1 149
订阅者
无数据24 小时
-37 天
-1830 天
帖子存档
1 149
ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ።
16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አስመልክቶ በኮሌጅ ደረጃ የሚደረገዉ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ዉድድር ተካሄደ ።
🇪🇹የካቲት 20/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አስመልክቶ የሚደረገዉ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ዉድድር በኮሌጅ ደረጃ ዳኞች እንዲሁም ከስራና ክህሎት ታዛቢዎች በተገኙበት ተካዶዋል። በዉድድሩም አራት የተግባራዊ ጥናትና ምርምር በአራት የስልጠና ዘርፎች በከተማ ግብርና ፣ በቴክስታይል ጋርመንት፣ በኤክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ እንዲሁም በኮንስትራክሽን ስልጠና ዘርፎች በአሰልጣኞች የተሰሩ ናቸዉ።
በውድድሩ ማጠቃለያ በዳኞች ከፍተኛ ነጥብ በማግኘት ወደ ክላስተር ለሁለተኛ ዙር ውድድር የሚላከው የተግባራዊ ጥናት ይፋ ተደርጓል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አስመልክቶ በኮሌጅ ደረጃ የሚደረገዉ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ዉድድር ተካሄደ ።
🇪🇹የካቲት 20/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት አስመልክቶ የሚደረገዉ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ዉድድር በኮሌጅ ደረጃ ዳኞች እንዲሁም ከስራና ክህሎት ታዛቢዎች በተገኙበት ተካዶዋል። በዉድድሩም አራት የተግባራዊ ጥናትና ምርምር በአራት የስልጠና ዘርፎች በከተማ ግብርና ፣ በቴክስታይል ጋርመንት፣ በኤክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ እንዲሁም በኮንስትራክሽን ስልጠና ዘርፎች በአሰልጣኞች የተሰሩ ናቸዉ።
በውድድሩ ማጠቃለያ በዳኞች ከፍተኛ ነጥብ በማግኘት በከተማ ግብርና ስልጠና ዘርፍ የቀረበው ጥናት አሸናፊ ሆኗል። "Enhancing milk yield through hydroponic fodder supplementation in TMPTC dairy farm" በሚል ርዕስ በአሰልጣኞች የቀረበው ይህ ጥናት፣ በሃይድሮፖኒክስ ዘዴ የሚመረት መኖ የወተት ምርትን ለመጨመር ያለውን ከፍተኛ ፋይዳ በተግባር በማሳየቱ አንደኛ በመውጣት ለቀጣዩ የክላስተር ውድድር ያለፈ ሆኗል ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በኪነጥበብና በሙዚቃ ተማሪዎች የተዘጋጀ የኪነጥበብ ፕሮግራም ።
🇪🇹የካቲት 20/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኪነጥበብና የሙዚቃ ተማሪዎች በጋራ በመሆን ያዘጋጁት ልዩ የኪነጥበብ መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት በኮበተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሌጁ አዳራሽ በድምቀት ተካሂዷል።
በዕለቱ ከቀረቡት ስራዎች መካከል በአቶ አንዷለም አባተ ተደርሶ በኪነጥበብ ተማሪዎች የቀረበው "የሞት ቀጠሮ" የተሰኘው የመድረክ ቲያትር የአዳራሹን ታዳሚ ቀልብ የገዛና ከፍተኛ አድናቆት የተቸረው ስራ ነበር። ድራማው በተማሪዎቹ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበትና የኪነጥበብ ክህሎታቸውን ያሳዩበት ሆኖ አልፏል።
ከመድረክ ድራማው በተጨማሪም፣ የሙዚቃ ተማሪዎች የተለያዩ ጣዕመ ዜማዎችን በመሳሪያና በድምፅ በማዋሃድ ለመርሃ-ግብሩ ልዩ ድምቀት ሰጥተውታል። ዝግጅቱ በተማሪዎች መካከል ያለውን የፈጠራ አቅም ከማሳየቱም በላይ፣ የኮሌጁ የኪነጥበብ ዘርፍ እያሳየ ያለውን እድገት የሚያንፀባርቅ እንደነበር ታውቋል።
