ch
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

关闭频道
1 149
订阅者
无数据24 小时
-37
-1830
帖子存档
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በእቅድ ዝግጅትና መልካም አስተዳደር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ። 🇪🇹የካቲት 19/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋሙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ለተከታታይ ሦስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው በእቅድ አዘገጃጀትና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በስኬት ተጠናቀቀ። በስልጠና ላይ የኮሌጁ ዲኖች፣ የአካዳሚክ ኮሚሽን አባላት፣ የውስጥ ሱፐርቫይዘር ኮሚቴዎች፣ ዳይሬክቶሬቶች እና የቡድን መሪዎች ተሳትፈዋል። የስልጠናው ዋነኛ ትኩረት ተቋማዊ አሰራርን በማዘመን፣ ውጤት ተኮር እቅዶችን በመንደፍና ፍትሃዊ የአገልግሎት አሰጣጥን በማስፈን ላይ ያተኮረ ነበር። ውጤት ተኮር የእቅድ ዝግጅት ሊለኩ የሚችሉና በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ውጤት የሚያመጡ እንዲሆኑ የሚያስችል ግንዛቤ ከአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስ በመጡ አሰልጣኝ አቶ አለምነህ ዋሴ እና ወንደሰን ሞገስ በኩል ተፈጥሯል። የመልካም አስተዳደር በተቋሙ ውስጥ በሰው ሀብት ስልጠና ባለሙያ በሆኑት አቶ ወንደሰን ሞገስ በስፋት ገለፃ የተሰጠበት ሲሆን ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትንና የህግ የበላይነትን በማስፈን የተገልጋዮችን እርካታ ማሳደግ እንደሚገባ አጽንኦት ተሰጥቶበታል። የውስጥ ሱፐርቫይዘር ኮሚቴዎችና የቡድን መሪዎች የታቀዱ ስራዎችን አፈጻጸም በየወቅቱ በመገምገም፣ ክፍተቶችን በመለየትና ፈጣን የማስተካከያ እርምጃዎችን በመውሰድ ረገድ ያላቸው ሚና በዝርዝር ቀርቧል። የኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በሰጡት አስተያየት የተገኘው ግንዛቤ በቀጣይ ለሚከናወኑ የኮሌጁ የልማትና የመማር ማስተማር ስራዎች የጎላ ፋይዳ እንዳለው ገልጸው፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ሰንሰለቱን በማሳጠር ለተማሪዎችና ለሰራተኞች ቀልጣፋ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ኮሌጁ መሰል የአቅም ግንባታ ስራዎችን በማጠናከር፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ተገልጿል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+8

photo content

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በሽሮሜዳ ካምፓስ ለሶስተኛ ዙር ስልጠና መሰጠት ተጀመረ !! 🇪🇹የካቲት 17/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔትና የስራ ፕሮጀክት የምግብ ዋስትና ፕሮግራም ተጠቃሚዎችን ወደ ዘላቂ የኑሮ ማሻሻያ ፕሮግራም ለማሸጋገር ስልጠና በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በሽሮሜዳ ካምፓስ ለሶስተኛ ዙር ስልጠና መስጠት ተጀመረ ። እንደሚታወቀው ስልጠናው በሁለት ዙር በተሳካ ሁኔታ የተሰጠ ሲሆን ለሶስተኛ ዙር ከ150 በላይ ለሚሆኑ ሰልጣኞች ከየካቲት 16 ጀምሮ ለተከታታይ አምስት ቀናት በዋናነት በንግድ ስራ ክህሎት፣ በንግድ እቅድ አዘገጃጀት እና በስራ ፍለጋ ስልቶች ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+3

