1 145
订阅者
无数据24 小时
-37 天
-1830 天
帖子存档
1 145
ዕለተ ሐሙስ ግንቦት 22/2016ዓ.ም
ለስራ ፈላጊ ወጣቶች የኮምፒውተር ስልጠና መስጠት ተጀመረ፡፡
ከጉለሌ ክፍለ ከተማ የተውጣጡ ከ12ኛ ክፍል በታች የሆኑና ዕድሜያቸው 18-25 ዓመት የሆኑ ወጣቶች በጉለሌ ክ/ከተማ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ አማካኝነት የህይወት ክህሎት ስልጠና መውሰዳቸው ይታወሳል፡፡
በመቀጠልም የ6 ወራት የስራ ላይ ልምምድ/ በየዘርፋቸው በኢንደስትሪ ውስጥ የተግባር ስልጠናውን አጠናቀው ዳግም በኮሌጃችን ለ5 ቀናት የሚቆይ የኮምፒውተር ስልጠና በዛሬው ዕለት ተጀምሯል፡፡
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
ግንቦት 22/2016 ዓ.ም
በ"ISO 21001:2018 Educational quality management system" ቅድመ ትግበራ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡
"ISO 21001:2018 Educational quality management system"ን አስመልክቶ በተለያዩ ግዚያት ለኮሌጁ ማህበረሰብ በተለያየ ደረጃ የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረኮች መመቻቸታቸው ይታወሳል፡፡ በዛሬው ዕለትም የኮሌጁ ማኔጅመንት፣ አካዳሚክ ከሚሽን እና ቡድን መሪዎች በጋራ በቅድመ ትግበራ ዝግጅት ላይ በጋራ የውይይት መድረክ አካሂደዋል፡፡
በተያያዘም በተጠናከረ መልኩ የተለያዩ የሰነድ ዝግጅቶች እና በየስራ ዘርፉ ሰነዶቹን አስመልክቶ መወያትና የማፀደቅ ስራዎችም መሰራታቸውን አስታውሰው በዛሬው ዕለት በተካሄደው የጋራ መድረክ አጠቃላይ ስራው የደረሰበትን ደረጃ እና ትኩረት የሚሹ፣ያጋጠሙና ሊያጋጥሙ የሚችሉ ጉዳዮችን አስመልክተው የቡድኑ አስተባባሪ አቶ ሚካኤል ጎኣ በሁለትዮሽ የታጀበ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
በቀረበው ማብራሪያና ሰነድ ላይ ውይይት ያደረጉ ተሳታፊዎች ቢጨመሩ፣ ቢስተካከሉ ያሏቸውን ሃሳብ በማንሳት ውይይት ተካሂዷል ፡፡
በተጨማሪም ትኩረት የሚሹና በአፋጣኝ መተግበር ስላለባቸው ስራዎችም አቅጣጫ በማስቀመጥ የዕለቱ ውይይት ተጠናቋል፡፡
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
የተቋም ምዘና ተሰጠ
በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ስልጠና ዘርፍ የ2016 ዓ.ም አዲስ ገቢ ሰልጣኞች በH.N.S /Hardware and Networking service , W.D.D.B.A /wave multimedia and Database adminstration በደረጃ አንድ የሰለጠኑ ሰልጣኞች የተቋም ምዘና/COC ደረጃውን ጠብቆ በትምህርት ክፍሉ ተዘጋጅቶ በሰልጣኝ ልማት ፀድቆ ከዕለት 19/9/2016ዓ.ም -21/9/2016 ዓ.ም የተሰጠ ሲሆን ለምዘና ከተቀመጡት 63ተመዛኞች መካከል 48ቱ ውጤታማ በመሆን ወደቀጣዩ ደረጃ የተሸጋገሩ ሲሆን ምዘናውን ያላለፉት በቀጣይ ለአንድ ሳምንት የሚቆይ የክህሎት ክፍተት መሙያ /ማጠናከሪያ ተሰጥቷቸው በድጋሚ የሚመዘኑ መሆናቸውን የትምህርት ክፍሉ ተጠሪ ወ/ሮ መሠረት ተሾመ ያሰረዳሉ ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
ለኮሌጁ አሰልጣኞች በሙሉ
ዛሬ 21/9/2016 ዓ.ም የካዘን ስልጠና በወጣው ፕሮገራም መሰረት ስልጠናው የሚሰጥ ሲሆን ከቀኑ 7፡30 በትልቁ አዳራሽ እንድትገኙ በድጋሜ እናሳስባለን
1 145
Check out our Latest News on the OFFICIAL website https://tmptc.edu.et/news/66555f59cf25e3d3ae13e201
