ch
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

关闭频道
1 149
订阅者
无数据24 小时
-37
-1830
帖子存档
የEASE ፕሮጀክት አፈጻጸም እና አመታዊ ዕቅድ ይፋ ተደረገ፤ በአቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ የሊደርሺፕ ስልጠና ተሰጠ ። 🇪🇹ታህሳስ 25/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክትን በተመለከተ ያለበትን የአፈፃፀም ደረጃ እና የወደፊት አመታዊ ዕቅዱን ለኮሌጁ ማኔጅመንትና አካዳሚክ ሰራተኞች አቅርቧል። በተጨማሪም የኮሌጁ ማኔጅመንት እና አካዳሚክ ሰራተኞች የአቅም ግንባታ የሊደርሺፕ ስልጠና ወስደዋል። በቀረበው የEASE ፕሮጀክት የአፈፃፀም ደረጃ እና የወደፊት አመታዊ እቅድ ላይ የኮሌጁ ማኔጅመንት፣ አካዳሚክ ሰራተኞች እና የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች ባደረጉት ዉይይት የEASE ፕሮጀክት በኮሌጁ ውስጥ እየተንቀሳቀሰበት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በዝርዝር ገምግመዋል። የአፈፃፀም ቁመና በፕሮጀክቱ ከተቀመጡት ግቦች አንፃር የተመዘገቡትን ውጤቶች፣ የተፈጸሙ ተግባራትን እንዲሁም በቀጣይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶችንና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል። የፕሮጀክቱ ትኩረት የትምህርት ጥራትን ማሳደግ፣ የዘመናዊ የትምህርት ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ተቋማዊ አቅምን ማጎልበት ላይ መሆኑ ተገልጿል።  በቀጣይ አመት የEASE ፕሮጀክትን በተሻለ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ዝርዝር የድርጊት መርሃ ግብር ቀርቦ የጋራ የሰነድ ስምምነት ተፈርሟል ። በተጨማሪም የኮሌጁ  ማኔጅመንት እና አካዳሚክ አመራሮች  የአቅም ግንባታ የሊደርሺፕ ስልጠና ተሳታፊ ሆነዋል።የስልጠናው ትኩረት ስልጠናው በዘመናዊ አመራር፣ በለውጥ አስተዳደር፣ በውሳኔ አሰጣጥ እና የቡድን ስራን በማጠናከር ዙሪያ ላይ ትኩረት አድርጎ የተሰጠ ሲሆን የEASE ፕሮጀክትን በኮሌጁ በተሳካ ሁኔታ ለመምራት የሚያስችል እውቀትና ክህሎት ላይ ያተኮረ ነበር። የስልጠናው ዋና ዓላማ የኮሌጁ አመራሮች የፕሮጀክቱን አላማዎች ከኮሌጁ ተልዕኮ ጋር በማጣመር በተሻለ ብቃት እንዲመሩ እና በየደረጃው ያሉ ሰራተኞችን ወደተሻለ የስራ አፈፃፀም እንዲያነሳሱ ለመርዳት ነው። የኮሌጁ የአካዳሚክ ምክትል ዲን  እና ጊዜያዊ ዋና ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በሰጡት አስተያየት የEASE ፕሮጀክት የኮሌጁን የትምህርት ጥራት የማረጋገጥ ጉዞ ወሳኝ አካል መሆኑን ገልፀው ። አመራሩ የወሰደው የሊደርሺፕ ስልጠና እና ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ለፕሮጀክቱ ስኬት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል። በቀጣይም ኮሌጁ ለትምህርት ጥራት መሻሻል እና ለሰራተኞቹ አቅም ግንባታ ትኩረት መስጠቱን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ከቤቱ ለተነሱ የዉይይት ጥያቄዎች የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪዎች እና የኮሌጁ አመራሮች ሰፊ ማብራርያ ሰተዉበታል መድረኩም ስራን በቁርጠኝነት ለመስራት በተለያየ የአመራር ደረጃ ያሉ አመራሮች ቃል በማስገባት እና የስምምነት ሰነድና በመፈራረም ተጠናቃል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://t.me/EntotoPtc1917 ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማህበራዊ ሚዲያዎች https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

