Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 336 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 651,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 347 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 336 名订阅者。
根据 26 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -104,过去 24 小时变化为 -8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 35.99%。内容发布后 24 小时内通常能获得 12.61% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 158 次浏览,首日通常累积 1 808 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 30。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 27 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 336
订阅者
-824 小时
-327 天
-10430 天
帖子存档
14 336
የሸማቂው ኮማንዶ ትንቢት
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖
ክላሹን አፈፍ ያረገው- የነጠቁት ለት ማረሻ
ደረት ላይ እርሳስ ይዘራል- ይኮተኩታል ትከሻ
ታጋሹ አራሹ ገበሬ- ልቡ ከአገሩ የሚሰፋው
ስንቱን ግፍ ይሸከም ዘንዳ- የአትላስን ጫንቃ የሰጠው
በትምክህት በአሃዳዊነት- በባንዳ አፍ የተፈረጀው
ያ ባለ ብዙ ቅጽል ሥም- ጨቋኝ፣ ጨፍላቂው አማራ
ገስግሶ እንደ አጎናፍር- ፈንድቶ እንደ ገሞራ
በአባቱ ክላሽ እና አልቢን፥ በአያቱ ሱኪ፣ ውዥግራ
አሸባሪውን አንኩቶ- ድግስ ይጠራል አሞራ፡፡
ትንቢት..
እንደ ሲሲፈስ እርግማን- መቻሉ ዳርጎት ለስቃይ
ሲያወጣ ሲያወርድ የኖረ- የዓድዋን መሸጦ ድንጋይ
የዚየስን ነጎድጓዴ- እሳት፥ ከክላሹ ሆድ አጉርሶ
አሸባሪውን በጣጥሶ፥ ጥቁር ድንጋዩን ፈርክሶ
በድል ይመጣል አርበኛው፥ አገር አፍራሹን አፍርሶ።
ሼር በማድረግ ለሌሎች ያጋሩት!
14 336
እኛ እና እነሱ➜ ጦር እና ልብ
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖
➜የፌደራል መንግሥት የእርዳታ እህል ወደ መቀሌ ለማድረስ ይታትራል፡፡ አሸባሪው ሃይል ግን አፋር ክልል ውስጥ የተከማቼ የሰላሳ ሺህ ስደተኛ የእርዳታ እህል በእሳት ያጋያል፡፡
➜የእኛ ወታደር ሊያጠቃው ከቤቱ የወጣ የአሸባሪ መንጋን እንደ ንጹሐን ቆጥሮ እራሱን ይሰዋል፡፡ ሰሜን ወሎ የገባው የአሸባሪው ወታደር ግን ቤቱ ውስጥ የተኛን ሕዝብ ይጨፈጭፋል፡፡
➜የእኛ አዋቂና ታዋቂ ሰዎች አሸባሪ ላይ የሚወሰደውን እርምጃ ‹‹በወንድማማቾች መሃከል የሚደረግ ስለሆነ ይቁም›› እያሉ ይቃወሙታል፡፡ በአሸባሪው ቀጠና ውስጥ ያሉ አዋቂና ታዋቂ ሰዎች ግን ሕዝብ ላይ ሒሳብ የሚያወራርደውን እና አገር የሚያፈርሰውን አሸባሪ እንደ መላዕክት ስብስብ ቆጥረው በሚችሉት ሁሉ ያግዙታል፡፡
➜የእኛው መንግሥት ድልድይ ተሰበረ ብሎ የWFP አውሮፕላኖች ወደ መቀሌ የሚበርሩበትን ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ አሸባሪው ሃይል ግን በውጭና በአገር ውስጥ ያሉ ቡችሎቹን በመጠቀም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ላይ ማዕቀብ ይጣል ዘንድ ይዘምታል፡፡
➜የፌደራል መንግሥት የተናጠል ተኩስ አቁም ማድረጉን ይገልጻል፡፡ ነፍስ ያለውን ሁሉ ልቅምቅም አድርጎ በማፈስ የሚታወቀው አሸባሪ ግን የሞት ሽረት ትግሉን አጧጡፎታል።
➜በሚሊዮን የሚቆጠር ተፈናቃይ የያዘችው ኢትዮጵያ እራሷን እያስራበች የአሸባሪውን ቀጠና ለማጥገብ አበሳዋን ታያለች፡፡ የአሸባሪው ምቹጌ ግን በእናት አገር ፍርሰትና ውድቀት የጥቂት ግለሰቦችን አሸናፊነት ለማረጋገጥ ደፋ ቀና ትላለች።
