ch
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

关闭频道
1 146
订阅者
无数据24 小时
-37
-1830
帖子存档
photo content

photo content

መልካም እድል !!

photo content

photo content

photo content

photo content
+1

🎆🎆 የእንጦጦ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአልባሳት ትዕይንት (Fashion Show) ውድድር ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ 5 ኮሌጆች መካከል ሆነ🎆🎆 👉 ነገ በሚካሄደው የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር የኮሌጃ
🎆🎆 የእንጦጦ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአልባሳት ትዕይንት (Fashion Show) ውድድር ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ 5 ኮሌጆች መካከል ሆነ🎆🎆 👉 ነገ በሚካሄደው የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር የኮሌጃችን አሰልጣኞች እና ሰልጣኞች በሚያቀርቡት 2ኛ ዙር ትዕይንት ላይ እንድትገኙ እየጋበዝን፡ መልካም ውጤትን እንመኛለን።

photo content

የክህሎት_ውድድር_ውጤት_ያመጡ_አሰልጣኝ፣_ሰልጣኝ_እና_አንቀሳቃሽ_እውቅና.jpg1.57 KB

photo content

T M S በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው.....

photo content
+7

የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠናን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ ለአገር ኢኮኖሚ እድገት ያለው ድርሻ የማይተካ ነው። ሰኔ 17/2016 ዓ ም ቴክኒክና ሙያን በአግባቡ መጠቀም ተግዳሮቶቹንም መፍታት ከተቻለ ለአገር ኢኮኖሚ እድገት ያለው ድርሻ የማይተካ መሆኑን የዘርፉ ምሁራን አስገነዘቡ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እያከበረ የሚገኘው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አካል የሆነው የፓናል ውይይት "ቴክኒክና ሙያ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ሀሳብ ዛሬ በዓድዋ ድል መታሰቢያ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ በዘርፉ ለረጅም አመታት የሥራ እና የትምህርት ልምድ ያላቸው ምሁራን የመወያያ ጽሁፎችን አቅርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል። በፌዴራል ቴክኒክና ሙያ ኢንስቲትዩት የአመራርና ማኔጅመንት ትምህርት ክፍል ሃላፊና የዘርፉ ባለሙያ የሆኑት አቶ አበባው ለማ ባቀረቡት ጽሁፍ፣ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ምቹ የስራ እድልን በመፍጠር የሀገርን ኢኮኖሚ ለማሳደግ ትልቅ ድርሻ ያለው መሆኑን አመላክተዋል። በዚህ መነሻነት ዘርፉ ላይ የሚሰጠው ስልጠና ውጤት ተኮር ስራን የተከተለና ከገበያና ኢንዱስትሪ ፍላጐት የሚመነጭ ሊሆን እንደሚገባው ገልጸዋል። ለዚህ ደግሞ የግሉን ዘርፍ አሁን ካለውም በላይ በስፋት ማሳተፍ እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል። የኢንዱስትሪና የከተማ መሰረተ ልማት ፖሊሲ ጥናት ማእከል ሃላፊ አማረ ባህተቡ (ዶ/ር) በኩላቸው፣ ቴክኖሎጂ እንዲያድግ ቴክኒክና ሙያ ላይ ተጨባጭ ስራዎችን መስራት ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ አራተኛው የኢንዱስትሪ አብዮት ቴክኖሎጂ ላይ እንድትደርስ እንደ አውቶሜሽንና መሰል የክህሎት ማበልጸጊያ ስራዎች ላይ መስራት እንዳለባትም ዶክተር አማረ ገልጸዋል። ከፍተኛ የፖሊሲ አማካሪ አንቶኒዮስ ፍሊቼ፣ "ስልጠና ከሌለ ኢኮኖሚ የለም። የአንድ ሀገር ኢኮኖሚ የሚጐለብተው የሰው ሀይል ልማት ላይ ከተሰራ ነው። ሰራተኛን ማልማት ካልተቻለ ኢኮኖሚን ማሰብ አአፕቻልም፤ ቴክኒክና ሙያ ከሌለ ኢኮኖሚ የለም" ብለዋል። እንደ ጀርመን፣ ጃፓንና አንድ አንድ የምእራብ አፍሪካ አገራት በዚህ ረገድ በዘርፉ ያላቸው ተሞክሮ አመርቂ መሆኑና ኢትዮጵያም በተለይ ኢንዱስትሪ ላይ የሚሰጡ ስልጠናዎችን በማዳበር ከቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ የሚገኘውን ዘርፈ ብዙ ጥቅም ልታገኝ ይገባል ነው ያሉት። በፓናል ውይይቱ ላይ በበቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ በቂ ክህሎትና ስብእና ያለውን ባለሙያ ለማፍራት ባለፉት አመታት በርካታ ስራዎች መከናወናቸው ተገልጿል። የቴክኒክና ሙያ ስትራቴጂ መከለሱም ዘርፉን ብቃት ባለው የሰው ሀይል ማነቃቃት ተችሏል ነው የተባለው። እስካሁን በዘርፉ ከተመዘገቡት ውጤቶች ባሻገር በተለይ ከትምህርት ጋር ተያይዞ ተግዳሮቶች ማጋጠማቸው የተነሳ ሲሆን፤ የፓናል ውይይቱ መሰል ችግሮችን ለመፍታት አንኳር ሀሳቦች የሚነሱበትና ወደ ፊት ዘርፉን ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ ግብአቶች እንደሚገኝበት ተብራርቷል። በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ተማሪዎች በትምህርት ቤት በቂ ክህሎት ይዘው መውጣት ላይ ከፍተኛ ክፍተት መኖሩና ለዚህ ደግሞ የግሉን ዘርፍ ተሳታፊ ያደረገ ትኩረት እንደሚሻ፣ የወጡ ፖሊሲዎችን በአግባቡ ተግባራዊ የማድረግ ሃላፊነት ከመንግስትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እንደሚጠበቅ ተነስቷል። ምንጭ:- ኢ.ፒ.ድ

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content