Ethiopian Public Service University
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Ethiopian Public Service University 的分析概览
频道 Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 12 734 名订阅者,在 教育 类别中位列第 15 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 642 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 12 734 名订阅者。
根据 11 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 106,过去 24 小时变化为 3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 34.72%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.17% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 419 次浏览,首日通常累积 2 058 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 27。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት”
凭借高频更新(最新数据采集于 12 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。
12 734
订阅者
+324 小时
+207 天
+10630 天
帖子存档
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የሪፎርም ጉዞውን አስመልክቶ ውይይት አካሄደ
(መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም)
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢ.ፐ.ሰ.ዩ.) በአዲስ ተልእኮው የጀመረውን የሪፎርም ጉዞ አስመልክቶ እየተከናወኑ የሚገኙ የለውጥ ስራዎች ላይ ከዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ እና የአስተዳደር አመራሮችና ሰራተኞች ጋር በአባይ አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት አካሄደ፡፡
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ወደ ተግባር ተኮር ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ የሽግግር ጉዞ እና የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ማሻሻያ ሪፎርም በሚል ሁለት ክፍል የተጠናቀረውን ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን፣ በእያንዳንዱ ርእሰ ጉዳይ የሪፎርም ስራዎች ያሉበትን ደረጃ ዘርዝረዋል፡፡
ዶ/ር ንጉስ በሪፖርታቸው እንደገለጹት፣ የሪፎርም ስራዎቹን ለማከናወን የተደራጁ ኮሚቴዎች አብዛኞቹ ስራዎቻቸውን አጠናቀው ማስረከባቸውን እና የቀሩትም ለመጠናቀቅ የደረሱ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም የተጠናቀቁት የሪፎርም ስራዎቻችን ለትምህርት ሚኒስቴር እና ለሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ቀርበው እየተገመገሙ መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡
አስከትለውም የስርአተ-ትምህርት ክለሳ እና ቀረጻ የሪፎርሙ ትልቁ እና ዋናው ስራ መሆኑን ጠቅሰው፣ በዚህ ረገድ በርካታ ስራዎች በስፋት እተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል፤ እንዲሁም የሴኒት መተዳደሪያ ደንቡን ከተግባር ተኮር እና ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ አንጻር የመከለስ ስራ እተከናወነ የሚገኝ መሆኑን እና ሌሎችም አንኳር ስራዎች በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡
በቀጫይም መደበኛ የመማር ማስተማር እቅድ እና የተቀመጡትን ቁልፍ ውጤት አመላካቾች (KPIs) ማከናወን፣ የተጀመሩ ስትራቴጂያዊ የሪፎርም ሰነዶችን ማጠናቀቅ እና ማጸደቅ፣ ቀሪ የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ማሻሻያ የሪፎርም ስራዎችን ማጠናቀቅ እና ወደ ተሟላ ትግበራ መግባት በዚህ በጀት አመት መፈጸም ያለባቸው ስራዎች መሆናቸውን በአጽንኦት ገልጸዋል፡፡