➜የአሸባሪው ሠራዊት ንጹሐንን ደጀኑ አድርጎ መከላከያ ሠራዊቱን ያጠቃል፡፡ የእኛው ጦር ግን ደጀን የሆነውን የራያንና የቆቦን ሕዝብ ለአሸባሪው አስረክቦ ይወጣል፡፡
➜የፌደራልና የአማራ ክልል መንግሥት ከማይካድራም ባለፈ በሰሜን ወሎ የሚፈጸመውን ጭፍጨፋ ለዓለም አቀፉ ማሕበረሰብ ሊያሳውቅ ቀርቶ አሸባሪው ያደረሰውን ጉዳት ስንጽፍ ጁንታውን እንደመደገፍ ይቆጥረዋል፡፡ የአሸባሪው ሃይል ባለሥልጣናትና አክቲቪስት ግን በጦርነት የተሰው ታጣቂዎቹን አስከሬን ሰብስቦ ተከዜ ውስጥ እየጣለ ‹‹ንጹሐን ተጨፈጨፉብኝ›› የሚል ድራማውን ያሰናዳል፡፡
➜የእኛው አርቆ አሳቢ ምርጥ ኢትዮጵያዊ ባድሜን የተቆጣጠረውን የኤርትራ ሠራዊት መውጣት አለበት›› እያለ ይዘምታል፡፡ በአሸባሪው ቀጠና ውስጥ ያሉት ኢትዮጵያውያን ግን የኢትዮጵያን መሬት የተቆጣጠረውን የሱዳን ወራሪ ‹‹ጎንደርን የምትወርበት ጊዜ አሁን ነው›› እያሉ ይጨቀጭቁታል፡፡
➜ሕጻናትን ያሰለፈው አሸባሪው ሃይል በንጹሐን ላይ ከባድ የጦር ወንጀል እየፈጸመ የውሸት ክሱን ይጦምራል፡፡ የእኛው መንግሥት ግን በዜጎች ላይ በገሃድ የተፈጸመውን እውነት በማሳወቅ ፈንታ ህውሓት የሚለጥፍበትን የውሸት ክስ ያስተባብላል፡፡
➜አሸባሪው ሃይል የዘረፈውን ገንዘብ ከካዝናው አውጥቶ እየከፈለ ጥቅመኛ የጦር መሪዎችን ያስከዳል፡፡ ሎቢስቶችን ይቀጥራል፡፡ ከክልሉ ውጭ ያሉ አመራሮችን በጥቅም ይገዛል፡፡ ሕጻናትን እያፈሰ ወደ ጦርነት ይማግዳል፡፡ የእኛው መንግሥት ግን ከእራሱ በጀት ባለፈ መዋጮም እየተሰበሰበለት የሚከዳው እንጂ የሚገዛው የጠላት አመራርም ሆነ ወታደር የለውም፡፡ ስንቁን እና ትጥቁን ችሎ ከቤቱ የወጣውን ሕዝብ ለማዝመት ይቸግረዋል፡፡
➜አሸባሪው ሐሰተኛ ዜናዎችን እየፈጠረ በአክቲቪስቶቹ አማካኝነት ሲያሠራጭ፣ የእኛው መንግሥት ግን እውነተኛ ዜናውን ደብቆ ‹‹በሐሰተኛ መረጃ እንዳትታለል›› ይመክርኻል፡፡
እናስ…
ገጥመውናል እንጂ ገጥመናቸዋል ማለት እንዴት ይቻላል?
‹‹እየወጉን ነው›› ከማለት ባለፈ ‹‹እየተዋጋን ነው›› እንዴት እንበል?
14 336
ከንቲባ ሙሐመድ ያሲን
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖
➜ለመፈናቀል የተዘጋጀውን ሕዝብ አረጋግቶ እራሱን እንዲከላከል ያደረገ፤
➜በአጭር ጊዜ ውስጥ የወልዲያን ወጣት አሰባስቦ ጠንካራ ሠራዊት የገነባ፤
➜እንደ ባቢሎን የመጥፋት አደጋ ያንዣበበባትን ከተማ እንደ ነነዌ የታደገ፤
➜በከንቲባነት ተሹሞ ከጄኔራል ጻድቃን በተሻለ መልኩ የጦር ጠበብት ሆኖ የተገኘ፤
➜ለጭፍጨፋ የተሰማራው አሸባሪ ላይ የጁዎችን አሰማርቶ የእጁን እንዲያገኝ ያደረገ
➜ጌታቸው ረዳ ለወልዲያ ያቀደውን የጥፋት እቅድ አሸባሪው ላይ ያከናወነ፤
➜ስንቅ ፍለጋ ከመጣው አሸባሪ በርካታ ትጥቅ የተረከበ፤💪
👏👏👏
"ከእናቱ ማሕጸን ጀግንነትን ይዞ የሚወጣ የለም።
ያለፈውን እና ያለውን ጀግና የሚያወድስ ሕዝብ ግን የወደፊቱን ጀግና ትውልድ ያፈራል።"
#Share ይደረግ
14 336
የራያ እጣ እንዳይደርስህ እንደ ወልዲያ ሁን❗️
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖
የአሸባሪው የትሕነግ ጦር…
➜ ‹‹ራያ እንዲትረሳ ቆቦን እና መርሳን ሰላም ንሳ››
➜‹‹ኮረምን እንዲዘነጓት ወልድያ እና ላሊበላ ላይ ጥቃት ክፈት››
➜‹‹ከኋላቸው ያለውን ምድር እንዳያስታውሱት የሚኖሩበትን ምድር ፈንጭበት›› የሚል የፍቃድ ወረቀት የተሰጠው ይመስል ሰሜን ወሎ ላይ ቀላል የማይባል የሕይወትና የንብረት ውድመት ፈጽሟል።
በዚህም ሒደት እራሳቸውን ለመከላከል የሚያስችል በቂ ዝግጅት እና አደረጃጀት ከማድረጋቸው በፊት ለአሸባሪው ጥቃት የተዳረጉ አንዳንድ የሰሜን ወሎ አካባቢዎች ከተማቸውን ለቅቀው በመፈናቀል ሕይወታቸውን ማዳን ቢችሉም ንብረታቸውን እና ከተማቸውን ግን ከውድመት መታደግ አልቻሉም፡፡
በሌላ መልኩ ግን...