የEASE ፕሮጀክት አፈጻጸም እና አመታዊ ዕቅድ ይፋ ተደረገ፤ በአቅም ግንባታ ላይ ያተኮረ የሊደርሺፕ ስልጠና ተሰጠ ። 🇪🇹ታህሳስ 25/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የEASE ፕሮጀክትን በተመለከተ ያለበትን የአፈፃፀም ደረጃ እና የወደፊት አመታዊ ዕቅዱን ለኮሌጁ ማኔጅመንትና አካዳሚክ ሰራተኞች አቅርቧል። በተጨማሪም የኮሌጁ ማኔጅመንት እና አካዳሚክ ሰራተኞች የአቅም ግንባታ የሊደርሺፕ ስልጠና ወስደዋል። በቀረበው የEASE ፕሮጀክት የአፈፃፀም ደረጃ እና የወደፊት አመታዊ እቅድ ላይ የኮሌጁ ማኔጅመንት፣ አካዳሚክ ሰራተኞች እና የፕሮጀክቱ አስተባባሪዎች ባደረጉት ዉይይት የEASE ፕሮጀክት በኮሌጁ ውስጥ እየተንቀሳቀሰበት ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በዝርዝር ገምግመዋል። የአፈፃፀም ቁመና በፕሮጀክቱ ከተቀመጡት ግቦች አንፃር የተመዘገቡትን ውጤቶች፣ የተፈጸሙ ተግባራትን እንዲሁም በቀጣይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶችንና የመፍትሄ አቅጣጫዎች ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል። የፕሮጀክቱ ትኩረት የትምህርት ጥራትን ማሳደግ፣ የዘመናዊ የትምህርት ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም እና ተቋማዊ አቅምን ማጎልበት ላይ መሆኑ ተገልጿል።  በቀጣይ አመት የEASE ፕሮጀክትን በተሻለ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል ዝርዝር የድርጊት መርሃ ግብር ቀርቦ የጋራ የሰነድ ስምምነት ተፈርሟል ። በተጨማሪም የኮሌጁ  ማኔጅመንት እና አካዳሚክ አመራሮች  የአቅም ግንባታ የሊደርሺፕ ስልጠና ተሳታፊ ሆነዋል።የስልጠናው ትኩረት ስልጠናው በዘመናዊ አመራር፣ በለውጥ አስተዳደር፣ በውሳኔ አሰጣጥ እና የቡድን ስራን በማጠናከር ዙሪያ ላይ ትኩረት አድርጎ የተሰጠ ሲሆን የEASE ፕሮጀክትን በኮሌጁ በተሳካ ሁኔታ ለመምራት የሚያስችል እውቀትና ክህሎት ላይ ያተኮረ ነበር። የስልጠናው ዋና ዓላማ የኮሌጁ አመራሮች የፕሮጀክቱን አላማዎች ከኮሌጁ ተልዕኮ ጋር በማጣመር በተሻለ ብቃት እንዲመሩ እና በየደረጃው ያሉ ሰራተኞችን ወደተሻለ የስራ አፈፃፀም እንዲያነሳሱ ለመርዳት ነው። የኮሌጁ የአካዳሚክ ምክትል ዲን  እና ጊዜያዊ ዋና ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በሰጡት አስተያየት የEASE ፕሮጀክት የኮሌጁን የትምህርት ጥራት የማረጋገጥ ጉዞ ወሳኝ አካል መሆኑን ገልፀው ። አመራሩ የወሰደው የሊደርሺፕ ስልጠና እና ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ለፕሮጀክቱ ስኬት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል ብለዋል። በቀጣይም ኮሌጁ ለትምህርት ጥራት መሻሻል እና ለሰራተኞቹ አቅም ግንባታ ትኩረት መስጠቱን እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። ከቤቱ ለተነሱ የዉይይት ጥያቄዎች የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪዎች እና የኮሌጁ አመራሮች ሰፊ ማብራርያ ሰተዉበታል መድረኩም ስራን በቁርጠኝነት ለመስራት በተለያየ የአመራር ደረጃ ያሉ አመራሮች ቃል በማስገባት እና የስምምነት ሰነድና በመፈራረም ተጠናቃል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://t.me/EntotoPtc1917 ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማህበራዊ ሚዲያዎች https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+6

