1 146
订阅者
无数据24 小时
-37 天
-1830 天
帖子存档
1 145
ዕለተ ሰኞ ግንቦት 28/2016ዓ.ም
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሴቶችን የማነቃቃትና የማብቃት ስልጠና መስጠት ተጀመረ።
በአገራችን 50+1 ቁጥር ያላቸው ሴቶች መሆናቸው በተለያዩ ግዚያት የሚወጡ መረጃዎች ያመላክታሉ ። የመንግስት ተቋማትን ብቻ በምሳሌነት ቢወሰድ እንኳን ተሳትፏቸዉ ከአማካይ በታች ለመሆኑ እማኝ መጥቀስ አስፈላጊ አይመስልም። ከጥቅል ተሳትፎ ባሻገር በአመራር ቦታወዏች ያላቸውን ተሳትፎ ቢወሰድ ደግሞ ኢፍትሃዊ የመሆኑ አውነት አከራካሪ አይደለም ።
የሴቶች ተሳትፎ ማነስ ከመብት አለ መከበር ጋር ብቻ የተያያዘ ሳይሆን ከምርታማነት እና ዘላቂ ልማት ለማረጋጥ በሚደረገው ጥረት አሉታዊ ተፅእኖ እንደሚኖረው የሥነ ጾታ የጥናት ግኝቶች ይጠቁማሉ።
ይህንን ክፍተት ለመሙላት ሴቶችን ማነቃቃትና ማብቃት ምርጫ ብቻ ሊሆን አይችልም። ይህንን እውነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኰሌጅ ለሦስት ቀናት የሚዘልቅ ሥልጠና በኰሌጁ የአመራር እርከኖች ላሉ ሴት ሠራተኞች በመስጠት ላይ ይገኛል።
የስልጠናውን ዓላማ በተመለከተ :-
- በኮሌጃችን በተለያየ ደረጃ ያሉ ሴት አመራሮች በራስ የመተማመን አቅም ለማጎልበት እና በሂደት ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እንዲሁም ተተኪ ሴት አመራሮችን ለማፍራት የሚያስችል /የሚያግዝ መሆኑን
- በተሰማራንበት የስራ መስክ ውጤታማ ለመሆን የሚያስችል መሆኑን ስልጠናውን ያዘጋጁት የኮሌጃችን አሠልጣኝ ወ/ሮ ያለምወርቅ በቀለ አስረድተዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
ግንቦት /2016ዓ.ም
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆ ለአሠልጣኞች እና የአስተዳደር ሰራተኞች የካይዘን እና አረንጓዴ ቴክኒክና ሙያ/GREEN TVET ስልጠና ተሰጠ ።
ከግንቦት19-24/9/2016ዓ.ም የተቋማት አቅም ግንባታ ባዘጋጀው የካይዘን እና አረንጓዴ ቴክኒክና ሙያ/GREEN TVET ስልጠና የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በኮሌጁ የተቋማት አቅም ግንባታ ም/ዲን አቶ በላይ ከፋለ ስልጠናው በተለያዩ ግዚያት የተሰጠ ቢሆንም በየግዜው የማነቃቃት ስራዎችን ለመስራት እና ኮሌጁ ለሚተገብረው የ"ISO 21001:2018 Educational quality management system" ትግበራን እውን ለማድረግ አጋዥ እንዲሆን የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ጠቁመው መልካም የስልጠና ግዜን ተመኝተዋል።
የካይዘን ስልጠናን የሰጡት በካይዘን ልህቀት ማእከል የካይዘን ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ገ/ህይወት ገ/ሚካኤል የስልጠና ሂደቱን አስመልክተው በቀደሙት ግዚያት ተመሳሳይ ስልጠናዎችን በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የሰጡ መሆናቸውን አስታውሰው የዕለቱን ስልጠና ዋና ዓላማ ሲያብራሩ :-
የስራ ቦታ የትብብር ጽንሰ ሃሳብ፣
የስራ ቦታ ትብብር አስፈላጊነት፣
የስራ ቦታ የትብብር መንፈስን እንዴት እናመጣለን?
የተግባቦት እንቅፋቶችን ማስወገድ፣
የስራ ቦታ ተግባቦትን ለማሳደግ መደረግ ስላለባቸው ጉዳዮች በሰፊው አብራርተዋል።
በተመሳሳይ አረንጓዴ ቴክኒክና ሙያ/GREEN TVET በአቶ በላይ ከፋለ እና በአቶ ወ/ሰንበት በሬቻ የቀረበ ሲሆን ኮሌጃችን በአረንጓዴ ልማት የበለፀገ ምቹ የስራ አካባቢ መፍጠር ፣መመሪያን ተግባራዊ በማድረግ ስራና አሰራርን አረንጓዴ ከማድረግ ባሻገር የመጪውን ትውልድ ፍላጎት የሚያሟላ እንዲሆን የትምህርት ካሪክለሙ/ OS በታዳሽ ሃይል ፈጠራና አጠቃቀም መቃኘት እንደሚገባው ተጠቁሟል።
በየዘርፉ ተመጋጋቢ የሆኑ ስራዎችን በመስራት
ስልጠናው ኢኮሎጂካል ኢኮኖሚን ለመፍጠር የሚያስችል ጽንሰ ሃሳብ በማስጨበጥ አረንጓዴ የስልጠና መስክ ታዳሽና አረንጓዴ ተቋማትን ለመፍጠር የሚያስችል መሆን ይጠበቅበታል።
ኢኮሎጂካል ኢኮኖሚን ለመፍጠር የሚያስችል ጽንሰ ሃሳብ ማስረጽ ፣አረንጓዴ ቴክኖሎጂዎችን በመፍጠር ታዳሽ ሃይልን የመጠቀም አቅጣጫ ማስጨበጥ ትኩረት ተሰጥቶ ሊሰራበት እንደሚገባ ተጠቁሟል።
ስልጠናው በባለ ሁለት መስተጋብር የተካሄደ ሲሆን በአቅራቢዎች ማጠቃለያ ሰጥቶበት ፕሮግራሙ ተጠናቋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
ግንቦት /2016ዓ.ም
በተለያዩ የሙያ መስኮች የክህሎት ውድድር ተካሄደ።
ከተማ አቀፍ 14ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት የተለያዩ ዝግጅቶች የሚካሄዱበት መሆኑ ይታወሳል፡፡ ከነዚህ ዝግጅቶች መካከል አንዱ የሆነው የክህሎት ውድድር ሲሆን በአሠልጣኞች፣በሠልጣኞች እና በአንቀሳቃሾች መካከል ይካሄዳል ፡፡የዚህ ውድድር ዋና ዓላማ የስልጠና ጥራትን ማሻሻል፣ አሠልጣኙና ሠልጣኙ ያሉበትን የክህሎት ደረጃ ለመለየትና ለማገዝ እንዲያስችል እንዲሁም ተነሳሽነትን በመፍጠር ስራ ፈጣሪነትና ተወዳዳሪነትን ማሳደግ ላይ ያለመ ነው።
በዚህ ውድድር የመወዳደርያ መስፈርቱን ያሟሉ አሰልጣኞች፣ሰልጣኞችና አንቀሳቃሾች በተለያየ የሙያ መስክ እና ደረጃ ተካሂዷል።
የዝግጅት ክፍላችንም ለተወዳዳሪዎች መልካም
ዕድልን ይመኛል!!
ኮሙኒኬሽን ቡድን
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