➜ከእነ ቆቦ እና ራያ ጉዳት በቂ ትምህርት የቀሰሙት የወልድያ ልጆች እራሳቸውን በማደራጀት ሒሳብ ሊያወራርድ የመጣውን አሸባሪ ለውርደት ዳርገውታል፡፡
➜የጁ ላይ የሚውጠው ካልሆነ በቀር የሚወርረው ምድር አለመኖሩን አሳይተውታል፡፡
➜ሕንጻቸው ላይ እሳት ሊለኩስና ከተማቸውን ሊያፈራርስ የመጣውን አሸባሪ ገላውን በእርሳስ በመቦዳደስ የጁዎች የእጁን ሰጥተውታል፡፡
➜‹‹ወልድያ ላይ ለወገን የሚለገስ እንጂ በባንዳ ጥቃት የሚፈስስ ደም የለም›› ብለው እነሱ ላይ ያሰበውን እቅድ እሱ ላይ አከናውነውበታል፡፡ ጠላታቸውን አዋርደው እራሳቸውን አስከብረዋል፡፡
እናም እንላለን…
የአሸባሪው ጦር በጥቂት ቀን ሥልጠና ወደ ሞት ቀጠና የተላከ እንጂ ዘመናዊ መሳሪያ ይዞ የሚንቀሳቀስ የሰለጠነ ጦር አይደለም፡፡ ለምሳሌ ያህል ዛሬ እግረ መንገዱን ባንክ አካባቢ ፎቶ ከተነሳ በኋላ ሾልኮ የወጣው የአሸባሪው መንጋ በሕጻናት የተሞላና ከ300 የማይበልጥ ነበር፡፡ እንዲህ ያለውን መንጋ ደግሞ ከብቦ መዋጥ እንጂ እንደ ግዙፍ ጦር ቆጥሮ መፈርጠጥ አያስፈልግም፡፡
የወልድያን የጀግንነት ተጋድሎ በመቅሰም ባጭሩ መቅጨት እየተቻለ በአንዳንድ ከተሞቻችንን ላይ የፈጸመውን ውድመት እንዲደግም ልንፈቅድለት አይገባም፡፡ ጥቂት ሕይወት ገብረን አሸባሪውን ድባቅ መምታት ስንችል በስነ ልቦና ተሸንፈን ብዙ የሕይወትና የንብረት ጉዳት እንዲያደርስብን ይሁንታችንን መስጠት ተገቢ አይደለም።
#Share
14 336
አሸባሪው ህውሓት ሰሜን ወሎ ላይ ያደረሳቸው ጉዳቶች፦
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖
➜ከ750 በላይ ተሽከርካሪዎች ከእነ ሙሉ ጭነታቸው ዘርፎ ወደ መቀሌ ወስዷል፤
➜በአሥር ሺህዎች የሚቆጠሩ ሱቆች ተዘርፈዋል፤
➜የባንኮችና የቁጠባ ተቋማት ካዝናዎች ባዷቸውን ቀርተዋል፤
➜የመንግሥት ተቋማትና መሥሪያ ቤቶች ተቃጥለዋል፤
➜ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ዜጎች ተገድለዋል፤
➜ሶስት መቶ ሺህ ሰው ተፈናቅሏል፤
➜በአመራርነት የሚሰሩ ግለሰቦችና ቤተሰቦቻቸው ተገድለዋል፤
➜የቅዱስ ላሊበላ ቤተ-መቅደስ ለአደጋ ተጋልጧል
ይህ ሁሉ ጉዳት ደርሶም መንግሥት የአጸፋ እርምጃ የመውሰድ ፍላጎት ስለሌለው የወሎ ሕዝብ ሆይ እራስህን አድን!!
ማንንም ሳትጠብቅ ቅዱስ ላሊበላን ታድገህ ሰማዕት ሁን❗️
ሕይወትህን እና አገርህን የማታስደፍር አርበኛ ሁን❗️
የሚጠብቀኝ ጦር ይመጣል እያልክ ከምትጠብቅ ተደራጅተህ እራስህን ጠብቅ❗️
#Share እናድርገው
14 336
በጠንካራው ህውሓት ፈንታ ትርፍራፊውን አሸባሪ መደምሰስ ለምን ከበደን?
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖
ሃያ ሰባት ዓመት ሙሉ ክልሉ ውስጥ ሲያጠራቅመው በኖረው ጦር መሣሪያ እብሪት የተሰማው የትሕነግ ቡድን ወደ ክልሉ ከተባረረ በኋላ ሦስት ዓመት ሙሉ ምሽግ ሲቆፍር ብሎም ኮማንዶና ልዩ ሃይል ሲያሰለጥን ነበር፡፡
ከዚያም በአገር ክህደት ወንጀል ተሰማርቶ የሰሜን እዝ ሠራዊት ላይ መብረቃዊ ጥቃት ፈጽሞ ጦርነቱን ለኮሰ፡፡ ከተሳካለት አራት ኪሎ ገብቶ ለመንገስ ካልሆነ ደግሞ አገር ለማፍረስም ተንቀሳቀሰ፡፡
በዚህም ጥቃት የተደናገጠው የኢትዮጵያ መንግሥት ‹‹ይሄን ከሃዲ ቡድን መደምሰስ ይገባል›› በማለት ወሰነ፡፡
እናም ሰማንያ ፐርሰንት የሚሆነው የጦር መሣሪያ በትሕነግ እጅ በነበረበት እና ኢትዮጵያ የምትኮራበት የሰሜን እዝ በተመታበት ሁኔታ ውስጥ ብንሆንም መንግሥት ቁርጠኛ ስለነበር የክተት አዋጅ ሳይታወጅ፣ በቂ ጊዜ ወስደን ሳንዘጋጅ ሰላሳ ዓመት ሙሉ ትሕነግ ሲዘጋጅበት የኖረውን ጦርነት በሰላሳ ቀናት ድባቅ መምታት ቻልን፡፡
የአሁኑን ያህል ስንቅም ሆነ ትጥቅ፣ ልዩሃይልም ሆነ መከላከያ፣ አገራዊ አንድነትና ሕብረት በሌለበት ሁኔታ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ ‹‹እነ እከሌ የተባሉ አመራሮችን ስንደመስስ እነ እከሌን ደግሞ በቁጥጥር ስር አዋልን›› የሚል ዜና እንሰማ ጀመር፡፡
