational quality management system" ትግበራ ላይ የልምድ ልውውጥ በንፋስ ስልክ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ተካሄደ።
የኮሌጁ ኮር አመራር፣ ማኔጅመንት እና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት በንፋስ ስልክ ፖ/ቴ/ኮሌጅ በመገኘት በISO 21001:2018 Educational quality management system ትግበራ ሂደትን ላይ የልምድ ልውውጥ አካሂዷል ።
ኮሌጃችን እውቅና ለማግኘት በሚደረገው እንቅስቃሴ ረጅም መንገድ የተጓዘ መሆኑ ይታወቃል ። በመሆኑም የተጀመረው ስራ በውጤት እንዲጠናቀቅ ለማስቻል ቀደም ብሎ ምዘናውን ባከናወነው በንፋስ ስልክ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመገኘትና በየዘርፉ በመሰማራት መረጃን ተጋርቷል ።
በቀጣይም ከልምድ ልውውጡ የተገኘውን መልካም ተሞክሮ በማቀናጀት ወደ ተግባር እንደሚገባ አስተባባሪው አቶ ሚካኤል ጎአ አሳስበዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+3
መጋቢት 26/2017ዓ.ም
የ9ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ሪፖርት ቀረበ ።
በኮሌጁ ዕቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት ለኮሌጁ ኮር አመራር፣ ማኔጅመንት እና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት የ9ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ሪፖርት ቀረበ ።
በቀረበው ሪፖርት ላይ በክፍል ሃላፊዎች ሐሳብ አስተያየት ተሰጥቶበት መካተት አለበት ያሏቸውንም ለግሰዋል ።
በአጠቃላይ በይዘትም ሆነ በአቀራረብ የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማጎልበት መስተካከል አለበት ተብሎ የቀረቡ አስተያየቶች በአፋጣኝ እንዲስተካከሉ አቅጣጫ ተሰጥቷል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+5
በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የክላስተር ደረጃ የተግባራዊ ጥናት እና ምርምር ውድድር ተካሄደ። በውድድሩም በአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ አሰልጣኞች የተሰራ እና በተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኞች የተሰራ የተግባራዊ ጥናት እና ምርምር ለውድድር የቀረበ ሲሆን በዘርፉ ልምድ ባላቸው ከተለያዩ ኮሌጆች በተውጣጡ ባለሙያዎች ተዳኝቷል።
👉 በዳኝነት የተሳተፉ ባለሙያዎች ከመዳኘት ባሻገር ገንቢ አስተያየቶችን ለተወዳዳሪዎች በመስጠት ውጤቱንም በአግባቡ አሳውቀዋል።
1 146
ዕለተ ሐሙስ መጋቢት 25/2017ዓ.ም
በአውቶሞቲቭ ስልጠና ዘርፍ በከተማ ደረጃ የተዘጋጀ ሞዴል ምዘና እየተሰጠ ነው ።
የአውቶሞቲቭ ስልጠና ዘርፍ የ2017ዓ.ም መደበኛ ተመራቂ ሰልጣኞች በማስመዘን ፋና ወጊ ሆኖ ስራውን ጀምሯል።
በትላንትናው ዕለት የተጀመረው እና ለተከታታይ 3 ቀናት የሚዘልቀው ምዘና በመደበኛው ስልጠና በደረጃ 4 ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ በአውቶ ኤሌክትሪክ 9 እና በአውቶ ሜካኒክስ 21 ተመዛኞች በከተማ ደረጃ የተዘጋጀውን Holistic (ሆልስቲክ) ሞዴል ምዘና እየተመዘኑ ነው ።