1 145
ዕለተ ሰኞ ግንቦት 19/2016ዓ.ም
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆ ለአስተዳደር ሰራተኞች ለሁለት ቀናት የሚቆይ የካይዘን ስልጠና መስጠት ተጀመረ ።
የተቋማት አቅም ግንባታ ባዘጋጀው የካይዘን ስልጠና ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በኮሌጁ የተቋማት አቅም ግንባታ ም/ዲን አቶ በላይ ከፋለ ስልጠናው በተለያዩ ግዚያት የተሰጠ ቢሆንም በየግዜው የማነቃቃት ስራዎችን ለመስራት እና ኮሌጁ ለሚተገብረው የ"ISO 21001:2018 Educational quality management system" ትግበራን እውን ለማድረግ አጋዥ እንዲሆን የተዘጋጀ ስልጠና መሆኔን ጠቁመው መልካም የስልጠና ግዜን ተመኝተዋል። ስልጠናውን የሰጡት በካይዘን ልህቀት ማእከል የካይዘን ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ገ/ህይወት ገ/ሚካኤል የስልጠና ሂደቱን አስመልክተው በቀደሙት ግዚያት ተመሳሳይ ስልጠናዎችን በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች የሰጡ መሆናቸውን አስታውሰው የዕለቱ ስልጠና ዋና ዓላማ ሲያብራሩ :-
የስራ ቦታ የትብብር ጽንሰ ሃሳብ፣
የስራ ቦታ ትብብር አስፈላጊነት፣
የስራ ቦታ የትብብር መንፈስን እንዴት እናመጣለን?
የተግባቦት እንቅፋቶችን ማስወገድ፣
የስራ ቦታ ተግባቦትን ለማሳደግ መደረግ ስላለባቸው ጉዳዮች በሚል ዘርዝረዋል። ስልጠናው ባለ ሁለት መስተጋብር ሆኖ የተካሄደ ሲሆን ባለሙያው ማጠቃለያ ሰጥተውበት የዕለቱ ፕሮግራም ተጠናቋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
+3
ዕለተ ሰኞ ግንቦት 19/2016ዓ.ም
የቴክኒክና ሙያ ሳምንትን ምክንያት በማድረግ
ስፖርታዊ ውድድሮች ይካሄዳሉ።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስራና ክህሎት ቢሮ ለ14ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት በደማቅ ሁኔታ እንዲከበር የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተሳትፎውን በማጠናከር ላይ ይገኛል።
ኮሌጁን ወክለው በእግር ኳስ ስፖርት ውድድር ለሚሳተፉ እስፖርተኞች የእግር ኳስ መጫወቻ ጫማ ድጋፍ በኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ተበርክቶላቸዋል።
በርክክቡ ሥነ-ስርዓት ተወዳዳሪዎችን የሚያበረታታ ንግግር ከማድረጋቸውም ባሻገር መልካም ዕድል ተመኝተውላቸዋል።
የእግር ኳስ ስፖርት ውድድሩ በነገው ዕለት ግንቦት 20/2016ዓ.ም ከጠዋቱ 3:00 በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በየካ ኢንደስትሪያል ኮሌጅ ሜዳ ላይ እንደሚካሄድ ከወጣው መርሃ ግብር ለማወቅ ተችሏል።
በዚሁ አጋጣሚ የኮሌጁ ማህበረሰብ በቦታው ተገኝቶ ቡድኑን እንዲያበረታታ መልእክታችንን እያስተላለፍን
ለቡድናችን መልካም ውጤትን እንመኛለን።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
የቤዝ ሙዚቀኛ (ቤዚስት) ሔኖክ ተመስገን የተሳካ ሙያዊ የዕውቀት ሽግግር አደረገ ።