ሽሬን፣ አክሱምን፣ አድዋን ያዝን የሚለው እለታዊ ዜናም መቀሌን በመቆጣጠርና አሸባሪውን ቆላ ተምቤን ዋሻ ውስጥ በመወርወር ማጠናቀቅ ተቻለ፡፡ ለምን? መንግሥት እስከ መቀሌ ድረስ ድል የማድረግ ፍላጎት ስለነበረው፡፡
ይህ የድል ፍላጎት ወደ ቁማር ጨዋታ ሲለወጥ ግን…
➜ከዋሻ የወጣ አሸባሪ ሕዝባዊ ማዕበል ቀስቅሶ የሰሜን እዝን ጥቃት በሌላ እዝ ላይ መድገሙን ትሰማለህ፡፡
➜በብዙ መስዋዕትነት እስከ መቀሌ መግባት የቻለው ጦር በቅጽበታዊ ውሳኔ ራያንም ጭምር ለቅቆ ሲወጣ ትታዘባለህ፡፡
➜ክላሽ ይዞ ዋሻ ውስጥ የከረመው አሸባሪ የማረከውን ሳይሆን ወድቆ ያገኘውን ታንክና ከባድ መሳሪያ ታጥቆ ሲተኩስ ታያለህ፡፡
➜በአዲስ የውጊያ ስፍራ ላይ ሕጻናት ሳይቀር አዝምቶ ከፍተኛ ጉዳት የሚያደርስ አሸባሪን የተናጠል ተኩስ አቁም ያደረገ መንግሥት በፕሮፖጋንዳ ሲመክተው ታስተውላለህ፡፡
➜የክተት አዋጅ ታውጆ በርካታ ወጣት በዘመተበት፣ መላው የኢትዮጵያ ወጣት ለክተት ጥሪው መልስ በሰጠበት፣ የክልል ልዩ ሃይሎች በተሳተፉበት ሁኔታ ተቆጣጠርን በሚል ዜና ፈንታ ያለምንም ሥልጠና ታፍሶ የዘመተው የአሸባሪው ጦር ራያንም አልፎ ቆቦን መቆጣጠሩንና ወደ ወልድያ መጠጋቱን ትሰማለህ፡፡
➜አዋጊ ያጣ ሠራዊትና ፈላጊ ያጣ አንድነት በያዘች አገር ላይ ‹‹መሪ ያለው አሸባሪ›› ያለምንም ከልካይ በወሎ ምድር እየፏለለ ውድመት ሲፈጽም ታስተውላለህ፡፡
➜‹‹ውሰዱት›› በተባለ መሬት ላይ ‹‹አስመልሱት›› የሚል ተውኔት ተጽፎ የተሠጠው ምስኪን ገበሬ በማረሻው ፈንታ ውጅግራውን ይዞ ዋጋ በመክፈል ላይ እንደሚገኝ ትረዳለህ፡፡
➜‹‹አሸንፈን እንመጣለን›› ብለው የዘመቱ አዋጊዎችና ‹‹ተሸንፈን እንመለሳለን›› ብለው ቃል በገቡ አዋጊዎች መሃከል አለመግባባትና ግጭት መከሰቱን ትሰማለህ፡፡
#Share
14 336
ቤተ-መንግሥት ውስጥ ታግቶ የቀረው አማራ
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖
የአማራ ሕዝብ ዝናቡ ሲቀርበት፣ በረዶና ውርጭ ሰብሉን ሲያጠፋበት ቀና ብሎ እግዜሩን ‹‹ምን አድርጌህ ነው?›› በማለት ፈንታ ‹‹ምን አድርጌው ይሆን?›› እያለ በጥጋብ ስሜት ውስጥ ሆኖ የፈጸመውን ጡር ልቡ ውስጥ የሚፈልግ ሕዝብ ነው፡፡
ግን ልቡን ቢበረብረውም እራት ባልበላ አንጀቱ ተኮራምቶ ‹‹ተመስገን›› ብሎ የተኛበትን ቀን እንጂ ጠገብኩ ብሎ ፈጣሪውን ወይም ፍጡሩን ያስቀየመበትን ቀን አያገኘውም፡፡ ምክንያቱም አማራ ከርሐብ በላይ ጥጋብን ይጠላል፡፡ ከእግዜርም በላይ ጡር ማድረግን ይፈራል፡፡
➖
የአማራ ሕዝብ ላለፉት አምሳ ዓመታት ለአገር እንጂ ለወንበር ብሎ ታግሎ አያውቅም፡፡ ይልቅስ ዜግነቱን ሲወድ ማንነቱን በመካድ ‹‹እናቴን ያገባ ሁሉ አባቴ ነው›› በሚል አስተሳሰብ አገሩን ላንቆለጳጰሰለት መሪ ሁሉ እራሱን ይሰዋለት ነበር፡፡ ኢትዮጵያንም ሆነ አማራን የማይወድ ሥርዓት ቢመጣ እንኳን ለሚወዳት አገሩ ሲል የማይወደውን መሪ ተከትሎ ቦታውን ቀርቶ ሥሙን ከማያውቀው ዳርቻ ሄዶ ይሞታል፡፡
የሚገርመው ነገር ታዲያ ላለፉት አምሣ ዓመታት ለወንበር የታገለም ሆነ አራት ኪሎ ዙፋን ላይ ቁጭ ያለ አማራ ባይኖርም ህውሓት የሚባል ድርጅት እውን ከሆነበት ጊዜ አንስቶ ግን አማራው በመንፈስ ከታገተበት ቤተ-መንግሥት አምልጦ መውጣት አልቻለም፡፡
በመሆኑም ያኔ ደደቢት በረሐ ሲገቡ በደርግ ሥርዓት ፈንታ ‹‹የአማራን ሥርዓት መገርሰስ›› የሚል ትግል ለኩሰው ሲወጉት ነበር፡፡ በዚሁ ሕዝብ ታዝለው ወደ ቤተ-መንግሥት ከገቡ በኋላ ደግሞ ‹‹ተገረሰሰ›› ያሉትን የነፍጠኛ ሥርዓት ‹‹እንዳይመለስ›› ብለው ይተኩሱበት ጀመር፡፡ አሁን ደግሞ ከእንደገና ቤተ-መንግሥት አስገብተው የተለመደውን እገታ ይፈጽሙበት ይዘዋል።
➖