በመጨረሻም ከቤቱ ለተነሱ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
+3
ኢ.ፐ.ሰ.ዩ አዲሱን ድረ ገጽ በይፋ ስራ አስጀመረ፤
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በኢኖቬሽን እና ዲጂታላይዜሽን ኮሌጅ (College of Innovation & Digitalization) አማካኝነት ያለማውን አዲሱን የዩኒቨርሲቲውን ድረ-ገጽ ዛሬ መጋቢት 4 ቀን 2018 ዓ.ም በአባይ አዳራሽ በተካሄደው መርሃ ግብር በይፋ ስራ አስጀመረ፡፡
ድረ ገጹን በይፋ ስራ ያስጀመሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ሲሆኑ፣ በመርሃ-ግብሩ ላይ እንደተናገሩት ድረ-ገጹ በመረጃም ሆነ በተደራሽነት በየጊዜው እየዳበረ የሚሄድ መሆኑን ገልጸው፣ በስራው ላይ የተሳተፉ የኮሌጁን መምህራን አመስግነዋል፡፡
በመቀጠልም የኢኖቬሽን እና ዲጂታላይዜሽን ኮሌጅ ዲን አቶ አለባቸው ጭጬ በአጠቃላይ ድረ- ገጹን ማልማት ከተጀመረበት እለት ጀምሮ እስካሁን የነበረውን ሂደት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ አስከትለውም፣ “የቀድሞው ድረ-ገጽ ተደራሽነቱ በጣም ደካማ የሆነ እና አስፈላጊ መረጃዎችን በተገቢው ሁኔታ ያላካተተ ከመሆኑም በላይ በየጊዜው ስለማይዘምን የማይጠቅሙ መረጃዎችን የያዘ ነበር፡፡” በማለት አሁን የለማው ድረ-ገጽ እነዚህን ችግሮች የሚቀርፍ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በመጨራሻም ድረ-ገጽን በማልማት ስራ ላይ ለተሰማሩ የኮሌጁ መምህራን የምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
+6
በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በልዩ ልዩ መርሃ- ግብሮች ተከበረ።
በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢ.ፐ.ሰ.ዩ) በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8) “የሴቶች ድምፅ ለእኩልነት እና ለበለፀገች ኢትዮጵያ'' በሚል መሪ ቃል፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃለፊዎች ፣ የዩኒቨርሲቲው ሴት ምሁራን፣ ሴት አመራሮች እና ሰራተኞች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በድምቀት አከበረ፡፡
በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በልዩ ልዩ መርሃ- ግብሮች ተከበረ።
በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢ.ፐ.ሰ.ዩ) በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8) “የሴቶች ድምፅ ለእኩልነት እና ለበለፀገች ኢትዮጵያ'' በሚል መሪ ቃል፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃለፊዎች ፣ የዩኒቨርሲቲው ሴት ምሁራን፣ ሴት አመራሮች እና ሰራተኞች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በድምቀት አከበረ፡፡
በበዓሉ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት ክብርት ወ/ሮ ሄለን ደበበ ፣ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ለታዳሚዎቹ ባደረጉት ንግግር “ዛሬ በዚህ አዳራሽ የተሰበሰብነው በዓሉን ለመዘከር ብቻ ሳይሆን፣ ባለፉት አምስት አስርት አመታት ውስጥ እናንተ ሴት ምሁራን በማህበረሰባችን ውስጥ የፈጠራችሁትን ጉልህ ለውጥ እና ያሳለፋችሁትን ፈታኝ የታሪከረ ጉዞ እውቅና ለመስጠት ነው፡፡” በማለት ኢትዮጵያውያን ሴቶች ያለፉበትን ፈታኝ ጉዞ አውስተዋል፡፡ በማስከተልም ከሴት ምሁራን የሚጠበቁ ትልልቅ ኃላፊነቶች መኖራቸውን ጠቅሰው፣ “ሴት ወጣቶችን በቃላት ብቻ ሳይሆን በተግባር የምታስተምሩ የሕይወት መጻሕፍት በመሆናችሁ፣ በማህበረሰባችን ውስጥ ስር የሰደዱና የሴቶችን ጉዞ የሚያደናቅፉ ጎጂ ልማዶችን በእውቀት የመታገል ትልቅ አደራ አለባችሁ፡፡” ብለዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ በመክፈቻው ንግግራቸው እንደተናገሩት፣ በየዓመቱ የሚከበረው ይህ በዓል በተለያዩ የሙያ መስክ እና በስራ አመራርነት ስኬታማ የሆኑ ሴቶች፣ እንዴት ስኬታማ እንደሆኑ ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት መሆኑ ከሌሎች በዓላት ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸው፣ “ከሁሉ በላይ ልዩ የሚያደርገው በቀጣይ ለሴቶች ምን መልካም አጋጣሚ አለ? ያንንስ አጋጣሚ እንዴት መጠቀም ይቻላል? የሚለው የሚመከርበት ቀን በመሆኑ ነው፡፡” ብለዋል፡፡