በመጨረሻም የዝግጅቱ ታዳሚዎችና የኮሌጁ ማህበረሰብ በተማሪዎቹ ብቃት መደሰታቸውን ገልጸው፣ መሰል መርሃ-ግብሮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ፍላጎታቸውን ገልጸዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሶስት ዙር የሰለጠኑ ከ2420 በላይ የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች በንግድ ስራ ዘርፍ አሰልጥኖ አስመረቀ፡፡
🇪🇹የካቲት 20/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔትና የስራ ፕሮጀክት የምግብ ዋስትና ፕሮግራም ተጠቃሚዎችን ወደ ዘላቂ የኑሮ ማሻሻያ ፕሮግራም ለማሸጋገር ስልጠና በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በሽሮሜዳ ካምፓስ በሶስት ዙር ለ2420 ሰልጣኞች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ ።
የስልጠና ማጠቃለያና የምረቃ ፕሮግራም ላይ የጉ/ክ/ከ የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ፣ የጉ/ክ/ከ የወረዳ 02 የስራና ክህሎት እና የኮሌጁ ተወካዬች በተገኙበት ተካሂዷል ።እንደሚታወቀው ስልጠናው በሶስት ዙር ለተከታታይ አምስት ቀናት በዋናነት በንግድ ስራ ክህሎት፣ በንግድ እቅድ አዘገጃጀት እና በስራ ፍለጋ ስልቶች ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ሰልጣኞች ተደራጅተው ወደ ስራ መግባት እዳለባቸው ተገልጿል ።
የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት እና ስራ ፕሮጄክት ተጠቃሚዎች ኑሮ በዘላቂነት ለማሻሻል ስኬታማ ሥራ በመሥራት ወደ አምራችነት እንዲሸጋገሩ የቁጠባ እና የስራ ባህል ይበልጥ በማሳደግ በመረጡት የሥራ ዘርፍ ለመሰማራት በሚያደርጉት ጥረት መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል ።
ስልጠናውን ላጠናቀቁም ሰልጣኞች የጉ/ክ/ከ የምግብ ዋስትና የሴፍትኔት አስተባባሪ ዶ/ር አብነው ቦጋለ በኩል ሰርተፍኬት የመስጠት ፕሮግራም ተኸናውኗል ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በእቅድ ዝግጅትና መልካም አስተዳደር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
🇪🇹የካቲት 19/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋሙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ለተከታታይ ሦስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው በእቅድ አዘገጃጀትና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በስኬት ተጠናቀቀ።
በስልጠና ላይ የኮሌጁ ዲኖች፣ የአካዳሚክ ኮሚሽን አባላት፣ የውስጥ ሱፐርቫይዘር ኮሚቴዎች፣ ዳይሬክቶሬቶች እና የቡድን መሪዎች ተሳትፈዋል። የስልጠናው ዋነኛ ትኩረት ተቋማዊ አሰራርን በማዘመን፣ ውጤት ተኮር እቅዶችን በመንደፍና ፍትሃዊ የአገልግሎት አሰጣጥን በማስፈን ላይ ያተኮረ ነበር።
ውጤት ተኮር የእቅድ ዝግጅት ሊለኩ የሚችሉና በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ውጤት የሚያመጡ እንዲሆኑ የሚያስችል ግንዛቤ ከአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስ በመጡ አሰልጣኝ ወንደሰን ሞገስ በተጨማሪም አቶ አለምነህ ዋሴ በኩል ተፈጥሯል።