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሀገር አቀፍ የክህሎትና ቴክኖሎጂ ውድድር እያደረገ ያለውን ዝግጅት ገመገመ ። 🇪🇹የካቲት 17/2018 ዓ.ም🇪🇹 በአገር አቀፍ እና በከተማ ደረጃ ለሚካሄደው የ2018 ዓ.ም ለ16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት የክህሎትና የቴክኖሎጂ ውድድር ውጤታማ ተሳትፎ ለማድረግ እንዲቻል፤ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአካዳሚክ ኮሚሽን፣ የማናጅመንት አባላትና የስልጠና ዘርፍ ኃላፊዎች በጋራ በመሆን የመስክ ምልከታና የሥራ ሂደት ክትትል አደረጉ። ኮሌጁ በዘንድሮው ውድድር ላይ በ11 የሥልጠና ዘርፎች ለመሳተፍ የታቀደ ሲሆን፣ በዕለቱም በእነዚህ ዘርፎች የሚቀርቡ የፈጠራ ሥራዎችና የቴክኖሎጂ ውጤቶች ያሉበት ደረጃ በዝርዝር ተመልክቷል። ለ16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት የታቀዱ የፋብሪኬሽን ቴክኖሎጂ ውጤቶች እና ሌሎች የፈጠራ ስራዎች ያሉበት የደረሱበት ደረጃ ተገመገመ ሲሆን በክህሎት ውድድሩ የሚሳተፉ ሰልጣኞችና ሜንቶሮቻቸው እያደረጉት ያለው ዝግጅት የተቃኘ ሲሆን፣ ሰልጣኞች የደረሱበት የክህሎት ደረጃም ተመልክቷል። በዝግጅት ሂደቱ ላይ ያጋጠሙ ማነቆዎችና ተግዳሮቶች ቀርበው ውይይት የተደረገባቸው ሲሆን፣ የኮሌጁ አመራሮች በቦታው በመገኘት አፋጣኝ ምላሽ የሚሹ ጉዳዮችን በመለየት የመፍትሄ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል። የኮሌጁ አመራሮች በክትትል ጉብኝቱ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ኮሌጁ በ16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት የክህሎትና የቴክኖሎጂ ውድድር ላይ ተወዳዳሪ ሆኖ እንዲወጣና የላቀ ውጤት እንዲያስመዘግብ አስፈላጊው ድጋፍ ሁሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+6

photo content

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዘርፍ የመስክ ምልከታ ተካሄደ ። 🇪🇹የካቲት 16/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴ/ኮሌጅ የአካዳሚክ ኮሚሽን እና የማናጅመንት አባላትና በስልጠና ዘርፎች በኮሌጅ የኤስቴቲክስ  እና ሆቴልና ቱሪዝም ስልጠና  ዘርፍ የመስክ ምልከታ ተካሄደ ። በተዘጋጀው መነሻ ቼክ ሊስት መሰረት በየስልጠና ዘርፉ ስራ ሂደት የሚገልፅ ስዕላዊ መግለጫ መኖሩ፤የስልጠናው ሂደት በአግባቡ በፕሮጀክት ቤዝድ ስለመሰጠቱ፤የስልጠና ክ/ግዜ በአግባቡ ተግባራዊ ስለመሆኑ፤አሰልጣኝ ሰልጣኝ ጥምርታው፤የሰልጣኞች ውጤት በአዲሱ ፖሊሲ በLO እየተመዘኑ፤የትብብር ስልጠና አተገባበር በእቅድ ስለመመራቱ፤ የአሰልጣኝ/ሰልጣኝ አቻ ለአቻ ግንኙነት እቅድ ስለመኖሩ፤ ፎካል ፐርሰን ስለመመደቡ፤ የክበባት እንቅስቃሴ ፤ የአሰልጣኝ ፤ሰልጣኝ የስልጠና ክ/ግዜ ሰዓት አጠቃቀም፤ የ2017 ዓ.ም ስልጠና አጠናቃቂ ሰልጣኞች የሀገር አቀፍ ምዘና አፈፃፀም ያለበት ደረጃ፤ የስልጠና ወርክሾፕ በ8 ስቴሽን ስለመደራጀቱ፤ምቹ ቢሮ ስለመኖሩ፤የOHS ሞጅል ስለመዘጋጀቱና አተገባበሩ ያለበት ደረጃ፤ ውጤታማ የሪሶርስ አጠቃቀም ስለመኖሩ(የግዜ፤የሰው ሀብት፤የማቴሪያል፤የፋይናንስ)፤በኮሌጁ አመራሮች የሚፈቱ ዋና ዋና ጉዳዮች ካሉ በዝርዝር በአጠቃላይ በ11ዱ ዘረመል/DNA እሳቤዎች በመደበኛ የስልጠና እና የቴክኖሎጂ ስራዎች ስለመተገበራቸው በጥልቀት ተመልክቷል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content

