ch
Feedback
Ethiopian Public Service University

Ethiopian Public Service University

前往频道在 Telegram

ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

显示更多

📈 Telegram 频道 Ethiopian Public Service University 的分析概览

频道 Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 12 734 名订阅者,在 教育 类别中位列第 15 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 642

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 12 734 名订阅者。

根据 11 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 106,过去 24 小时变化为 3,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 34.72%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.17% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 419 次浏览,首日通常累积 2 058 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 27

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

凭借高频更新(最新数据采集于 12 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

12 734
订阅者
+324 小时
+207
+10630
帖子存档
የኢፐሰዩ ካውንስል የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛ ሩብ ዓመት የመደበኛና የሪፎርም ስራዎችን አፈጻጸም ገመገመ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል የዩኒቨርሲቲውን የ2018 በጀት ዓመት የ3ኛ ሩብ ዓመት የመደበኛና የሪፎርም ስራዎች እና ቁልፍ የውጤት አመላካችን (KPIs) አፈጻጸም ግምገማ እና በቀጣይ ሶስት ወራት የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ላይ የውይይት መርሀ ግብር መጋቢት 29 ቀን 2018 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ አካሄደ፡፡ በዕለቱም የስትራቴጂክ ጉዳዮች ስራ አስፈጻሚው አቶ ተፈሪ ጊሼ የ3ኛው ሩብ ዓመት የሪፎርም፣ የመደበኛ እና ቁልፍ የውጤት አመላካች (KPIs) የአፈጻጸም ሪፖርትን አቅርበዋል፡፡ በመቀጠልም የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ በቀጣይ ሶስት ወራት ትኩረት ተሰጥቷቸው ሊከናወኑ የሚገቡ የሪፎርም፣ የመደበኛ እና ቁልፍ የውጤት አመላካቾች ከማስፈጸሚያ ስልታቸው እና ዝርዝር የጊዜ ሰሌዳቸው ጋር ለካውንስሉ አቅርበዋል፡፡ ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ይህን ዝርዝር መረሃግብር ማዘጋጀትና ማቅረብ ያስፈለገበትን ዓላማ ሲገልጹ እስከ ቀጣይ ሰኔ 30 ድረስ መደበኛም ሆኑ የሪፎርም ሥራዎችን በተቀናጀ ሁኔታ ለማጠናቀቅና ወደ ቀጣይ ስራዎች ለመግባት ለመፍጠር መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ባቀረቡት ዝርዝር መርሃ ግብር፣ በቀጣይ የሚፈጸሙትን ስራዎች በሶስቱም ዘርፎች እና በስልጠና ኢንስቲትዩት ለይተው ያመላከቱ ሲሆን፣ ይዘቱም የተጀመረውን የለውጥ ስትራቴጂክ እቅድ አጠናቆ ማስጸደቅ፣ የአገልግሎት አሰጣጥ እና አስተዳደር ሪፎርም ሙሉ በሙሉ ወደስራ ማስገባት፣ የተግባር እና የራስገዝ ዩኒቨርሲቲ ማስፈጸሚያ ስትራቴጂክ ሰነዶችን ማጠናቀቅ እና ወደስራ ማስገባ፣ ለዩኒቨርሲቲው ገቢ ማሳደጊያ የሚውሉ አዳዲስ ኢንተርፕራዞችን ማቋቋም የሚሉ እና ሌሎችም ዋና ዋና ጉዳዮች ተካተዋል፤ ለእያንዳንዱ ተግባር የማስፈጸሚያ ስልት ተቀምጦለታል፡፡ ከዚያም የካውንስሉ አባላት በቀረበው ሪፖርትና በቀጣይ ሶስት ወራት ዝርዝር የስራ መርሀግብር ላይ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ያቀረቡ ሲሆን፣ የዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንቶች እና የሚመለከታቸው የስራ ኃላፊዎች ምላሽ እና ማብራሪያ፣ እንዲሁም ዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ማጠቃለያ ተሰጥቷል፡፡ Visit our website: http://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/ Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt

በኢፐሰዩ መጋቢት 12 ቀን የተጀመረው የማህበረሰብ አገልግሎት መርሀ ግብር ተጠናቀቀ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የማህበረሰብ ተሳትፎ የኢንዱስትሪ ትስስር እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት በየካ እና በለሚኩራ ክፍለ ከተሞች ለሚገኙ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ከመጋቢት 12 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ ሲደርግ የቆየውን የማህበረሰብ ድጋፍ አገልግሎት ተጠናቀቀ፡፡ የዩኒቨርሲቲው የምርምር እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ምትኩ አዲሱ በመዝጊያ ስነስርዓቱ ላይ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፣ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በአካባቢው ከሚገኙ ተቋማት ጋር የተቀናጀ የማህበረሰብ አገልግሎትን የመስጠት ተግባሩን በቀጣይነት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቁመው፣ ይህ ተግባር ከዩኒቨርሲቲው ተቀዳሚ ተግባራት አንዱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ተግባር ላይ ለተሳተፉ አካላትም ምስጋናቸውን አቅርበው፣ ወደፊትም ተሳትፎአቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉም አሳስበዋል፡፡ የማህበረሰብ ተሳትፎ የኢንዱስትሪ ትስስር እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት አስተባባሪ የሆኑት ዶ/ር ዋርካው ለገሰ በበኩላቸው የማህበረሰብ አገልግሎቱ፣ ለዩኒቨርሲቲው በተሰጡት ቁልፍ የውጤት አመላካቾች መሰረት የተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የማህበረሰብ አገልግሎቱ በየካ እና በለሚኩራ ክፍለከተማ ከሚገኙት ከሮፋም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ ከጊብሰን አካዳሚ፣ ከሂልሳይድ አካዳሚ፣ ከሳፋሪ አካዳሚ እና ከደጃዝማች ወንድይራድ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለተጠሩ 25 የትምህርት አመራሮች የአንድ ቀን የአስተዳደር እና የትምህርት አመራር የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዶ/ር ዘውዴ ዛኬ አማካኝነት፣ ከአምስቱ ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ 50 መምህራን የትምህርት እቅድ እና ዝግጅት፣ የትምህር ክፍል አስተዳደር እና የዲሲፕሊን የግምገማ ቴክኒኮች ላይ ያተኮረ የአንድ ቀን ስልጠና ደግሞ በዶ/ር አስማማው ገብረ እግዚአብሔር እና በአቶ አበበ ተስፋ አማካኝነት ተሰጥቷል፡፡ ከየትምህርት ቤቶቹ ለተጠሩ 300 የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችም የሂሳብ ትምህርት ማጠናከሪ ትምህርት (tutorial) ለአስር ቀናት በአቶ ሹመቴ አበጀ፣ በአቶ ንጉሴ ማሞ፣ በአቶ ፈየራ አስፋው እና በአቶ ኢሳያስ ሽፈራው አማካኝነት ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ ከዚህም ሌላ በአእምሮ ጤና እና አደንዛዥ ዕጽ አላግባብ መጠቀም የሚያስከትለውን ጉዳት መሰረት ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና፣ ከየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 እና ከለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ለተጠሩ 50 ወጣቶች፣ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ዙሪያ ለሚገኙ በርካታ የማህበረሰብ ክፍሎች በዶ/ር ብስራት ተክሌ አማካኝነት የተሰጠ ሲሆን፣ የመንገድ ደህንነት እና የትራፊክ አደጋን አስከፊነት የተመለከተ የአንድ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለ50 የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች በዶ/ር በለጠ እጅጉ እና ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በመጡ ባለሙያ ተሰጥቷል፡፡ በመጨረሻም መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ/ም በተካሄደው የመዝጊያ ስነስርዓት ላይ፣ ከየካ እና ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያዎች ከመጡ የትራፊክ ፖሊስ አባላት እና ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን ከመጡ ባለሙያዎች ጋር በመሆን የጎዳና ላይ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስነ ስርዓት ተካሂዷል፡፡ Visit our website: http://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/ Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt

በኢፐሰዩ የመምህራን ማህበር ሥራ አስፈጻሚዎች ምርጫ ተካሄደ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም ( ኢፐሰዩ) የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን ማህበር ሥራ አስፈጻሚዎች ምርጫ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማህበር ፕሬዚደንት፣ የውጪና የህዝብ ግንኙነት ተጠሪ እንዲሁም የማህበሩ ተወካይ በተገኙበት ዛሬ መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም በህዳሴ አዳራሽ ተካሄደ፡፡ በተደረገው ምርጫም ዶ/ር ወይንሸት መንግስቱ የማህበሩ ፕሬዚደንት ሆነው የተመረጡ ሲሆን፣ አቶ አብደላ ሁሴን ዋና ጸሐፊ፣ ዶ/ር መርጊቱ ደበላ የሥርዓተ-ጾታ እና ምክትል ዋና ጸሐፊ ፣ ዶ/ር መስፍን ስዩም የህዝብ ግንኙነት፣ ዶ/ር ይመር መሀመድ ኦዲተር እና ዶ/ር ወንድአፈራሁ ሙሉጌታ የትምህርት ስልጠናና ምርምር አሰተባባሪ ሆነው ተመርጠዋል፡፡ በምርጫ ሥነ ስርዓቱ መክፈቻ ላይም የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር አማኑኤል ኩሲያ እንደገለጹት በዩኒቨርሲቲው የመምህራን ማህበርን ለመመስረት በርካታ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ጠቁመው፣ የማህበሩ ምስረታው እውን ሊሆን በመቻሉ የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡ አክለውም ማህበሩ በዩኒቨርሲቲ የሚገኙ መምህራን አንድነት በመፍጠር እና በመደራጀት የመምህራንን መብትና ጥቅም ከማስከበሩም በተጨማሪ፣ በመምህራን ላይ የሚመጡ ጫናዎችን አስቀድሞ ለመከላከል እንደሚያግዝ አመልክተው፣ የማህበሩ ምስረታም ዩኒቨርሲቲው በለውጥ ሂደት ላይ እያለ እውን ሊሆን መቻሉ እጅግ ከፍተኛ የሆነ ትርጉም ያለው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማህበር ፕሬዚደንት በበኩላቸው ለማህበሩ መመስረት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንትና አመራር ላበረከቱት አሰተዋጽኦና ድጋፍ አመስግነው፣ ያለውን መነሳሳት አድንቀዋል፡፡ አያይዘውም የማህበሩ የምስረታ ሂደትና ዓላማ እንዲሁም ማህበሩ ከምስረታው ጀምሮ እያከናወቸው ያሉ ተግባራትን ለመምህራኑ አጋርተዋል፡፡ በምርጫው ላይ የተሳተፉ መምህራን በሰጡት አስተያየት የማህበሩ መመስረት እንደ መምህርም ሆነ እንደተቋም የሚኖረው ሚና እጅግ ከፍተኛ መሆኑን እና ማህበሩን በመምራት ላይ ያሉትን አመራሮች እያደረጉ ላለው አስተዋጽኦ ያላቸውን አድናቆት ገልጸዋል፡፡ በመጨረሻም የተመረጡት ሥራ አስፈጻሚዎች ማህበሩን በቅንነትና በታማኝነት ለማገልገል ቃለ መሀል ፈጽመዋል፡፡ Visit our website: http://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt

ኢፐሰዩ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር የማማከር ውል ስምምነት ተፈራረመ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ቢሮ ጋር የ10ኛዉ አዲስ አበባ ከተማ መዋቅራዊ ፕላን አፈጻጸም ዉጤታማነት እና ተጽዕኖ ግምገማ እና በ2025 በአዲስ አበባ ያለዉን ድህነት ግምገማ በሚሉ ሁለት ፕሮጀክቶች ላይ የማማከር አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን የስምምነት ውል መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ/ም በቢሮው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተፈራረመ፡፡ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ቢሮ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በተካሄደው በዚህ የፊርማ ስነስርዓት የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ምትኩ አዲሱ ከመስተዳድሩ የፕላንና ልማት ቢሮ የስፓሻል ፕላን አፈጻጸም ክትትልና ቁጥጥር ዘርፍ ም/ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ መዓዛ መንግስቱ እና የፕላንና ልማት ቢሮ የከተማ ጥናት መረጃና አቅም ግንባታ ዘርፍ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌታቸዉ ኃይሌ ጋር ውሎቹን ተፈራርመዋል፡፡ በፊርማ ስነስርዓቱ ላይ ዶ/ር ምትኩ አዲሱ እንደተናገሩት ቢሮው እነዚህን ትልልቅ ሁለት ፕሮጀክቶችን ለማሰራት በዩኒቨርሲቲያችን ላይ ላሳደረው እምነት አመስግነው፣ ዩኒቨርሲቲው የካበተ ልምድ ያላቸው ባለሙያዎችን ተጠቅሞ በስምምነቱ በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ፕሮጀክቱን አጠናቆ እንደሚያስረክብ አረጋግጠዋል፡፡ Visit our website: http://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/ Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የሚሰጠው የተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም ክፍያ ለረጅም ጊዜ ሳይሻሻል በመቆየቱ፣ አሁን ካለው የገበያ ሁኔታና ለትምህርት ጥራት ከሚያስፈልገው ወጪ ጋር የማይመጣጠን ሆኖ ቆይቷል። በመሆኑም ዩኒቨርሲቲው ጥራት ያለው ትምህርት ለመስጠትና አስፈላጊው የትምህርት ግብዐቶችን ለማቅረብ እንዲችል የክፍያ ማሻሻያ ጥናት አድርጎ በዩኒቨርሲቲ የሥራ አመራር ቦርድ የክፍያ ማሻሻያው የጸደቀ መሆኑ ይታወቃል። ሆኖም ዩኒቨርሲቲው በተማሪዎች ላይ ሊያርፍ የሚችለውን የኢኮኖሚ ጫና ከግምት ውስጥ በማስገባት፣ ማሻሻያው በዚህ የ2018 ዓ.ም ሁለተኛ መንፈቀ ዓመት ተግባራዊ እንደማይሆን እየገለጽን፤ አዲሱ የክፍያ ተመን ከሚቀጥለው አካዳሚክ ዓመት ( መስከረም 2019 ዓ.ም) ጀምሮ ሥራ ላይ የሚውል መሆኑን እናስታውቃለን። የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ

በኢፐሰዩ የኮምቲዩቲንግ እና ዲጂታላይዜሽን ኮሌጅ የመጀሪያ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች የዳሰሳ ጥናት ግምገማ ተካሄደ፡፡ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ(ኢፐሰዩ) የኮምቲዩቲንግ እና ዲጂታላይዜሽን ኮሌጅ (College of Computing and Digitalization) ዩኒቨርሲቲው በተሰጠው አዲስ ተክዕኮ መሰረት፣ ሊከፈቱ በታቀዱት አምስት የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ያካሄደውን የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት ግምገማ መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ/ም አካሄደ፡፡ የፍላጎት ዳሰሳ የተደረገባቸው የትምህርት ፕሮግራሞችም ሶፍትዌር ኢንጅነሪንግ፣ /Software Engineering/ ኮምፒዩተር ሳይንስ፣ /Computer Science/ ዳታ ሳይንስ፣ / Data Science ኢንፎርሜሽን ሲስተም፣ /Information Systems/ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ /Information Technology/ ሲሆኑ፣ የዳሰሳ ጥናቱን ያካሄዱት ባለሙያዎች የጥናት ዝርዝር ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ የኮሌጁ ዲን አቶ አለባቸው ጭጬ በግምገማው መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት፣ በእያንዳንዱ የትምህርት ፕሮግራም የተካሄደው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በተናጠል በጥልቀት ተገምግሞ አስተያየት የተሰጠበት መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህ መድረክ የሚካሄደው ግምገማ ጥናቱ በተሰጠው አስተያየት መሰረት መስተካከሉን የማረጋገጥ ስራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ቀጥሎም በአምስቱም የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ የተካሄደው የፍላጎት ዳሰሳ ሪፖርት በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ Visit our website: http://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt

በኢፐሰዩ የኮምቲዩቲንግ እና ዲጂታላይዜሽን ኮሌጅ የመጀሪያ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች የዳሰሳ ጥናት ግምገማ ተካሄደ፡፡ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ(ኢፐሰዩ) የኮምቲዩቲንግ እና ዲጂታላይዜሽን ኮሌጅ (College of Computing and Digitalization) ዩኒቨርሲቲው በተሰጠው አዲስ ተክዕኮ መሰረት፣ ሊከፈቱ በታቀዱት አምስት የመጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ያካሄደውን የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ሪፖርት ግምገማ መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ/ም አካሄደ፡፡ የፍላጎት ዳሰሳ የተደረገባቸው የትምህርት ፕሮግራሞችም ሶፍትዌር ኢንጅነሪንግ፣ /Software Engineering/ ኮምፒዩተር ሳይንስ፣ /Computer Science/ ዳታ ሳይንስ፣ / Data Science ኢንፎርሜሽን ሲስተም፣ /Information Systems/ ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ /Information Technology/ ሲሆኑ፣ የዳሰሳ ጥናቱን ያካሄዱት ባለሙያዎች የጥናት ዝርዝር ሪፖርት አቅርበዋል፡፡ የኮሌጁ ዲን አቶ አለባቸው ጭጬ በግምገማው መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት፣ በእያንዳንዱ የትምህርት ፕሮግራም የተካሄደው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በተናጠል በጥልቀት ተገምግሞ አስተያየት የተሰጠበት መሆኑን ጠቁመው፤ በዚህ መድረክ የሚካሄደው ግምገማ ጥናቱ በተሰጠው አስተያየት መሰረት መስተካከሉን የማረጋገጥ ስራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ቀጥሎም በአምስቱም የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ የተካሄደው የፍላጎት ዳሰሳ ሪፖርት በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል፡፡ Visit our website: http://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt

AFD Expertise Delegation Visits EPSU to Strengthen Ties and Define Collaborative Roles in Public Service Reform (March 19, 2026 ; E.P.S.U.) A key expertise delegation from the Agence Française de Développement (AFD) visited the Ethiopian Public Service University (EPSU) today to strengthen bilateral ties and define collaborative roles in supporting Ethiopia's national public service reform agenda. The AFD team, led by Lauriane Thibaud, Task Team Leader for Public Administration Reform at AFD, and Hiwotee Salvat from the AFD Addis Ababa office, was warmly received at the university by Dr. Amanuel Kussia, Vice President for Academic Affairs; Dr. Dereje Teklemariam, Director of International Collaboration and Partnership; and Dr. Azeb Assefa, Dean of the Training Institute. The visit aimed to provide the AFD delegation with a comprehensive understanding of EPSU's unique mandate as the only university in the country specifically tasked with building capacity across the entire public sector. Through specialized education, demand-driven training, policy-oriented research, and consultancy services, EPSU continues to play a pivotal role in shaping Ethiopia's civil service. Discussions held on campus focused on identifying synergies to further support the ongoing reform efforts of the Civil Service Commission. During the meeting, EPSU leadership proudly reflected on the historic partnership with France. Historical records indicate that the French government was a founding partner in the establishment of the Institute of Leadership and Good Governance in 2010 and has remained a steadfast supporter ever since. This enduring collaboration is formalized through institutional links with prestigious French institutions, including the French National School of Administration (ENA) and the School of Magistrates in France. The EPSU team noted that France's long-term vision and consistent commitment have been instrumental in developing generations of Ethiopian public sector leaders, and expressed enthusiasm for building upon this strong legacy. Building on this foundation, EPSU presented six key areas for potential future partnership: Trainers' Capacity Building to create a multiplier effect across the public service, A Digitalization and Incubation Centre to pilot innovative service delivery models, A Public Sector Innovation and Reform Centre to serve as a policy think tank, A Leadership Excellence Centre dedicated to executive-level development, Support for EPSU's own institutional capacity building as the university transitions to autonomy, Positioning EPSU as a national hub for supporting applied universities across the country. Following the productive discussions, the delegation was briefed on EPSU's ongoing transformation toward producing competent public servants through technology-driven, innovative, and modern programs. The university leadership showcased its commitment to delivering quality education, research, and community engagement services that contribute to a dynamic and accountable public sector. The visit represents a significant step in defining and advancing the collaborative framework between EPSU and AFD. Both sides expressed a shared commitment to deepening their partnership, with the AFD delegation acknowledging EPSU's strategic position in the future of Ethiopian public sector governance and conveying strong enthusiasm for supporting national reform efforts. The EPSU leadership, in turn, reaffirmed its dedication to translating the discussed areas of collaboration into concrete initiatives, ensuring that the partnership continues to yield meaningful outcomes for the modernization of Ethiopia's public service.