ቀጥሎም በዶ/ር ትህትና አያሌው ለሴት የዩኒቨርሲቲ ምሁራን መወያያ ሰነድ እና በዶ/ር አባይ አክማቸው “የኢትዮጵያ ሴቶች የ50 አመት የለውጥ ጉዞ እና የማርች 8 ታሪካዊ ፋይዳ” በሚል የተዘጋጀ ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡
በመጨረሻም በትምህርታቸውም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ሴት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችም የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል፡፡
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በልዩ ልዩ መርሃ- ግብሮች ተከበረ።
በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢ.ፐ.ሰ.ዩ) በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ50ኛ ጊዜ የሚከበረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8) “የሴቶች ድምፅ ለእኩልነት እና ለበለፀገች ኢትዮጵያ'' በሚል መሪ ቃል፣ ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃለፊዎች ፣ የዩኒቨርሲቲው ሴት ምሁራን፣ ሴት አመራሮች እና ሰራተኞች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና የስራ ኃላፊዎች በተገኙበት በድምቀት አከበረ፡፡
በበዓሉ ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት ክብርት ወ/ሮ ሄለን ደበበ ፣ የከተማ እና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ለታዳሚዎቹ ባደረጉት ንግግር “ዛሬ በዚህ አዳራሽ የተሰበሰብነው በዓሉን ለመዘከር ብቻ ሳይሆን፣ ባለፉት አምስት አስርት አመታት ውስጥ እናንተ ሴት ምሁራን በማህበረሰባችን ውስጥ የፈጠራችሁትን ጉልህ ለውጥ እና ያሳለፋችሁትን ፈታኝ የታሪከረ ጉዞ እውቅና ለመስጠት ነው፡፡” በማለት ኢትዮጵያውያን ሴቶች ያለፉበትን ፈታኝ ጉዞ አውስተዋል፡፡ በማስከተልም ከሴት ምሁራን የሚጠበቁ ትልልቅ ኃላፊነቶች መኖራቸውን ጠቅሰው፣ “ሴት ወጣቶችን በቃላት ብቻ ሳይሆን በተግባር የምታስተምሩ የሕይወት መጻሕፍት በመሆናችሁ፣ በማህበረሰባችን ውስጥ ስር የሰደዱና የሴቶችን ጉዞ የሚያደናቅፉ ጎጂ ልማዶችን በእውቀት የመታገል ትልቅ አደራ አለባችሁ፡፡” ብለዋል፡፡
በመርሃ ግብሩ ላይ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ በመክፈቻው ንግግራቸው እንደተናገሩት፣ በየዓመቱ የሚከበረው ይህ በዓል በተለያዩ የሙያ መስክ እና በስራ አመራርነት ስኬታማ የሆኑ ሴቶች፣ እንዴት ስኬታማ እንደሆኑ ልምዳቸውን የሚያካፍሉበት መሆኑ ከሌሎች በዓላት ልዩ እንደሚያደርገው ገልጸው፣ “ከሁሉ በላይ ልዩ የሚያደርገው በቀጣይ ለሴቶች ምን መልካም አጋጣሚ አለ? ያንንስ አጋጣሚ እንዴት መጠቀም ይቻላል? የሚለው የሚመከርበት ቀን በመሆኑ ነው፡፡” ብለዋል፡፡
ቀጥሎም በዶ/ር ትህትና አያሌው ለሴት የዩኒቨርሲቲ ምሁራን መወያያ ሰነድ እና በዶ/ር አባይ አክማቸው “የኢትዮጵያ ሴቶች የ50 አመት የለውጥ ጉዞ እና የማርች 8 ታሪካዊ ፋይዳ” በሚል የተዘጋጀ ጥናታዊ ጽሁፍ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡
በመጨረሻም በትምህርታቸውም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ሴት የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችም የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል፡፡
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
Congratulations!
Our journal, the African Journal of Leadership and Development (AJOLD), has been nationally accredited by the Ministry of Education as of March 2026 for a consecutive three-year period.