አማራው ወልቃይትና ራያን በሃይል ሲነጠቅ ‹‹አገር ላፍርስ፣ ምድሩን ላተራምስ›› የሚል ጨዋታ ውስጥ በመግባት ፈንታ ትግራይን ‹‹አገሬ›› ብሎ በዝምታ ነበር ያለፈው፡፡ ወደ ትግራይ ከተወሰደው መሬት በላይ እንደውም የባድሜ መሬት መደፈር ነበር ያንገበገበው፡፡ ርስቱን እና ማንነቱን የነጠቁት መሪዎች ‹‹መሬታችን ተደፈረ›› ብለው በነገሩት ማግሥትም ‹‹እናት ኢትዮጵያ የደፈረሽ ይውደም›› እያለ ለባድሜ መሬት ነበር መስዋዕትነት የከፈለው፡፡
እንዳለመታደል ሆኖ ግን ሎሬት ጸጋዬ…
‹‹…የተወጋ በቅቶት ቢተኛ፥ የወጋ መች እንቅልፍ አለው
የጅምሩን ካልጨረሰው
የተበደለ ቢችልም-የበደለ ዝም አይልም…›› ብሎ እንዳለው ከተቆጣጠሩት ቤተ-መንግሥት ውስጥ ሆነው ‹‹የነፍጠኛው ሥርዓት እንዳይመለስ›› እያሉ ሲያዳክሙት የኖሩት ከሃዲዎች በነጠቁት መሬትም ወሮታ ሊከፍሉት ሲገባ ‹‹የሆነ አጋጣሚ ካገኘ ማንነቱን ያስመልሳል›› በሚል ሥጋት በጠላትነት ፈርጀው ተቆጥሮ የማያልቅ ግፍ ሲፈጽሙበት መኖራቸው ነው፡፡
ከዚህ ባለፈም ከአማራ በወሰዱት መሬት ‹‹እንገነጠላለን›› ወይም ደግሞ ‹‹አገር እናፈርሳለን›› እያሉ አማራውንና ኢትዮጵያን ሲያስፈራሩበት ነበር፡፡
ስለሆነም ባሁኑ ሰዓት አሸባሪው ቡድን የሚዋጋው በሃይል ነጥቆ የግል ሃብት ሲያካብትበት ለኖረው የሰሊጥ መሬት ሲሆን አማራው ግን ሃያ ሰባት ዓመት ሙሉ በጠላትን አስፈርጆ ፍዳና ግፍ ሲያስተናግድበት ለኖረው ማንነቱና መሬቱ ነው፡፡
አሸባሪው ጦርነት የለኮሰው ‹‹ሕዝብን የምጨፈጭፍበትን እና አገር የምዘርፍበትን ሥልጣን ካጣሁ የወልቃይትና የራያ ነባር ባለርስቶችን በማፈናቀል መሬቱን ይዤ ልገንጠል›› በሚል ሐሳብ ሲሆን፣ አማራው ግን ‹‹በእኔ መሬት የኢትዮጵያን ፍርሰትም ሆነ የበሰበሰ ሥርዓትክን ቀጣይነት ማረጋገጥ አትችልም›› ብሎ ነው ወደ ትግል የገባው፡፡
አሸባሪው የክልሉን ሕዝብ ሕይወት የሚማግደው ታሪካዊ ማስረጃ አቅርቦ በሕግም ሆነ በሃይል ለማያሸንፍበት መሬት ሲሆን አማራው ግን እውነትና በቂ ምክንያት ይዞ ነው፡፡ እውነትን የያዘ ሃይል ደግሞ በሕግም ሆነ በሃይል እንደሚያሸንፍ ጥርጥር የለውም፡፡
#Share
14 336
አፈር ገፍቶ እንዳይኖር፥ አምርቶ እንዳይበላ
እርሻው ድረስ መጥተህ፥ ከወረርከው ኋላ
ሁል ጊዜ ቀረርቶ- ሁልጊዜ ሽለላ- ሁልጊዜ ፉከራ
ብለህ ያሾፍክበት፥ አራሹ ታጋሹ፥ ነፍጠኛው አማራ
እልፍ ዓመት አስቦ፣ ለክቶ መዝኖ
የፈጸምከውን ግፍ- ስቃዩን ተንትኖ
ሒሳብ ሊተሳሰብ- ያው መጣልህ ፋኖ፡፡
ስትዘርፍ፣ስትጨፈጭፍ- የከረምከው ባንዳ
ውዝፍ ሒሳብ ካለህ- ያልተከፈለ እዳ
ታጣቂህን አቅርብ-ጉጅሌህን ደርድር
አማራ ጡር እንጂ- መች ያስፈራዋል ጦር
Share
14 336
"እገነጠላለሁ"
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖
➜የጥቁር ሕዝቦች ነጻነት ከተረጋገጠበት የአድዋ ተራራ ስር ተወልዶ ባንዳነትን የሕይወት ፍልስፍናው ያደረገ አሸባሪ
➜የቀበሮ ጉድጓድ ውስጥ ሆኖ ሃያ ዓመት ሙሉ የጠበቀው ሠራዊት ላይ ክህደት ፈጽም እንደ አንበጣ የጨፈጨፈ…
➜በውስኪ ስካር በጀመረው ጦርነት የስንቱን ለጋ ወጣት ሕይወትና የአገር ሐብት ያወደመ
➜በጥጋብ ተቆዝሮ ጦርነት ከለኮሰ በኋላ በክልሉ ውስጥ የፈጠረውን ሰው ሰራሽ ርሐብ ወደ ኢትዮጵያ አከፋፍሎ በኑሮ ውድነትና በእጦት የምትሰቃይ አገር የፈጠረ
➜በአንድ ዐይናችን የኦሎምፒክ ውድድር፣ በሌላ ዐይናችን ጦርነት እንዲንከታተል ያደረገ የእረፍት ጸር
➜በእሱ ብርታት ሳይሆን በእኛ ድክመት ሃያ ሰባት ዓመት ሙሉ ሕዝብን እየከፋፈለና አገሩን እየገደለ በሰው አገር ላይ ኢንቨስት ሲያደርግና ቪላ ሲቀልስ የኖረ የሙሰኛ ስብስብ
➜ምክንያት የለሽ ጦርነት ለኩሶ ኢትዮጵያ የምትኮራበትን መከላከያ ሠራዊት ያዳከመ፣ ኢትዮጵያ ተስፋ የምታደርግበትን የአባይ ግድብ ወገኑን በሚገድልበት ጦር መሳሪያ ለግብጾች የለወጠ፣ ሕዝቧን የሚያበላውን የአየር መንገድ ለማውረድ የትዊተር ዘመቻ የከፈተ ሕሊና ቢስ…