ከከንቲባ ጽ/ቤት የመልካም አስተዳደርናእና የቅሬታ ሰሚ ቡድን መሪ በሆኑት አቶ ዋሲሁን በላይ በስፋት ገለፃ የተሰጠበት ሲሆን ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትንና የህግ የበላይነትን በማስፈን የተገልጋዮችን እርካታ ማሳደግ እንደሚገባ አጽንኦት ተሰጥቶበታል። የውስጥ ሱፐርቫይዘር ኮሚቴዎችና የቡድን መሪዎች የታቀዱ ስራዎችን አፈጻጸም በየወቅቱ በመገምገም፣ ክፍተቶችን በመለየትና ፈጣን የማስተካከያ እርምጃዎችን በመውሰድ ረገድ ያላቸው ሚና በዝርዝር ቀርቧል።
የኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በሰጡት አስተያየት የተገኘው ግንዛቤ በቀጣይ ለሚከናወኑ የኮሌጁ የልማትና የመማር ማስተማር ስራዎች የጎላ ፋይዳ እንዳለው ገልጸው፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ሰንሰለቱን በማሳጠር ለተማሪዎችና ለሰራተኞች ቀልጣፋ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ኮሌጁ መሰል የአቅም ግንባታ ስራዎችን በማጠናከር፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ተገልጿል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኪነጥበብና በሙዚቃ ተማሪዎች የተዘጋጀ የኪነጥበብ ፕሮግራም ።
🇪🇹የካቲት 20/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኪነጥበብና የሙዚቃ ተማሪዎች በጋራ በመሆን ያዘጋጁት ልዩ የኪነጥበብ መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት በኮሌጁ አዳራሽ በድምቀት ተካሂዷል።
በዕለቱ ከቀረቡት ስራዎች መካከል በአቶ አንዷለም አባተ ተደርሶ በኪነጥበብ ተማሪዎች የቀረበው "የሞት ቀጠሮ" የተሰኘው የመድረክ ቲያትር የአዳራሹን ታዳሚ ቀልብ የገዛና ከፍተኛ አድናቆት የተቸረው ስራ ነበር። ድራማው በተማሪዎቹ ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበትና የኪነጥበብ ክህሎታቸውን ያሳዩበት ሆኖ አልፏል።
ከመድረክ ድራማው በተጨማሪም፣ የሙዚቃ ተማሪዎች የተለያዩ ጣዕመ ዜማዎችን በመሳሪያና በድምፅ በማዋሃድ ለመርሃ-ግብሩ ልዩ ድምቀት ሰጥተውታል። ዝግጅቱ በተማሪዎች መካከል ያለውን የፈጠራ አቅም ከማሳየቱም በላይ፣ የኮሌጁ የኪነጥበብ ዘርፍ እያሳየ ያለውን እድገት የሚያንፀባርቅ እንደነበር ታውቋል።
በመጨረሻም የዝግጅቱ ታዳሚዎችና የኮሌጁ ማህበረሰብ በተማሪዎቹ ብቃት መደሰታቸውን ገልጸው፣ መሰል መርሃ-ግብሮች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ፍላጎታቸውን ገልጸዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሶስት ዙር የሰለጠኑ ከ2400 በላይ የሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች በንግድ ስራ ዘርፍ አሰልጥኖ አስመረቀ፡፡
🇪🇹የካቲት 20/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔትና የስራ ፕሮጀክት የምግብ ዋስትና ፕሮግራም ተጠቃሚዎችን ወደ ዘላቂ የኑሮ ማሻሻያ ፕሮግራም ለማሸጋገር ስልጠና በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በሽሮሜዳ ካምፓስ በሶስት ዙር ለ2420 ሰልጣኞች ሲሰጥ የቆየው ስልጠና ተጠናቀቀ ።
የስልጠና ማጠቃለያና የምረቃ ፕሮግራም ላይ የጉ/ክ/ከ የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ፣ የጉ/ክ/ከ የወረዳ 02 የስራና ክህሎት እና የኮሌጁ ተወካዬች በተገኙበት ተካሂዷል ።እንደሚታወቀው ስልጠናው በሶስት ዙር ለተከታታይ አምስት ቀናት በዋናነት በንግድ ስራ ክህሎት፣ በንግድ እቅድ አዘገጃጀት እና በስራ ፍለጋ ስልቶች ዙሪያ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና የተሰጠ ሲሆን ሰልጣኞች ተደራጅተው ወደ ስራ መግባት እዳለባቸው ተገልጿል ።
የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት እና ስራ ፕሮጄክት ተጠቃሚዎች ኑሮ በዘላቂነት ለማሻሻል ስኬታማ ሥራ በመሥራት ወደ አምራችነት እንዲሸጋገሩ የቁጠባ እና የስራ ባህል ይበልጥ በማሳደግ በመረጡት የሥራ ዘርፍ ለመሰማራት በሚያደርጉት ጥረት መንግስት አስፈላጊውን ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል ።
ስልጠናውን ላጠናቀቁም ሰልጣኞች የጉ/ክ/ከ የምግብ ዋስትና የሴፍትኔት አስተባባሪ ዶ/ር አብነው ቦጋለ በኩል ሰርተፍኬት የመስጠት ፕሮግራም ተኸናውኗል ።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በእቅድ ዝግጅትና መልካም አስተዳደር ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
🇪🇹የካቲት 19/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለተቋሙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ለተከታታይ ሦስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው በእቅድ አዘገጃጀትና በመልካም አስተዳደር ዙሪያ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በስኬት ተጠናቀቀ።
በስልጠና ላይ የኮሌጁ ዲኖች፣ የአካዳሚክ ኮሚሽን አባላት፣ የውስጥ ሱፐርቫይዘር ኮሚቴዎች፣ ዳይሬክቶሬቶች እና የቡድን መሪዎች ተሳትፈዋል። የስልጠናው ዋነኛ ትኩረት ተቋማዊ አሰራርን በማዘመን፣ ውጤት ተኮር እቅዶችን በመንደፍና ፍትሃዊ የአገልግሎት አሰጣጥን በማስፈን ላይ ያተኮረ ነበር።
ውጤት ተኮር የእቅድ ዝግጅት ሊለኩ የሚችሉና በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ውጤት የሚያመጡ እንዲሆኑ የሚያስችል ግንዛቤ ከአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስ በመጡ አሰልጣኝ ወንደሰን ሞገስ በተጨማሪም አቶ አለምነህ ዋሴ በኩል ተፈጥሯል።
ከከንቲባ ጽ/ቤት የመልካም አስተዳደርናእና የቅሬታ ሰሚ ቡድን መሪ በሆኑት አቶ ዋሲሁን በላይ በስፋት ገለፃ የተሰጠበት ሲሆን ግልጽነትን፣ ተጠያቂነትንና የህግ የበላይነትን በማስፈን የተገልጋዮችን እርካታ ማሳደግ እንደሚገባ አጽንኦት ተሰጥቶበታል። የውስጥ ሱፐርቫይዘር ኮሚቴዎችና የቡድን መሪዎች የታቀዱ ስራዎችን አፈጻጸም በየወቅቱ በመገምገም፣ ክፍተቶችን በመለየትና ፈጣን የማስተካከያ እርምጃዎችን በመውሰድ ረገድ ያላቸው ሚና በዝርዝር ቀርቧል።
የኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በሰጡት አስተያየት የተገኘው ግንዛቤ በቀጣይ ለሚከናወኑ የኮሌጁ የልማትና የመማር ማስተማር ስራዎች የጎላ ፋይዳ እንዳለው ገልጸው፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ሰንሰለቱን በማሳጠር ለተማሪዎችና ለሰራተኞች ቀልጣፋ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።
ኮሌጁ መሰል የአቅም ግንባታ ስራዎችን በማጠናከር፣ የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥና ተወዳዳሪ ዜጎችን ለማፍራት የሚያደርገውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥልም በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ ተገልጿል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