የኢፐሰዩ የአካዳሚክ እና አስተዳደርና ልማት ዘርፍ ምክትል ፕሬዚደንቶች ከተማሪዎች ጋር ተወያዩ
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ እና አስተዳደርና የልማት ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንቶች በአካዳሚያዊ እና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ከመደበኛ እና የተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎች ጋር የካቲት 26 ቀን 2018 ዓ/ም በአባይ አዳራሽ፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች እና ስራ አስፈጻሚዎች በተገኙበት ውይይት አደረጉ፡፡
የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንቱ ዶ/ር አማኑኤል ኩስያ በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት፣ “ከእናንተ ጋር በተደጋጋሚ የውይይት መድረክ የምናዘጋጀው፣ ከቤተሰቦቻችሁ በአደራ ስለተቀበልናችሁና እውቀትን፣ ክህሎትን እና መልካም ስነ-ምግባርን አስታጥቀን፣ ሙሉ ሰው አድርገን መልሰን ማስረከብ ስላለብን ነው፡፡” ብለዋል፡፡
የአስተዳደር እና ልማት ዘርፍ ምክትል ፕሬዝደንቱ ዶ/ር ተሸመ ዱላ በበኩላቸው፣ በአስተዳደር እና ልማት ዘርፍ ስር የሚገኙ ስራ አስፈጻሚዎች እና ሰራተኞች ባሉበት ውይይት ማድረግ፣ የሚነሱ ጥያቄዎችን በሚነገሩበት መጠን ለመረዳት እንደሚያስችል ገልጸው፣“ እኛ እዚህ ያለነው ችግሮችን ፈተን፣ የመማር ማስተማር ሂደቱን የተሳካ ለማድረግ ነው፡፡” ብለዋል፡፡
ቀጥሎም ከተማሪዎቹ አካዳሚያዊ እና አስተዳደራዊ ይዘት ያላቸው ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን፤ ከጥቄዎቹም መካከል የምግብ ሜኑ ማስተካከያ እንዲደረግ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ እንዲዘጋጅ፣ የጽዳት አገልግሎት እንዲሻሻል የሚሉ እና ሌሎችም ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡
በአካዳሚ ጉዳዩች ላይ ለተነሱት ጥያቄዎች የጋራ ኮርሶች ዲን የሆኑት ዶ/ር ተስፋዬ ጩፋና በሰጡት ማላሽ “ያነሳችኋቸውን አንዳንድ ማስተካከያዎች በተመለከተ በአጭር ጊዜ ተገቢዉን ምላሽ እንሰጣለን፤ ደንብን እና መመሪያን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ግን የትምህርት ሚኒስቴር በጥናት ላይ ተመስርቶ ያወጣቸው ስለሆኑ እነርሱን መሸራረፍ አንችልም፡፡” በማለት በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
የኢፐሰዩ የአካዳሚክ እና አስተዳደርና ልማት ዘርፍ ምክትል ፕሬዚደንቶች ከተማሪዎች ጋር ተወያዩ
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ እና አስተዳደርና የልማት ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንቶች በአካዳሚያዊ እና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ከመደበኛ እና የተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎች ጋር የካቲት 26 ቀን 2018 ዓ/ም በአባይ አዳራሽ፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች እና ስራ አስፈጻሚዎች በተገኙበት ውይይት አደረጉ፡፡
የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንቱ ዶ/ር አማኑኤል ኩስያ በውይይቱ ላይ እንደተናገሩት፣ “ከእናንተ ጋር በተደጋጋሚ የውይይት መድረክ የምናዘጋጀው፣ ከቤተሰቦቻችሁ በአደራ ስለተቀበልናችሁና እውቀትን፣ ክህሎትን እና መልካም ስነ-ምግባርን አስታጥቀን፣ ሙሉ ሰው አድርገን መልሰን ማስረከብ ስላለብን ነው፡፡” ብለዋል፡፡
የአስተዳደር እና ልማት ዘርፍ ምክትል ፕሬዝደንቱ ዶ/ር ተሸመ ዱላ በበኩላቸው፣ በአስተዳደር እና ልማት ዘርፍ ስር የሚገኙ ስራ አስፈጻሚዎች እና ሰራተኞች ባሉበት ውይይት ማድረግ፣ የሚነሱ ጥያቄዎችን በሚነገሩበት መጠን ለመረዳት እንደሚያስችል ገልጸው፣“ እኛ እዚህ ያለነው ችግሮችን ፈተን፣ የመማር ማስተማር ሂደቱን የተሳካ ለማድረግ ነው፡፡” ብለዋል፡፡
ቀጥሎም ከተማሪዎቹ አካዳሚያዊ እና አስተዳደራዊ ይዘት ያላቸው ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን፤ ከጥቄዎቹም መካከል የምግብ ሜኑ ማስተካከያ እንዲደረግ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራ እንዲዘጋጅ፣ የጽዳት አገልግሎት እንዲሻሻል የሚሉ እና ሌሎችም ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡
በአካዳሚ ጉዳዩች ላይ ለተነሱት ጥያቄዎች የጋራ ኮርሶች ዲን የሆኑት ዶ/ር ተስፋዬ ጩፋና በሰጡት ማላሽ “ያነሳችኋቸውን አንዳንድ ማስተካከያዎች በተመለከተ በአጭር ጊዜ ተገቢዉን ምላሽ እንሰጣለን፤ ደንብን እና መመሪያን የሚመለከቱ ጉዳዮችን ግን የትምህርት ሚኒስቴር በጥናት ላይ ተመስርቶ ያወጣቸው ስለሆኑ እነርሱን መሸራረፍ አንችልም፡፡” በማለት በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
በኢፐሰዩ የሴኔት መተዳደሪያ ረቂቅ የማሻሻያ ሰነድ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡
በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በመዘጋጀት ላይ በሚገኘው የሴኔት መተዳደሪያ ህግ /Senate Legislation/ ማሻሻያ ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡ የካቲት 19 ቀን 2018 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ ተደረገው በዚህ የውይይት መድረክ ላይም በተቋሙ የተቋቋመው የለውጥ ግብረ- ኃይል አባላት ተሳትፈዋል፡፡
በውይይቱ መክፈቻ ላይ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ደ/ር ንጉስ ታደሰ ባደረጉት ንግግር በዩኒቨርሲቲው እየተደረገ ያለውን ለውጥ ተከትሎ የተለያዩ ሰነዶች በመዘጋጀት ላይ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ በዘርፍ ደረጃ የሚታዩት በየዘርፋቸው እንዲገመገሙ የሚደረግ መሆኑንና ስትራቴጂያዊ ጉዳዮች ላይ የሚዘጋጁ ተቋማዊ ሰነዶችን ደግሞ በግብረ-ኃይሉ እና በሂደትም በየደረጃው በስፋት ታይተውና ውይይት ተደርጎባቸው ወደቀጣይ ምዕራፍ የሚሻገሩ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
ከእነዚህ ስትራቴጂያዊ ሰነዶች አንዱ የዩኒቨርሲቲው የሴኔት መተዳደሪያ መሆኑን የገለጹት ዶ/ር ንጉስ በሚቀርበው የማሻሻያ ረቂቅ ሰነድ ላይ ትኩረት ተደርጎበት መወያየት ተገቢ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም በተቋሙ አሁን እየተደረገ ያለው የለውጥ ሂደት ትግበራውንም አብሮ የማስኬድ ባህሪ ያለው መሆኑን በመጠቆም አሁን ባለንበት ሁኔታ ሰነዶችን አዘጋጅተንና አጽድቀን ወደ ተግባር የምንገባበት ሳይሆን የለውጥ ሰነዶችን እያዘጋጀን ፣ ወደትግበራው በመግባት ትግበራና ለውጥን አብረን ጎን ለጎን የምናስኬድበት ነው ብለዋል፡፡
የማሻሻያ ረቂቅ ሰነዱም በዶ/ር ዘላለም እጅጉ የቀረበ ሲሆን፣ ዶ/ር ዘላለም የማሻሻያው አስፈላጊነት ሲያብሩ ዩኒቨርሲቲው እየተመራበት ያለው የ2023 የሴኔት መተዳደሪያ መሆኑን ጠቅሰው፣ ይህ የመተዳደሪያ ደንብም አሁን ዩኒቨርሲቲው ካነገበው ራዕይና ተልዕኮ እንዲሁም ከምርምር ዩኒቨርሲቲነት ወደ ተግባራዊ ሳይንስ ዩኒቨርሲቲነት በተደረገው ለውጥ በተሰጠውን ተግባርና ኃላፊነት ጋር አብሮ ሊሄድ የማይችል በመሆኑ ክለሳ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚሁ መሰረትም በነበረው መተዳደሪያ ህግ ላይ የነበሩ በርካታ አወዛጋቢና አሁን ካለው ተጨባጭ ሁኔታ ጋር የማየሄዱ አንቀጾችና ድንጋጌዎች ላይ የተደረጉት ማሻሻያዎች በዝርዝር አቅርበዋል፡፡
በቀረበው ረቂቅ ማሻሻያ ሰነድ ላይም ከተሳታፊዎች የተለያዩ ትኩረት የሚሹ፣ ለረቀቂቅ ሰነዱ መሻሻል ግብዐት የሚሆኑ ሀሳብና አስተያየቶች ተሰጥተዋል፡፡ ሰነዱም ወደ ኮሌጆችና የትምህርት ክፍሎች ደርሶ ሁሉም የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እንዲወያይባቸውም ሀሳብና አስተያየት እንዲሰጥበት ሀሳብ ቀርቧል፡፡
በመጨረሻም ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ባደረጉት ማጠቃለያ ከተደረገው ውይይት ሰነዱን ለማዳበር ጠቃሚ የሆኑ ሀሳቦች መነሳታቸውን ጠቅሰው ሌሎች ብዙ ማሻሻያዎች ተደርጎበት መጎልበት ያለበት ሰነድ መሆኑን በአጽንኦት ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም “ይህ የሴኔት መተዳደሪያ ለዩኒቨርሲቲው ህገ- መንግስት ማለት በመሆኑ እንደገና በጥንቃቄ ታይቶ፣ ለተቋሙን የወደፊት ጉዞ መሰረት የሚጥል እና ተራማጅ የሆነ፣ መምህሩንም ሆነ ተማሪውን የሚያገለግል ሰነድ አድርገን ማዘጋጀት ይኖርብናል፡፡ ለዚህም ከኮሌጆችና ከመምህራን ጋር ደጋግመን የምንወያይበት እና የዩኒቨርሲቲውን ክብር በሚጠብቅ መልኩ የምናዘጋጃው ይሆናል::” ብለዋል፡፡
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/
Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt
PR call: 0945746405
Ethiopian Public Service University Joins Prestigious International Project to Modernize Public Sector Leadership
**********,,*********,,*******,,********,,**********
Caserta, Italy – A delegation from the Ethiopian Public Service University (EPSU), led by its President Dr. Nigus Tadesse, participated in the official launch of a major international capacity-building project held in Italy from February 10-12, 2026. The official launching ceremony took place on the morning of February 10 at the Royal Palace of Caserta, headquarters of Italy's National School of Administration (SNA-Scuola Nazionale dell'Amministrazione), followed by high-level professional meetings in Rome.