ተመዛኞች የተቋም ምዘናውን በየደረጃው ተመዝነው ብቃታቸውን እያረጋገጡ እዚህ ደረጃ የደረሱ ሲሆን በሞዴል ምዘናው ውጤታማ የማይሆኑ ሰልጣኞች በቀጣይ ክፍተታቸው ተሞልቶላቸው ዳግም ለምዘና እንደሚቀመጡ የስልጠና ዘርፍ ተጠሪው የቶ ደሳለኝ አዱኛ ጠቁመዋል።
በመዛኝነትም ሆነ በሱፐር ቫይዘርነት ምዘናውን የሚያከናውኑት አሠልጣኞች ብቃታቸውን በምዘና ያረጋገጡ መሆናቸውን አስተባባሪው አቶ ይሳቅ አበራ ይገልጻሉ ።
በምዘናው ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የምዘናውን አስፈላጊነት እና በቀጣይ በሃገራቀፍ ደረጃ ለሚሰጠው ምዘና ያለውን ጠቀሜታንም አብራርተዋል ።
በመጨረሻም ሰልጣኞች በስልጠናው ብቁ ሆነው እንዲወጡና ምዘናውን በብቃት እንዲያጠናቅቁ የሚያስችል የተሟላ የማሰልጠኛ ማቴሪያል ባይኖርም አሰልጣኙ አቅም የፈቀደውን ሁሉ ጥረት በማድረግ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ያሰለጠ ሲሆን የCOC ምዘናው ከኮሌጃችን ውጪ የሚሰጥ ከሆነ በሰልጣኞች ውጤት ላይ ክፍተት ሊፈጠር ይችላል በማለት ስጋታቸውን የገለጹት የስልጠና ዘርፍ ተጠሪው አቶ ደሳለኝ አዱኛ በቀጣይ የተጓደሉ የማሰልጠኛ ማቴሪያል ቢሟላልን ውጤታማ ስልጠና እና ተጠባቂ የምዘና ውጤት ማስመዝገብ ይቻላል። ይህን ለማድረግ ደግሞ ኮሌጁ በተጓደሉ የማሰልጠኛ ማቴሪያል ማሟላት ላይ በትኩረት ቢሰራ በማለት ሃሳባቸውን ለግሰዋል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+8
ዕለተ ማክሰኞ መጋቢት 23/2017ዓ.ም
የ9ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ።
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች በስሩ ከሚገኙ የስልጠና ዘርፎች እና የስራ ክፍሎች ጋር የ9 ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማ አካሄዱ። የመረጃው ምንጭ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ነው።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+7
ዕለተ ሰኞ መጋቢት 22/2017 ዓ.ም
በምልክት ቋንቋ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ።
ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሌሎች አቻ ኮሌጆች በተለየ ሁኔታ በከተማ ደረጃ መስማት የተሳናቸውን ሰልጣኞች ተቀብሎ የሚያሰልጥን መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።
በመሆኑም በተለያዩ ዘርፎች ላይ እነኝህን ሰላጣኞች ለመርዳት/ለማገዝ ያስችል ዘንድ ከበር ላይ የጥበቃ ሰራተኞች ጀምሮ ከተለያዩ ዘርፎች ለተውጣጡ የኮሌጁ ሰራተኞችን ለ15 ቀናት ሲሰጥ የነበረው የምልክት ቋንቋ ስልጠና በዛሬው ዕለት የተጠናቀቀ ሲሆን ስልጠናቸውን በአግባቡ ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን እና የኮሌጁ ዋና ዲን ተገኝተው የምስክር ወረቀት ሰጥተዋል ። ኃላፊዎቹ ይህን ስልጠና ላዘጋጁት እና ላሠለጠኑት አቶ ያሬድ ጫሞ እና ፀሐይ ምስጋናቸውን በማቅረብ መስማት የተሳናቸውን ወገኖች መርዳት መሠጠትን የሚፈልግ ነው በመሆኑም ሁላችሁም ባገኛችሁት ግንዛቤ እነኝህን ወገናች ከልብ መርዳት ያስፈልጋል ። ይህን እንደምታደርጉት/ እንደምትረረዷቸው ባለሙሉ ተስፋ ነኝ በማለት በአጽንኦት አሳስበዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+7