➜ታሪኩ-ታሪክ ከማጥፋት፣ ገድሉ- አገር ከመውጋት፣ ሕልሙ- ኢትዮጵያን ከማፍረስ፣ ሰላሙ- ሰላም ከመደምሰስ የሚቀዳ አሸባሪ…. ‹‹መገንጠል›› የሚል ቃል ሲሰማ በመደንገጥ ፈንታ ‹‹እገነጠላለሁ›› እያለ ሊያስፈራራ አይችልም፡፡
ምክንያቱም…
ከሰፈሩ እየወጣ አገሩን ሲዘርፍ፣ ሲጨፈጭፍ፣ ሲያራቁት፣ ሲያደኸይ፣ ሲያሸብር፣ ሲያጋጭ የኖረ ወንጀለኛ ‹‹ከዚህ በኋላ እናንተን አልፈልጋችሁም›› ብሎ ሲዝት መደንገጥ ያለበት የሰፈሩ ሰው እንጂ አገሬው አይደለም፡፡ ‹‹የምትገነጠለው ማንን ልትዘርፍና ልታጨፋጭፍ አስበህ ነው?›› ብሎ መጠየቅ ያለበትም የአካባቢው ሕዝብ ድርሻ ነው፡፡
#Share
14 336
በምድር ቅዱስ ላሊበላን፣ በትዊተር የኢትዮጵያ ዓየር መንገድን
(አሳዬ ደርቤ)
➖➖➖
ሊጠብቃቸውና ሊያተርፋቸው ከሚገቡ ታሪካዊ ቅርሶች እና የእምነት ቦታዎች ላይ ፖለቲካዊ ትርፍ ለማግኘት ሲል የጦር መሳሪያ መጋዘን እና ምሽግ አድርጎ በአልነጃሽ እና በበርካታ አድባራት ላይ ውድመት የፈጸመው አሸባሪ በክልሉ የፈጸመውን ጥፋት አማራ ክልል ላይ ለመድገም አቅዶ መንቀሳቀስ ከጀመረ ቀናት ተቆጠሩ፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘም ይሄ እርኩስ ቡድን ባንድ ወቅት ተኩስ ከፍቶ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሰበትን የቅዱስ ላሊበላን መቅደስ ለማውደምና ለመዝረፍ እቅዶ በእሾህ የተሞላ ጉዞውን ጀምሯል፡፡ በሳይበር የሚዋጋው የአሸባሪው ክንፍ ደግሞ የአገራችን ኩራት እና ሐብት የሆነውን የኢትዮጵያ አየር መንገድን ከጨዋታ ውጭ ለማድረግ መጠነ ሰፊ የሥም ማጥፋት ዘመቻ ከፍቷል፡፡
ስለዚህ መላው ኢትዮጵያዊ ይሄን አውቆ ከመንፈሳዊው እስከ ቁሳዊው፣ ከቅርስ እሰከ ነፍስ ያገኘውን ነገር ሁሉ ለማጥፋት የተነሳውን ይሄን አሸባሪ ቡድን መመከት ግድ ይለናል፡፡ የትዊተሩን በትዊተር፣ የምድሩን በምድር እየመከትን ከማይጠግብ ከርስ እና ከማይሞላ ካዝና ውጭ አገርም ሆነ እግዜር የማያውቀውን አሸባሪ ከምድራችን መጠራረግ ይገባናል፡፡
በተለይ ደግሞ የሆነ ጥቃት ሲደገስ ከሁሉም በፊት ቀድሞ የሚደርስ በአካባቢው ያለው ሕዝብ እንደመሆኑ መጠን ‹‹የኔ ነፍስ ሳታልፍ የቅዱስ ላሊበላ ቤተ-መቅደስ አይደፈርም›› በሚል አቋም ድፍን የወሎ ሕዝብ ነቅሎ በመውጣት ይህ የአጋጋንንት ቡድን የጀመረውን ጉዞ መንገድ ላይ መቅጨት ይኖርበታል፡፡
#Share
14 336
እሚገርም መንግሥት
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖
እሚገርም መንግሥት- ቅጥ አንባር የጠፋው
ወንበር ተረክቦ- አገር የቸገረው
ሕዝብ ተሸክሞት- ድካም የሚሰማው
የሚደንቅ መንግሥት፣
ደጋፊውን ትቶ- ከአጥፊው ጎን የሚዘምት
‹‹እኩይ›› ሲሉት እርግብ፣ ‹‹የዋህ›› ሲሉት እባብ
በትሩን ወርውሮ- በሆዱ የሚሳብ
ጭንቅላቱን ጥሎ- በቆሽቱ የሚያስብ
ባሕሪው የአራስ ሴት፣ መልኩ የእስስት ቆዳ
ደማከሴ ሳለ- አንካሴ እያነሳ- ወገን የሚጎዳ
የሚገርም መንግሥት...
ጥርስ ያወጣል ሲሉት- እግሩ ጠና ሲባል
አልጋ ላይ ተጋድሞ- ዝንታለም መጥመልመል
አቅሙን አሽቀንጥሮ- አዚሙን የማጥል
ይገለጣል ሲሉት- ይይዛል አንድ አቋም
ሰርክ ዥዋዥዌ- ሁልጊዜ ፔንዱለም
የሚገርም መንግሥት- መላ ቅጥ የሌለው
መድፉን ያገኘ ቀን- ሰልፉ የሚጠፋው
ሰላም ላይ ልግመኛ- ጦርነት ላይ ሰነፍ
ጦር ሜዳ ምሽግ ውስጥ- በፍቅር የሚሸነፍ
ትግሉን አቀጣጥሎ- ድሉን የሚያከሽፍ፡፡
የሚገርም መንግሥት…
አጋም ቆንጥር ለቅሞ፣ እሾሁን ጎንጉኖ- አበባ የሚሠራ
ዘንባባ መንጥሮ- ጠመንጃ የሚያበጅ- ሱኪና ውዥግራ
አገር ሲሉት ብሔር፣ ወንበር ሲሉት ምድር
ዘመድ ሲሉት ባዳ- ገዢ ሲሉት ገባር
እንደ ጦር ማስቲካ-
ከምላሱ ጫፍ ላይ- ያኖራትን አገር
ጣሟ እስኪያልቅ አላምጦ-
አክ እንትፍ እያለ- ከአፉ የሚያሽቀነጥር
እሚገርም መንግሥት...