The project, titled "Strengthening the skills, expertise, and knowledge of senior public officials in Côte d'Ivoire, Ethiopia, Kenya, and Tunisia," was officially launched by Italy's Deputy Minister of Foreign Affairs and International Cooperation, Hon. Edmondo Cirielli, and the President of the SNA, Professor Paola Severino. With total funding of approximately €6.5 million, the initiative will provide training to senior public officials from the four participating countries in strategic areas critical to national development.
The ceremony brought together delegations from the four African pilot nations alongside representatives of key Italian institutions, including the Ministry of Foreign Affairs and International Cooperation, the Department of Public Administration of the Presidency of the Council of Ministers, the Italian Agency for Development Cooperation (AICS), and the Mattei Plan Mission Structure.
In his address, Deputy Minister Cirielli underscored Italy's commitment to the initiative, revealing its origins during the G7 high-level meeting on training that he chaired in Caserta in October 2024. "I strongly supported this project, which was conceived during the G7 high-level meeting on training that I chaired in October 2024 right here in Caserta, and I thank Minister Tajani for believing in the initiative," the Deputy Minister stated. Professor Paola Severino, President of the SNA, echoed this sentiment, affirming that the SNA was ready to seize the opportunity and, through collaboration with the Foreign Ministry and other partners, quickly implemented an initiative that could transform the Royal Palace of Caserta into an educational hub for Africa, within the framework of the Mattei Plan launched by President Meloni.
In his remarks, Dr. Nigus Tadesse emphasized the strategic importance of this collaboration for Ethiopia's on-going public sector modernization efforts. "The collaboration of Ethiopian Public Service University with Italy's National School of Administration is not only vital for Ethiopia's public sector modernization but also furthers the longstanding relationship between our two nations," Dr. Nigus stated. He highlighted that the project's comprehensive training areas, ranging from digital transformation, artificial intelligence (AI), and cybersecurity to public procurement, public policy, and debt management, directly align with Ethiopia's national strategic priorities of capacity building. With training set to commence in critical fields such as public debt management, innovative financial instruments, fiscal resource mobilization, investment promotion, and the energy and digital transition, the initiative promises to equip senior Ethiopian public officials with cutting-edge skills to enhance governance, drive efficiency, and foster innovation across the public sector. "This transfer of expertise," he added, "is crucial for building a more resilient, transparent, and effective public service, capable of supporting Ethiopia's efforts towards sustainable development”.
---------------------+++---------------------
We are for the public sector.
--------------+++------------
Visit our website: http://www.epsu.edu.et/
Follow our Facebook page:
https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