photo content
+5

የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሃያ ስድስተኛ ሳምንት ተካሄደ ። 🇪🇹25/05/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከከተማ ግብርና ዲፓርትመንት ጋር በመተባበር ለኮሌጁ ማህበረሰብ በእንጉዳይ አሰራርና ጥቅሞች ዙሪያ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በዲፖርትመንት ተጠሪና አሰልጣኝ አቶ እድሜአለም ሳልል ተሰጠ ሲሆን በአጭር ጊዜ ስልጠና ወደ ስራ መግባት እንደሚቻል ለማወቅ ተችሏል ። በመድረኩ ላይ እንደተገለጸው፣ የእንጉዳይ ልማት በትንሽ ቦታና በአነስተኛ ካፒታል ሊከናወን የሚችል፣ በአጭር ጊዜ በአንድ ወር ውስጥ ምርት የሚሰጥና ከፍተኛ የገበያ ተፈላጊነት ያለው ዘርፍ ነው። በተለይም በአሁኑ ወቅት በአንድ ኪሎ እስከ 600 ብር የሚሸጥ በመሆኑ፣ ለከተማ ግብርና ተመራጭና አዋጭ የሥራ ዘርፍ መሆኑ ተመላክቷል። የኮሌጁ የተቋማት ልማት አስተዳደር ጉዳዮች ምክትል ዲን ዶ/ር ከበደ በሬቻ በእለቱ እንደገለፁት የቀረበው የግንዛቤ ማስጨበጫ ወቅቱን ያገናዘበና ለኮሌጁ ማህበረሰብ አዲስ የገቢ ምንጭ የሚፈጥር ነው ይህ ግንዛቤ ወደ ተግባር እንዲቀየር በቀጣይ ለሰልጣኞችና ለፍላጎቱ ላላቸው አካላት ስልጠናዎችን ለማመቻቸት ኮሌጁ ዝግጁ መሆኑን ገልጸዋል።ይህ መርሀ-ግብር ኮሌጁ የተግባር ትምህርትን ከዘመናዊ የከተማ ግብርና ጋር በማቀናጀት ለተማሪዎችና ለሰራተኞች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚሰራው ስራ አካል መሆኑ ተገልጿል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+9