14 336
ሰበር❗️
ከፕሬዝዳንት ኢሳያስ አንደበት...❗️❗️
(አሳዬ ደርቤ)
➖➖➖
"ክረምት አግቢ ወይም አሸን የመጨረሻ የእድገት ደረጃ ላይ ሲደርስ እንደ ጉድ ይቀፈቀፋል። ክንፍ አብቅሎ እየበረረ ቀየህን እና ምድርህን ይወርረዋል።
ከአፍታ በኋላ ግን ክንፉ ይረግፍና መብረር ቀርቶ መራመድ ይሳነዋል። ጥቂት ቆይቶም ይሞታል።
የወያኔ የአሁኑ መንቀዥቀዥም ከአሸን ጋር የሚመሳሰል ነው። በመሆኑም ከሰሞኑን ህውሓት በአማራ፣ በአፋርና በኤርትራ በኩል የሚቅበዘበዘው ወደ መቃብር ከሚሸጋገርበት የመጨረሻ የትግል ደረጃ ላይ ስለደረሰ ነው። ሞትን ከመጠበቅ ይልቅ ገዳይ መፈለግ መርጦ ነው።
ይህ ፉከራ አይደለም። በቅርቡ የሚታይ ነገር እንጂ"
እውነት ብለዋል ክቡር ፕሬዝዳንት❗️
#Share ይደረግ!
14 336
ከአንድ አማራ ለሁሉም አማራ
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖
➜ከባድ ትግል ከሚጠይቅ ዘመቻ ውስጥ ያገኘናትን ብጣቂ ድል እያገዘፍን ለትግል የተነሳሳውን ወጣት አናዘናጋ
➜ምንም አይነት ውጊያ ባልተደረገበት ሁኔታ ደምሳሽ እና ተደምሳሽ እየፈጠሩ፣ ያለምንም ጦር ከተሞችን እየተቆጣጠሩ ሰበር ዜና ሲሰብሩ የኖሩ አክቲቪስቶች ዋነኛ የህውሓት ምሽጎች ናቸው፡፡ እስካሁንም አሸባሪውን አቅም አልባ አድርገው በማቅረብ መከላከያችንን እና ልዩ ሃይላችንን ሲያስበሉ ኖረዋል፡፡ አሁንም በዚያው ተግባራቸው ቀጥለዋል፡፡ በመሆኑም ‹‹አንቂዎች›› በሚል ስም የተደራጁት እኒህ ‹‹የእንቅልፍ ክኒኖች›› የሚነዙትን የድል ዜና ሼር በማድረግ ፈንታ እረፉ ማለት ይገባናል፡፡
➜ኤሊት›› በሚል የጭፍጨፋ ሥም የአማራን ሕዝብ ከምድረ ገጽ ማጥፋት የሚፈልግ አሸባሪ ምድራችን ውስጥ ገብቶ ከባድ ውድመት እየፈጸመ ባለበት ሠዓት በቴዲ አፍሮ የክብር ዶክትሬት ዙሪያ በመጨቃጨቅ ሁለት ቀናት እንዳባከንነው ሁሉ ነገም ከባዱን ትግል ትተን በቀላል አጀንዳዎች እንዳንጠለፍ እንጠንቀቅ
➜በክልሉ ጉዳይ ተሰባስቦ የሚመክርን አካል ያደረገውን ውይይት ከመጣጣል ይልቅ የእራሳችንን የውይይት መድረክ እየፈጠርን ትግሉን ማገዝ በምንችልባቸው ጉዳዮች ዙሪያ እንምከር
➜አሸባሪው ሃይል በአማራ ክልል ላይ ያደረሰው ጉዳት በእራሱ ክልል ላይ ከፈጠረው ውድመት ጋር ሲነጻጸር ኢምንት ነው፡፡ ያም ሁኖ ግን ‹‹ድርጅታችን ከሚሸነፍ የእኛና የልጆቻችን ሕይወት ይቀጠፍ›› ከማለት ባለፈ ‹‹እረፍ›› የሚለው አካል አልተገኘም፡፡ የአማራ አክቲቪስቶች የሚል ሥም የያዙ የአማራ ጠላቶች ግን የምናውቀውን ብአዴን በማጣጣል ብሎም ሕዝቡ ይሄን ድርጅት በቅድሚያ ይታገል ዘንድ በመቀስቀስ ተጠምደዋል፡፡
አብን እንኳን ‹‹ቅድሚያ ለሕዝብና ለአገር›› በሚል መርሕ ትግሉን በሚመራበት ሠዓት እኒህ አረሞች ግን ሕዝቡን የወንበር ትግል ውስጥ በማስገባት የአሸባሪውን ድል ለማረጋገጥ ደፋ ቀና እያሉ ነው፡፡ ሆኖም ግን ትሕነግ ከአማራው በፊት ማጥፋት የሚፈልገው ብአዴንን በመሆኑ የዚህ ጦርነት ውጤት የአማራውን ብቻ ሳይሆን የድርጅቱንም ህልውና የሚወስን ነው፡፡ ስለሆነም የክልል መሪዎችንም ሆነ ብአዴንን ከመዝለፍና ከመጥለፍ ወጥተን ለጭፍጨፋ የዘመተብንን አሸባሪ በጋራ ትግል እናጥፋ፡፡
➜የትኛውንም መረጃ ስንለጥፍ በሚያስገኘው ላይክና ኮሜንት ልክ ሳይሆን ለሕዝባችን የሚያመጣውን ጥቅምና ጉዳት በማስላት ይሁን፡፡
➜የምናስተላልፋቸው ሐሳቦች አጋሮቻችንን እንጂ ባላንጋራዎቻችንን የሚያበዙ እንዳይሆኑ እንጠንቀቅ፡፡
➜የአሸባሪውን ወረራም ሆነ የሚፈጽመውን ጥቃት የሚያረሳሱና የሚያድበሰብሱ ሰበር መረጃዎችን ከመግዛት እንቆጠብ
➜ለጸረ አማራ ፖስቶች የአጸፋ ኮሜንት በመስጠት ፈንታ ሪፖርት እናድርግ
➜እርስ በእርስ ከመጠላለፍና ከመዘላለፍ ጸድተን በአማራነት ጥላ ስር በመተቃቀፍ አሸናፊነታችንን እናረጋግጥ!
