ch
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

关闭频道
1 149
订阅者
无数据24 小时
-37
-1830
帖子存档
photo content
+9

በአ/አ/ከ/አ የመንግስት ንብረት ባለስልጣን ባበለፀገው AMIS ሶፍትዌር ላይ ግንዛቤ ተፈጠረ ። 🇪🇹 ጥር 06 /2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአ/አ/ከ አስተዳደር የመንግስት ንብረት ባለስልጣን ባበለፀገው AMIS ሶፍትዌር ግንዛቤ ተፈጠረ ። በለቱም የኮሌጅ የተቋማት አቅም ግንባታ ምክትል ዲን ዶ/ር ከበደ  በሬቻ የበለፀገው ሶፍትዌር ብዙ ችግሮችን የሚፈታና አሰራራችንን ግልጽና ቀልጣፋ የመረጃ ፍሰት እንዲኖረው ያስችለዋል በማለት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩን አስጀምረዋል ። ስልጠናውም ከአ/አ/ከ አአስተዳደር የመንግስት ንብረት ባለስልጣን በመጡ ባለሙያዎች የተሰጠ ሲሆን ከመድረኩ ለተነሱ የአተገባበርና የግንዛቤ ጥያቄዎች በባለሙያዎቹ በኩል ማብራሪያ ተሰቶበታል ። የኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የተፈጠረው ግንዛቤ የበለፀገውን AMIS ሶፍትዌር በብቃት ለመተግበርና ለመጠቀም የሚያስችል አቅም እንደነበረው ገልፀው በቀጣይ እንዲህ አይነቱ ድጋፍ እንዲቀጥል መልክት አስተላልፈዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+8

photo content

photo content

የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከክላስተር ኮሌጆች ጋር የጋራ ስምምነት ተፈራረመ ። 🇪🇹 ጥር 05 /2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከክላስተር ኮሌጆች ማለትም ከአራዳ፣ ከሰላም ፣ልደታ እና ከየካ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እና የጋራ የመግባቢያ ሰነድ (MOU) ተፈራረመ ። ኮሌጁ ጥር 2 ቀን 2018 ዓ.ም ባካሄደው በዚህ መድረክ ላይ በኮሌጆቹ መካከል ያለውን ትብብር ለማጠናከር፣ የሀብት ክፍፍልን ለማሳለጥ እና ወቅቱን የዋጀ ስልጠና በመስጠት ብቁ እና ተወዳዳሪ የሰለጠነ የሰው ኃይል ለገበያ ለማቅረብ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በተጨማሪም የልምድ ልውውጥ በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ስልጠና ዙሪያ ያሉ ምርጥ ተሞክሮዎችን በመለዋወጥ ፣ የሀብት አጠቃቀም ላይ ያሉ የላብራቶሪ፣ የዎርክሾፕ እና የሰው ኃይል አቅምን በጋራ በመጠቀም የሥልጠና ጥራትን ማሳደግ ፣ የገበያ ትስስር ሰልጣኞች ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ በቀጥታ ወደ ሥራ እንዲሰማሩ የሚያስችል ምቹ ሁኔታ መፍጠር ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች እንደሆኑ ተገልፀዋል ። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአራዳ፣ ከሰላም ፣ልደታ እና ከየካ ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር የተደረገው ይህ የሥራ ስምምነት (MOU)፣ ኮሌጆቹ በሥርዓተ-ትምህርት ዝግጅት እና በተግባራዊ ሥልጠና ወቅት በቅንጅት እንዲሰሩ ሕጋዊ ማዕቀፍ ከመፍጠሩም ባሻገር በተለይ በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን በመቅረፍ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+2

photo content
+9

photo content

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ። 🇪🇹ጥር 04/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሃያ ሁለተኛ ሳምንት ተካሄደ። በእለቱ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የስልጠና ዘርፍ ክፍል ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ አሰልጣኝ በመጋበዝ ለኮሌጅ ማህበረሰብ በ " የአንድ ነገር ሀይል " በሚል ርእስ ጉዳይ ላይ ሰፋ ያለ ትንታኔ በአቶ ወንደሰን እንዳለ ቀርቧል ። ድጋሜ እድል ቢሰጠን እንደገና ልናስተካክለው የምንፈልገው አንድ ነገር አለ በማለት ያለፈን ጊዜ ልንመልሰው እንደማንችል እና የአንድ ሰው ሀይል ስር ብዙ ዘርፍ ፣ብዙ ሀሳብ ፣ብዙ መውጣት መውረድ እንዳለና በዚያ ውስጥ ደግሞ ሰልጣኞቻችን እንዳሉና በአንድ ሰልጣኝ ውስጥ ብዙ ሀይል እንዳለ ራሱን ፣ ቤተሰብን ብሎም ሀገሩን እና እኛንም የሚጠቅም አንድ አቅም ሀይል እንዳለ ማወቅ ተገቢ መሆኑን አስገንዝበዋል ። የአንድ ደቂቃን ሀይል እንደኮሌጅ ማህበረሰብ በመገንዘብ ትኩረትን ስራና ስራ ላይ በማድረግ መስራት ወደፊት መልካም ፍሬ ፈርቶ ለማየት እንደሚያስችል ገልፀዋል ። አቅማችን በጊዜ ሂደት ውስጥ የተገደበ መሆኑን መገንዘብና በጊዜው መከናወን ያለበትን ተግባር በጊዜው የሚጠበቅብንን መስራት አሁን ያለን አቅም ፣ጉልበት እና ጊዜ ነገ እንደምናጣው በመረዳት ማከናወን ይጠበቅብናል ።ጊዜ ወደኋላ አያልፍም ወደፊት ሄዶ ይጠብቀናል በማለት ሁሉም የሰራውን ይቀበላል በማለት አስረድተዋል ። አጠቃለውም ያለን አቅም ጉልበት ሳይደክም የምንሰራውን ስራ አስተውለን ብንሰራ ፣ብናንጽ ፣ ብናስተምር እና ሁላችንም በአንድ አቅም ውስጥ በተደመረ ሀይል በአንድ የኮሌጅ አቅም ሆነን መስራት ይጠበቅብናል በማለት መልክት አስተላልፈዋል ። በመጨረሻም የኮሌጁ የሽሮሜዳ ካምፓስ ምክትል ዲን አቶ ተስፋ ጺኦን ስልጠናውን ላመቻቹት የየኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ የስልጠና ዘርፍ ክፍል ምስጋና አቅርበው በቀጣይም ሌሎች ክፍሎች ተሞክሮውን መውሰድ እንዳለባቸው ገልፀዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+8