photo content

photo content

photo content
+7

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተገልጋይና አገልጋይ የውይይት መድረክ ።      🇪🇹ታህሳስ 24/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ   የተገልጋይና አገልጋይ የውይይት መድረክ  ከባለድርሻ አካላት እና ከተገልጋይ ጋር አካሄደ  ።    በውይይቱ ላይ የኮሌጅ ሰልጣኞች  በስልጠና አሰጣጥ ፣ በስልጠና ግብአት አቅርቦት እና በአፓረንት ስልጠና ጥራት ለይ  ጥያቄ ያቀረብ ሲሆን በየዘርፋ ለተነሱት ሀሳቦች የሚመለከታቸው ዳሬክቶሬቶች እና የዘርፉ ተጠሪዎች የኮሌጅ ስ/አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጅ ዋና ዲን ተወካይ ማብራሪያ ሰተውበታል  ። የውይይት መድረኩን በዋነኝነት የመሩት የኮሌጅ  ነባር እና አንጋፋ አሰልጣኝ አቶ ነገሰ ተፈረደኝ ባቀረቡት ሀሳቦች  ላይ ጠቅለል አድርገው ምላሽ ተሰተውበታል ። የኮሌጅ  ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን  ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ኮሌጅ በስልጠና አሰጣጥና ጥራት እና በኢንዱስትሪ ኤኤክስቴንሽን እየሰጠ ያለውን መጠነ ሰፊ አገልግሎት በማስገንዘብ ሰልጣኞች የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ በማስገንዘብ  በመድረኩ ለተሳተፉ የኮሌጁ ሰልጣኞች ፣ የሰልጣኝ ተጠሪዎችና የክባት ተጠሪዎች  ስለነበረው ገንቢ ውይይት አመስግነዋል ። የኮሌጅ ማህበረሰብ እና በየደረጃው የሚመለከታቸው የዘርፍ ተጠሪዎች እና ዳሬክቶሬቶች የተነሱ ሀሳቦችን እንደ ግብአት በመውሰድ  በቀጣይ ተግባራዊ እንዲደረጉ እና በኮሌጁ ዲኖች በኩል የሚፈቱ ጉዳዮችን በትኩረት እንደሚኬድባቸው ገልፀዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+9

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተገልጋይና አገልጋይ የውይይት መድረክ ። 🇪🇹ታህሳስ 24/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተገልጋይና አገልጋይ የውይይት መድረክ ከባለድርሻ አካላት እና ከተገልጋይ ጋር አካሄደ ። በውይይቱ ላይ የኮሌጅ ሰልጣኞች በስልጠና አሰጣጥ ፣ በስልጠና ግብአት አቅርቦት እና በአፓረንት ስልጠና ጥራት ለይ ጥያቄ ያቀረብ ሲሆን በየዘርፋ ለተነሱት ሀሳቦች የሚመለከታቸው ዳሬክቶሬቶች እና የዘርፉ ተጠሪዎች ማብራሪያ ሰተውበታል ። የውይይት መድረኩን በዋነኝነት የመሩት የኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ እና የሽሮሜዳ ካምፓስ ዲን አቶ ለገሰ ተፈረደኝ በቀረቡት ሀሳቦች ላይ ጠቅለል አድርገው ምላሽ ሰተውበታል ። የኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ኮሌጅ በስልጠና አሰጣጥና ጥራት እና በኢንዱስትሪ ኤኤክስቴንሽን እየሰጠ ያለውን መጠነ ሰፊ አገልግሎት በማስገንዘብ ሰልጣኞች የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ በማስገንዘብ በመድረኩ ለተሳተፉ የኮሌጁ ሰልጣኞች ፣ የሰልጣኝ ተጠሪዎችና የክባት ተጠሪዎች ስለነበረው ገንቢ ውይይት አመስግነዋል ። የኮሌጅ ማህበረሰብ እና በየደረጃው የሚመለከታቸው የዘርፍ ተጠሪዎች እና ዳሬክቶሬቶች የተነሱ ሀሳቦችን እንደ ግብአት በመውሰድ በቀጣይ ተግባራዊ እንዲደረጉ እና በኮሌጁ ዲኖች በኩል የሚፈቱ ጉዳዮችን በትኩረት እንደሚኬድባቸው ገልፀዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+9

የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር ዕቅድ አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት እና ከሲቪክ ማህበራት ጋር የተደረገ የውይይት መድረክ ። 🇪🇹ታህሳስ 24/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አፈጻጸም ከባለድርሻ አካላት እና ከሲቪክ ማህበራት ጋር የተደረገ የውይይት መድረክ ። የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር ዕቅድ አፈጻጸም በኮሌጁ እቅድና በጀት ዳሬክቶሬት ወ/ሮ ንግስቲ ገ/ህይወት በዝርዝር ለባለድርሻ አካላት እና ለሲቪክ ማህበራት ቀርቧል ። ከባለድርሻ አካላት እና ከሲቪክ ማህበራት አስተያየትና ጥያቄ የቀረበ ሲሆን በየዘርፋ ለተነሱት ሀሳቦች የሚመለከታቸው ዳሬክቶሬቶች እና የዘርፉ ተጠሪዎች ማብራሪያ ሰተውበታል ። የውይይት መድረኩን በዋነኝነት የመሩት የኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ እና የሽሮሜዳ ካምፓስ ዲን አቶ ተስፋፂኦን በቀረበውን የ6 ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ የተነሱትን ሀሳቦች ጠቅለል አድርገው ምላሽ ሰተውበታል ። ከባለድርሻ አካላት እና ከሲቪክ ማህበራት በሰጡት አስተያየት ኮሌጅ ለማህበረሰቡ ብሎም እንደ ሀገር እያበረከተ ያለውን አስተዋፅዎ አመስግነዋል በማከልም በቀጣይም ኮሌጅ ቢያተኩርበት ያሉትን ገንቢ ሀሳቦች አንስተዋል ።ኮሌጅ ከባለድርሻ አካላት እና ከሲቪክ ማህበራት የተነሱትን ሀሳቦች እንደ ግብአት በመውሰድ ለቀጣይ እቅድ አፈፃፀም ተግባራዊ እንዲደረጉ ከባለድርሻ አካላት እና ከሲቪክ ማህበራት ጋር እንደሚሰራ ገልፆል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+8

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ። 🇪🇹ታህሳስ 20/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክ የኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሀያኛ ሳምንት ተካሄደ።በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት የኮሌጁ አሰልጣኝና የስልጠና ዘርፍ ተጠሪ አቶ ደሳለኝ አድኛ '' ፍረሃትን ማሸነፍና ለውጥን መላመድ " በሚል መሪ ቃል ለኮሌጁ ህብረተሰብ ግንዛቤ ሰተዋል ። ፍርሃት ምንድ ነው? ፣ ለውጥ ምንድ ነው ? ፣የለውጥ ትርጉም በTVET ፣ የፍርሃት አሉታዊ ተፅዕኖዎች እና ፍርሃትን ለማሸነፍ የሚረዱ ስልቶች ላይ ለኮሌጁ ህብረተሰብ ሰፋ ያለ ገለፃ አቅርበዋል ።በለቱም የኮሌጅ የተቋማት ልማት አስ/ጉ/ም ዲን ዶ/ር ከበደ በሬቻ ፍረሃትን ማሸነፍና ለውጥን መላመድ ዘመናዊነት መሆኑን ገልፀው እራሳችንን ከለውጡ ጋር ለማራመድ ዝግጅት በማድረግ ኮሌጃችንን ይበልጥ ተመራጭ እና ተወዳዳሪ ለማድረግ በራሳችን ላይ መስራት አለብን በማለት መልክት አስተላልፈዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://t.me/EntotoPtc1917 ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማህበራዊ ሚዲያዎች 1. https://vm.tiktok.com 2. https://t.me/EntotoPtc1917 3. https://youtube.com/@entototms 4. https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+7