AFD Expertise Delegation Visits EPSU to Strengthen Ties and Define Collaborative Roles in Public Service Reform (March 19, 2026 ; E.P.S.U.) A key expertise delegation from the Agence Française de Développement (AFD) visited the Ethiopian Public Service University (EPSU) today to strengthen bilateral ties and define collaborative roles in supporting Ethiopia's national public service reform agenda. The AFD team, led by Lauriane Thibaud, Task Team Leader for Public Administration Reform at AFD, and Hiwotee Salvat from the AFD Addis Ababa office, was warmly received at the university by Dr. Amanuel Kussia, Vice President for Academic Affairs; Dr. Dereje Teklemariam, Director of International Collaboration and Partnership; and Dr. Azeb Assefa, Dean of the Training Institute. The visit aimed to provide the AFD delegation with a comprehensive understanding of EPSU's unique mandate as the only university in the country specifically tasked with building capacity across the entire public sector. Through specialized education, demand-driven training, policy-oriented research, and consultancy services, EPSU continues to play a pivotal role in shaping Ethiopia's civil service. Discussions held on campus focused on identifying synergies to further support the ongoing reform efforts of the Civil Service Commission. During the meeting, EPSU leadership proudly reflected on the historic partnership with France. Historical records indicate that the French government was a founding partner in the establishment of the Institute of Leadership and Good Governance in 2010 and has remained a steadfast supporter ever since. This enduring collaboration is formalized through institutional links with prestigious French institutions, including the French National School of Administration (ENA) and the School of Magistrates in France. The EPSU team noted that France's long-term vision and consistent commitment have been instrumental in developing generations of Ethiopian public sector leaders, and expressed enthusiasm for building upon this strong legacy. Building on this foundation, EPSU presented six key areas for potential future partnership: Trainers' Capacity Building to create a multiplier effect across the public service, A Digitalization and Incubation Centre to pilot innovative service delivery models, A Public Sector Innovation and Reform Centre to serve as a policy think tank, A Leadership Excellence Centre dedicated to executive-level development, Support for EPSU's own institutional capacity building as the university transitions to autonomy, Positioning EPSU as a national hub for supporting applied universities across the country. Following the productive discussions, the delegation was briefed on EPSU's ongoing transformation toward producing competent public servants through technology-driven, innovative, and modern programs. The university leadership showcased its commitment to delivering quality education, research, and community engagement services that contribute to a dynamic and accountable public sector. The visit represents a significant step in defining and advancing the collaborative framework between EPSU and AFD. Both sides expressed a shared commitment to deepening their partnership, with the AFD delegation acknowledging EPSU's strategic position in the future of Ethiopian public sector governance and conveying strong enthusiasm for supporting national reform efforts. The EPSU leadership, in turn, reaffirmed its dedication to translating the discussed areas of collaboration into concrete initiatives, ensuring that the partnership continues to yield meaningful outcomes for the modernization of Ethiopia's public service.