photo content

የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ የTTLM ዝግጅት እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ ጀመረ።  🇪🇹የካቲት 14/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም ከፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት፣ በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፎች ላይ  የመማሪያ ማስተማሪያ ሞጁሎች (TTLM) ዝግጅት እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ በይፋ ማስጀመሩን አስታወቀ። ይህ የመማሪያ  ማስተማሪያ ሞጁሎች (TTLM) እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ በዋናነት የሚያተኩረው በሦስት ቁልፍ የስልጠና መስኮች ላይ ሲሆን እነሱም  የሙዚቃ መሳሪያዎች አጠቃቀም ፣የድምፅ ስልጠና  እና አትሌቲክስ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል   በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ የTTLM ዝግጅት እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ  በዘርፉ የሚሰጠውን ስልጠና በጥራት ለመስጠትና የመማር ማስተማር ሂደትን በተሻለ መልኩ ለማሳለጥ የታለመ ተግባር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ።  የኮሌጁ አመራሮች እና የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪዎች እንደገለጹት፣ ይህ ተግባር ለመማር ማስተማር ሂደቱ ስኬታማነት እጅግ ወሳኝ እና ቁልፍ የሚባል ስራ እንደሆነና በተጨማሪም ነባር ካሪኩለሞችን ከወቅቱ የገበያ ፍላጎትና ከቴክኖሎጂ እድገት ጋር በማጣጣም፣ ሰልጣኞች ብቁና ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑ  ይሕ የTTLM ዝግጅትና የካሪኩለም የሪቪዥን ስራ የሰልጣኞችን ተግባራዊ ክህሎት ከማሳደጉ ባለፈ፣ በዘርፉ ያለውን የማስተማር ስታንዳርድ ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል" ሲሉ  የዝግጅቱ አስተባባሪዎች  ገልፀዋል። በ EASE ፕሮጀክት አስተባባሪነት የሚከናወነዉ ይህ መጠነ-ሰፊ የዝግጅት ስራ በEASE (Education and skill for employeblity) ፕሮጀክት ሙሉ ድጋፍ የሚከናወን ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ የክህሎት ልማትን ለማቀናጀትና የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን አቅም ለመገንባት እና የትምህርት ጥራትን ለመጠበቀ ከሚሰራው ስራ አንዱ አካል ነው። በተጨማሪም ከዚህ በፊት ያልተካተቱ ማለትም Digital skill ;Green skill ; Entrepreneurship and moral & ethics የመሳሰሉትንም እንደሚያካትት ተገልጿል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ የTTLM ዝግጅት እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ ጀመረ።  🇪🇹የካቲት 14/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም ከፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት፣ በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፎች ላይ  የመማሪያ ማስተማሪያ ሞጁሎች (TTLM) ዝግጅት እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ በይፋ ማስጀመሩን አስታወቀ። ይህ የመማሪያ  ማስተማሪያ ሞጁሎች (TTLM) እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ በዋናነት የሚያተኩረው በሦስት ቁልፍ የስልጠና መስኮች ላይ ሲሆን እነሱም  የሙዚቃ መሳሪያዎች አጠቃቀም ፣የድምፅ ስልጠና  እና አትሌቲክስ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል   በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ የTTLM ዝግጅት እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ  በዘርፉ የሚሰጠውን ስልጠና በጥራት ለመስጠትና የመማር ማስተማር ሂደትን በተሻለ መልኩ ለማሳለጥ የታለመ ተግባር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ።  የኮሌጁ አመራሮች እና የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪዎች እንደገለጹት፣ ይህ ተግባር ለመማር ማስተማር ሂደቱ ስኬታማነት እጅግ ወሳኝ እና ቁልፍ የሚባል ስራ እንደሆነና በተጨማሪም ነባር ካሪኩለሞችን ከወቅቱ የገበያ ፍላጎትና ከቴክኖሎጂ እድገት ጋር በማጣጣም፣ ሰልጣኞች ብቁና ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑ  ይሕ የTTLM ዝግጅትና የካሪኩለም የሪቪዥን ስራ የሰልጣኞችን ተግባራዊ ክህሎት ከማሳደጉ ባለፈ፣ በዘርፉ ያለውን የማስተማር ስታንዳርድ ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል" ሲሉ  የዝግጅቱ አስተባባሪዎች  ገልፀዋል። በ EASE ፕሮጀክት አስተባባሪነት የሚከናወነዉ ይህ መጠነ-ሰፊ የዝግጅት ስራ በEASE (Education and skill for employeblity) ፕሮጀክት ሙሉ ድጋፍ የሚከናወን ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ የክህሎት ልማትን ለማቀናጀትና የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን አቅም ለመገንባት እና የትምህርት ጥራትን ለመጠበቀ ከሚሰራው ስራ አንዱ አካል ነው። በተጨማሪም ከዚህ በፊት ያልተካተቱ ማለትም Digital skill ;Green skill ; Entrepreneurship and moral & ethics የመሳሰሉትንም እንደሚያካትት ተገልጿል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ የTTLM ዝግጅት እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ ጀመረ።  