የተፈሪ መኮንን ፖ/ቴ/ኮ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር ዕቅድ አፈጻጸም መድረክ። 🇪🇹ታህሳስ 23/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለኮሌጁ ማህበረሰብ የ2018 በጀት ዓመት የ6 ወር ዕቅድ አፈጻጸም በኮሌጁ እቅድና በጀት ዳሬክቶሬት ወ/ሮ ንግስት ገ/ህይወት በዝርዝር ቀርቧል ። በተጨማሪም የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶርት አቶ መከታው ሹመት በኩል በቀረበውም የ6 ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ የኮሌጅ ማህበረሰብ አስተያየትና ጥያቄ ያቀረብ ሲሆን በየዘርፋ ለተነሱት ሀሳቦች የሚመለከታቸው ዳሬክቶሬቶች እና የዘርፉ ተጠሪዎች ማብራሪያ ሰተውበታል ። የውይይት መድረኩን በዋነኝነት የመሩት የኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ እና የሽሮሜዳ ካምፓስ ዲን አቶ ተስፋፂዮን በቀረበውን የ6 ወር ዕቅድ አፈጻጸም ላይ የተነሱትን ሀሳቦች ጠቅለል አድርገው ምላሽ ሰተውበታል ። የኮሌጅ ማህበረሰብ እና በየደረጃው የሚመለከታቸው የዘርፍ ተጠሪዎች እና ዳሬክቶሬቶች በቀጣይ የተነሱ ሀሳቦችን እንደ ግብአት በመውሰድ ለቀጣይ እቅድ አፈፃፀም ተግባራዊ እንዲያደርጉት በማስገንዘብ በኮሌጁ ዲኖች በኩል የሚፈቱ ጉዳዮችን በትኩረት እንደሚኬድባቸው ገልፀዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+8

photo content

የEASE ፕሮጀክት ከኮሌጁ  አድቫይሰሪ ቦርድና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ከፍተኛ የምክክር እና የእቅድ ዝግጅት ትውውቅ መድረክ በድምቀት ተካሄደ ። 🇪🇹ታህሳስ 18/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አስተባባሪነት የሚመራው የ EASE Project (EASE ፕሮጀክት)፤ የስራ አፈጻጸም ግምገማ፣ የቀጣይ እቅድ ዝግጅት እና የጋራ የውይይት መድረክ በተሳካ ሁኔታ አከናወነ።በዚህ ወሳኝ የምክክር መድረክ ላይ ቁልፍ የሆኑ የፕሮጀክቱ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈዋል። በዋናነትም የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከፍተኛ አመራሮች፣የስራና ክህሎት ቢሮ የስራ ኃላፊዎች፣የአድቫይዘሪ/አማካሪ ቦርድ አመራሮች፣የEASE ፕሮጀክት ስራ አስፈጻሚ አባላት፣ እንዲሁም የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የሆኑ የአራቱ የሥልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች በጋራ ተገኝተዋል። የመድረኩ ዋና ዓላማ የፕሮጀክቱን አጠቃላይ የስራ አፈጻጸም በመገምገም ጥንካሬዎችን እና መሻሻል ያለባቸውን ጉዳዮች መለየት ሲሆን፤ በቀጣይ ፕሮጀክቱ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆን የሚያስችሉ ስትራቴጂካዊ እቅዶች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በውይይቱ ወቅት የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ የሆኑት አራቱ የሥልጠና ዘርፎች እያሳዩት ያለው ለውጥ እና በቀጣይ ሊሰሩ የሚገባቸው የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ከመድረኩ ተሳታፊዎች ጋር ገንቢ ምክክር ተካሂዷል። ተሳታፊዎቹም ፕሮጀክቱ ለወጣቶች የክህሎት ማሻሻያ እና የስራ እድል ፈጠራ እያበረከተ ያለውን አስተዋጽኦ አድንቀው፤ ለቀጣይ ስኬት በጋራ ለመስራት ቃል ገብተዋል።በዚህ የምክክር መድረክ በተሳታፊዎች የጋራ መግባባት እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ተጠናቋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+9

photo content
+1