የእንጦጦ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሥነ-ውበት ትምህርት ክፍል ማስተማር ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ ከመደበኛው የመማር ማስተማር ሂደት ባሻገር በስሩ ባሉ የትምህርት ክፍሎች ለሰልጣኞች መነቃቃትን ይፈጥር ዘንድ አንቱታን ያተረፉ በሥነ-ጥበብ ዘርፉ አንጋፋ ባለሙያዎችን በመጋበዝ የሕይወትና የሥራ ልምዳቸውን እንዲያካፍሉ በማድረግ መዝለቁ ይታወሳል። በመሆኑም በስነ-ውበት ስልጠና ዘርፍ በሙዚቃ ትምህርት ክፍል እንግዳ በመሆን የተጋበዘው ዓለማቀፍ የቤዝ ሙዚቀኛ (ቤዚስት) ሔኖክ ተመስገን ነው።
የዚህ ወር እንግዳ የሆነው ሄኖክ ተመስገን ከኢትዮጵያ እስከ አሜሪካ የሚዘረጋ በርካታ ስራዎችን የሰራ ብዙ ልምድ ያካበተ አንጋፋ ቤዚስት ነው። ተወልዶ ያደገው አዲስ አበባ ሲሆን የሙዚቃ ፍቅር ካደረበት ማለትም የስምንተኛ ክፍል ተማሪ እያለ ጀምሮ የስዊድሽ ሚሽን ቸርች ውስጥ በኳየርነት ይዘምር፤ የሙዚቃ መሳርያ ይጫወት ነበር። ይህ በእንዲህ እንዳለ ወደ አሜሪካ ለትምህርት ባቀናበት ወቅት ከትምህርቱ ጎን ለጎን ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ባንድ በማቋቋም ሙዚቃ ይጫወቱ ነበር።
ወደ አሜሪካ በማቅናት ሲቪል ኢንጅነሪንግ ያጠና ቢሆንም የነብስ ጥሪው ሙዚቃ በመሆኑ በልምድ ከመጫወት ባሻገር በሙያው ስልጡን ለመሆን Berkeley College of music ለአምስት ዓመታት የዘለቀ ትምህርት ወስዷል። ከዚህም ባሻገር ጃዝ አንባ የተሰኘ የሙዚቃ ት/ቤት እና መዝናኛ ክለብ የነበረው ሲሆን በአሁን ወቅት በሸገር ሬድዮ ጣቢያ ላይ ከአስር ዓመት በላይ የዘለቀ ሙዚቃ ላይ ትኩረት ያደረገ የሬድዮ ዝግጅት አለው። በተጨማሪም ያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት መምህር በመሆን እያገለገለ ይገኛል።
ባለሙያው ከነሙሉ ባንዱ በኮሌጃችን በስነ ውበት የስልጠና ዘርፍ በሙዚቃ ትምህርት ክፍል በመገኘት ለደረጃ 3 ሰልጣኞች እና አሰልጣኞች ሙያዊ ዕውቀቱንና ክህሎቱን እንደዚሁም ልምዱን አካፍሏል/አጋርቷል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 145
+3
ዕለተ ሐሙስ ግንቦት 8/2016 ዓ.ም
ተግባራዊ ጥናትና ምርምር (Action research) ውድድር ተካሄደ።
በትናንትናው ዕለት ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር የተካሄደ ሲሆን ውድድሩ ላይ የስለጠና ዘርፍ ሀላፊዎች፣ የጥናትና ምርምር አወዳዳሪዎችና ተወዳዳሪ አሰልጣኞች በተገኙበት አራዳ መኒፍክቸሪንግን ጨምሮ ስድስት ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ለውድድር ቀርቧል።
የውድድሩ ዓላማ ኮሌጆች በስልጠና እና በኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን እንዲሁም በቴክኖሎጂ ሽግግር ዙርያ የአሰራር ስርአታቸውን ለማዘመንና ቀልጣፍ አገልግሎት መስጠት ያስችላቸው ዘንድ መነሳሳትን መፍጠርና ከዚህም ባሻገር በኮሌጆች ውስጥ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን መፍታት የሚያስችል አቅም መፍጠር ላይ ያለመ ነው።
በዚህም በዛሬው ዕለት በተካሄደው የክላስተር ውድድር በትናንትናው ዕለት ከቀረበው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውስጥ 1ኛ የወጣው በክላስተር ደረጃ የሚወዳደር ሲሆን ከዚህ ውድድር አንደኛ የሚወጣው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር በቀጣይ በከተማ እና በተዋረድ በሀገር አቀፍ ጀረጃ የሚቀርብ መሆኑን የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ዲን አቶ ወንድምሲያምረኝ መኮንን ገልፀዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