🇪🇹የካቲት 14/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም ከፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት፣ በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፎች ላይ  የመማሪያ ማስተማሪያ ሞጁሎች (TTLM) ዝግጅት እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ በይፋ ማስጀመሩን አስታወቀ።ይህ የመማሪያ  ማስተማሪያ ሞጁሎች (TTLM) እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ በዋናነት የሚያተኩረው በሦስት ቁልፍ የስልጠና መስኮች ላይ ሲሆን እነሱም የሙዚቃ መሳሪያዎች አጠቃቀም ፣የድምፅ ስልጠና እና አትሌቲክስ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ። በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ የTTLM ዝግጅት እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ በዘርፉ የሚሰጠውን ስልጠና በጥራት ለመስጠትና የመማር ማስተማር ሂደትን በተሻለ መልኩ ለማሳለጥ የታለመ ተግባር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ።  የኮሌጁ አመራሮች እና የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪዎች እንደገለጹት፣ ይህ ተግባር ለመማር ማስተማር ሂደቱ ስኬታማነት እጅግ ወሳኝ እና ቁልፍ የሚባል ስራ እንደሆነና በተጨማሪም ነባር ካሪኩለሞችን ከወቅቱ የገበያ ፍላጎትና ከቴክኖሎጂ እድገት ጋር በማጣጣም፣ ሰልጣኞች ብቁና ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑ  ይሕ የTTLM ዝግጅትና የካሪኩለም የሪቪዥን ስራ የሰልጣኞችን ተግባራዊ ክህሎት ከማሳደጉ ባለፈ፣ በዘርፉ ያለውን የማስተማር ስታንዳርድ ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል" ሲሉ  የዝግጅቱ አስተባባሪዎች  ገልፀዋል። በ EASE ፕሮጀክት አስተባባሪነት የሚከናወነዉ ይህ መጠነ-ሰፊ የዝግጅት ስራ በEASE (Education and skill for employeblity) ፕሮጀክት ሙሉ ድጋፍ የሚከናወን ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ የክህሎት ልማትን ለማቀናጀትና የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን አቅም ለመገንባት እና የትምህርት ጥራትን ለመጠበቀ ከሚሰራው ስራ አንዱ አካል ነው።በተጨማሪም ከዚህ በፊት ያልተካተቱ ማለትም Digital skill ;Green skill ; Entrepreneurship and moral & ethics የመሳሰሉትንም እንደሚያካትት ተገልጿል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ የTTLM ዝግጅት እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ ጀመረ።  🇹የካቲት 02/2018 ዓ.ም🇪 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም ከፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመቀናጀት፣ በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፎች ላይ  የመማሪያ ማስተማሪያ ሞጁሎች (TTLM) ዝግጅት እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ በይፋ ማስጀመሩን አስታወቀ።ይህ የመማሪያ  ማስተማሪያ ሞጁሎች (TTLM) እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ በዋናነት የሚያተኩረው በሦስት ቁልፍ የስልጠና መስኮች ላይ ሲሆን እነሱም የሙዚቃ መሳሪያዎች አጠቃቀም ፣የድምፅ ስልጠና እና አትሌቲክስ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ። በኤስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ የTTLM ዝግጅት እና የካሪኩለም ክለሳ ስራ በዘርፉ የሚሰጠውን ስልጠና በጥራት ለመስጠትና የመማር ማስተማር ሂደትን በተሻለ መልኩ ለማሳለጥ የታለመ ተግባር እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል ።  የኮሌጁ አመራሮች እና የEASE ፕሮጀክት አስተባባሪዎች እንደገለጹት፣ ይህ ተግባር ለመማር ማስተማር ሂደቱ ስኬታማነት እጅግ ወሳኝ እና ቁልፍ የሚባል ስራ እንደሆነና በተጨማሪም ነባር ካሪኩለሞችን ከወቅቱ የገበያ ፍላጎትና ከቴክኖሎጂ እድገት ጋር በማጣጣም፣ ሰልጣኞች ብቁና ተወዳዳሪ ሆነው እንዲወጡ ለማስቻል ያለመ መሆኑ  ይሕ የTTLM ዝግጅትና የካሪኩለም የሪቪዥን ስራ የሰልጣኞችን ተግባራዊ ክህሎት ከማሳደጉ ባለፈ፣ በዘርፉ ያለውን የማስተማር ስታንዳርድ ወደ ላቀ ደረጃ ያሸጋግረዋል" ሲሉ  የዝግጅቱ አስተባባሪዎች  ገልፀዋል። በ EASE ፕሮጀክት አስተባባሪነት የሚከናወነዉ ይህ መጠነ-ሰፊ የዝግጅት ስራ በEASE (Education and skill for employeblity) ፕሮጀክት ሙሉ ድጋፍ የሚከናወን ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ የክህሎት ልማትን ለማቀናጀትና የቴክኒክና ሙያ ተቋማትን አቅም ለመገንባት እና የትምህርት ጥራትን ለመጠበቀ ከሚሰራው ስራ አንዱ አካል ነው።በተጨማሪም ከዚህ በፊት ያልተካተቱ ማለትም Digital skill ;Green skill ; Entrepreneurship and moral & ethics የመሳሰሉትንም እንደሚያካትት ተገልጿል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content

photo content
+7