መጋቢት 22/2017 ዓ.ም
የ ተፈሪ መኮንን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ምስረታ 100ኛ ዓመት ክብረ በዓል 27 ቀን ቀረው።
''ያለፈዉን ማክበር ፤ መጭውን መገንባት'' በሚል መሪ ቃል ለሚከበረዉ 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል (count down) በኮሌጁ ኮሙኒኬሽን ቡድን ከ90 ቀናት ቀሩት ጀምሮ በየዕለቱ ቆጠራውን እያከናወነ የቆየ መሆኑ ይታወሳል ። ከዚህ በተጨማሪ የተፈሪ መኮነን ፖ/ቴ/ኮሌጅ የኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ ከኮሌጁ ጋር በመተባበር የ30 ቀናት ወደ ታች ቆጠራ (count down)ማስጀመሪያ ፕሮግራም አካሂዷል።
የ30 ቀናት ወደ ታች ቆጠራ (Count down )መርሃግብሩ የተጀመረዉ ባለፈዉ ዓርብ ሲሆን በመክፈቻ ስነስርአቱ የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ንግግር አድርገዋል ።
በዚህ የ30 ቀናት ወደ ታች ቆጠራ (count down ) ፕሮግራም ሙዚቃ፣ግጥም፣ መነባንብ፣ የስዕል ዓውደ ርዕይ እና አጭር ውይይት የቀረበ ሲሆን እስከ ክብረ በዓሉ ማብሰሪያ ዕለት የት/ክፍሉ ሰልጣኞች እና አሰልጣኞች የሚሳተፉበት የጥበብ ድግሶችን እንደሚያዘጋጅ ተነግሯል ።
የስነ-ጥበብ ክፍል ባልደረባ መምህር ኃይሉ ክፍሌ ደግሞ የቀሪ ቀን መቁጠሪያ ካላንደር አዘጋጅተው በኮሌጁ መምህራን ካፍቴሪያ ባለው የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ እንዲለጠፍ አድርገዋል::
የኮሙኒኬሽን ቡድን!!
1 146
+9
ዕለተ ዓርብ መጋቢት 19/2017ዓ.ም
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሠልጣኞች ሮተሪ ክለብ ልገሳ አደረገ።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሠልጣኞች ሮተሪ ክለብ በአካባቢ ለሚገኙት የአቅመ ደካማ እና ችግርተኛ ቤተሰቦችየኢድ አልፈጥር በዓልን ምክንያት በማድረግ 30 ለሚሆኑ ህፃናት የአልባሳት እርዳታ መደረጉን የኰሌጁ የኮሚኒኬሽን ቡድን በቦታው ተገኝቶ ለማየት ችሏል።
የሮተሪ ክለብ አባላቱ አልባሳቱን ከተለያዪ በጎ አድራጊ ግለሰቦች ያሰባሰቡት እንደሆነ በልገሳ ሥነ-ሥርዓቱ ከተደረገው ንግግር እና ከሠልጣኞች ሮተሪ ክለብ ፕሬዘዳንት ወንድማገኝ አለኸኝ የተገኘው መረጃ ያስረዳል።
በዚህ የልገሳ ሥነ-ሥርዓት አርቲስት ልዑል ሰገድ ረታ ከሮተሪ ኢንተርናሽናል አዲስ አበባ እና አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የኰሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን በክብር እንግድነት ተገኝተው ስጦታውን እንደሰጡና ክለቡን እንዳበረታቱ ለማወቅ ተችሏል። በተያያዘ እርደታ የተደረገላቸው ሰዎች ደግሞ በጎ አድራጊዎችን እና ተባባሪዎቻቸውን አመስግኘዋል።
ይህ ምግባረ ሠናይ ሥራ ወገን ወገኑን መርዳት እንዳለበት የሚያስተምር ለሮተሪ ክለብ አባላቱ ፋና ወጊ ሥራ ነው። ከእምነትም ሰብአዊነትም አንፃር መበረታታት ያለበት ተግባርም ነው እንላለን።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