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ የሰላም የፍቅር የአንድነት እንዲሆንላችሁ እንመኛለ ተፈሪ መኮንን
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ የሰላም የፍቅር የአንድነት እንዲሆንላችሁ እንመኛለ ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮምንኬሽን ቡድን

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ የሰላም የፍቅር የአንድነት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን ተፈሪ መኮን
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ የሰላም የፍቅር የአንድነት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን ተፈሪ መኮንን ፖለቲካ ኮሌጅ

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ የሰላም የፍቅር የአንድነት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉ የሰላም የፍቅር የአንድነት እንዲሆንላችሁ እንመኛለን።

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማእድ ማጋራት መረሀ ግብር ተካሄደ ። 🇪🇹ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኮሌጅ እናት አምባሳደር ለሚደገፋ ልጆች የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ የማእድ ማጋራት መረሀ ግብር ተካሄደ ። በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሌጁ የአካዳሚክ ምክትል ዲን  እና ጊዜያዊ ዋና ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ እንኳን ለገና በዓል አደረሳችሁ መልክት የስተላለፉ ሲሆን በቀጣይ ድጋፉ በተጠናከረ መልኩ እንደሚደረግ በመግለፅ ይህ የበዓል ስጦታ ኮሌጁ ከጎናችሁ መሆኑን የሚያሳይ ፕሮግራም ነው በማለት ገልፀዋል ። በተጨማሪም የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽ /ም /ዲን አቶ ወንድም ሲያምረኝ የእንኳን ለ2018ዓ/ም የገና በዓል አደረሳችሁ መልክት አስተላልፈዋል ። ኮሌጁ ከሚሰጣቸው አገልግሎት በተጨማሪ የማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት አንድ እንደሆና ኮሌጁ የአረጋዊያን ቤት እድሳት ፣ በኮሌጅ ዝቅተኛ ደሞዝ ሰራተኞች እና የኮሌጅ እናት አምባሳደር የሚደገፉ ልጆች እንደሆኑ ገልፀዋል ። በቀጣይም ኮሌጅ በቻለው አቅም ከጎናቸው እንደሆነ በማስገንዘብ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ኮሌጅ ያዘጋጀውን የበዓል ስጦታ ሰጥተዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://t.me/EntotoPtc1917 ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማህበራዊ ሚዲያዎች 1. https://vm.tiktok.com 2. https://t.me/EntotoPtc1917 3. https://youtube.com/@entototms 4. https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+1

photo content
+9

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ። 🇪🇹ታህሳስ 27/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክ የኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሀያ ሁለተኛ ሳምንት ተካሄደ።በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት የኮሌጁ የሬጅስትራር ጽ/ሀላፊ አቶ ስመኝ ሚደቅሳ አሉታዊ አስተሳሰብ /Negative Thinking/ በሚል መሪ ቃል ለኮሌጁ ህብረተሰብ ግንዛቤ ሰጥተዋል ።ቀና ያልሆነ አስተሳሰብ መገለጫዎች ማለትም ችግር ሲፈጠር አንድ መአት እንደመጣ አድርጎ ማሰብ ፣ ላጋጠሙን ችግሮች ሌሎችን መውቀስ፣ የሚፈጠሩ ነገሮችን ሁሉ ከራስ ጋር ማያያዝ ፣ስም መለጠፍ ፣ ከአቅማችን በላይ ለሆኑ ነገሮች እራስን ማስጨነቅ ፣ በስሜት ሆኖ መወሰን እና ችግርን ከመጠን በላይ አጉልቶ ማየት እንደማሳያ ተብራርተው ቀርበዋል ። የኮሌጅ የተቋማት ልማት አስ/ጉ/ም ዲን ዶ/ር ከበደ በሬቻ አሉታዊ አስተሳሰብ በኮሌጃችን የሚታይ መሆኑን ገልፀው ከግጭትን በሰከነ መንፈስ ሆኖ መፍታት ላይ የነበራቸውን ልምድ ለኮሌጁ ማህበረሰብ አካፍለዋል ። በቀጣይም የኮሌጁ አመራሮች ፣ ዳሬክተር ፣ ብድን መሪ ፣ አሰልጣኞች ልንወስደው እና ልንተገብረው የሚገባን የአዎንዊ አስተሳሰብን በማዳበር ተግባብተን መስራት እና ማገልገል አለብን የሚል መልክት አስተላልፈዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://t.me/EntotoPtc1917 ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማህበራዊ ሚዲያዎች https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content

photo content
+8