➜በመሃከላችን ችግር ሲፈጠር ፌስቡክ ግድግዳ ላይ ሳይሆን በጓዳ እንምከር፡፡
ድል ለእኛ!
Share
14 336
የአሜሪካ ወቅታዊ አቋም…
(አሳዬ ደርቤ)
➖➖➖➖
እባቡ አፈሩን ልሶ- ከወደቀበት ተነስቶ- እያነከሰ ሲያዘግም
የብሱን ሲያተራምሰው- ንብረት፣ ሕይወትን ሲያወድም
ኢትዮጵያ ዘመቻ ጠርታ- በፌስቡክ በትዊተሩ- ሽብሩን ብትቃወምም
አሜሪካ ያለ መብቷ- በአገራት ሉዓላዊነት- በውስጥ ችግር አትገባም፡፡
የአሜሪካ ወቅታዊ አቋም….
ከወላጅ በላይ ለልጁ- ማንም ሰው ስለማያስብ- ህውሓት ሕጻናት ያዝምት
ከሐሺሽ ባገኙት ወኔ- በክላሽ ዙሪያውን ከብበው- መከላከያን ይበሉት
በአጸፋው የኢትዮጵያ ጦር- ሤሪፋም ይመግባቸው- በጡጦ ያቀብል ወተት
የአሜሪካ ወቅታዊ አቋም…
ሱዳን ጎንደርን ትውረር- አማራ ከራያ ይውጣ- ኤርትራ ከመረብ አትለፍ
ህውሓት ጦሩን አዝምቶ- ስደተኞችን አይቅጠፍ
ይልቅስ ማዶ ተሻግሮ- ከራያ እስከ ወልድያ- ሊጥና ዱቄቱን ይዝረፍ
አማራው መንገዱን ከፍቶ- በሌለ ሒሳብ ይጨፍጨፍ
ቲዲኤፍ ወደ አራት ኪሎ- እርዳታው ወደ መቀሌ- በአፋጣኝ አሁኑ ይለፍ
የአሜሪካ ወቅታዊ አቋም…
ኢትዮጵያ እንዳትበተን- ትሕነግ ጠንክሮ ይውጣ- አፋርን በሃይል ያስገብር
መንግሥት በፍጹም ቅንነት- የተኩስ አቁሙን ይተግብር
ግብጽ ይሁንታዋን ሳትሰጥ- ታላቁ የሕዳሴ ግድብ- ጠብታ ውሃ አይያዝ
ለፖለቲካ ድርድር- የአራት ኪሎ በር ተከፍቶ- የምርጫ ውጤቱ ይሰርዝ
መንግሥት መድረቁን ትቶ- እንደ ቤርጎ ቤት አንሶላ- እየታጠበ ይጠምዘዝ❗️
#Share
14 336
የአሸባሪውን መኪና አብኖች እንዴት እንደማረኩት…
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖➖
የአማራን ጦር እየመሩ በራያ ግንባር የዘመቱት አቶ ጋሻው መርሻና ጧሂር መሃመድ አድካሚውን ዳገት ወጥተው ተራራው ጫፍ ላይ ብቅ ሲሉ ከፊት ለፊታቸው የጁንታውን ጦር አገኙት፡፡
ያን ጊዜም እየፎከሩ መዋጋት ያደጉበት ባሕል በመሆኑ አቶ ጧሒር መሃመድ…
"በብዙ ድካም- በስንት ልፋት
እዳ ሊያስከፍል- የአማራን ኤሊት
ግደሉኝ ብሎ- የመጣው ጠላት
ያው እዚያ ማዶ- ከምሽጉ ስር
ሲምስ ሰንብቶ- የእራሱን ቀብር
እየጠበቀ- የአማራን እድር›› ብሎ ከፎከረ በኋላ ለተኩስ ሲዘገጃጅ አቶ ጋሻው መርሻ ደግሞ…
‹‹ይህ የአገር ሕመም- የዘር ጥቀርሻ
ሲያቀብጠው ወጥቶ- ከተንቤን ዋሻ
ከጓድ ጧሒር እጅ- ከጋሻው መርሻ
ወድቆ ተገኘ- በመጨረሻ››… በማለት ክላሹን ያንፈቀፍቀው ጀመር፡፡
በተመሳሳይ ጊዜም በዙሪያቸው ያለው ሠራዊት አሸባሪውን ቀለበት ውስጥ አስገብቶ እንደ ገብስ ይሸከሽከው፣ እንደ ኑግ ይወቅጠው፣ እንደ ሰሊጥ ይጨምቀው፣ እንደ በርበሬ ይደቁሰው ያዘ፡፡
በአንድ እጁ ክላሽ፣ በሌላ እጁ ሐሺሽ ይዞ የሚዋጋው የአሸባሪው ሠራዊትም ማንኮዚየም እንደተረጨ አንበጣ በቅጽበት ውስጥ ተረፈረፈ፡፡ ይሄንንም እልቂት የተመለከተው መንጋ አንገቱ ላይ ያሠረው የሱዳን መተት ከጥይት በመታደግ ፈንታ ገዳይ ለመፈለግ የሚያግዝ መሆኑን ተረድቶ እጁን ይሰጥና ይፈረጥጥ ያዘ፡፡
ከዚህም ጋር ተያይዞ እነ ጧሂር ፈርጣጩን ጦር መልቀም አስበው ወደ ፊት ሲገሰግሱ፣ አብዛኛው ሠራዊት ደግሞ የአሸባሪው ጦር ጥሎት የሄደውን ትጥቅ ሲለቅም ቆይቶ ከክላሽ እስከ ጅምላ ጨራሽ የጦር መሳሪያ ከእጁ ማስገባት ቻለ፡፡
ወደ ሞት ቀጠና የከተተውን ወጣት ከርቀት ሆኖ የሚያዋጋው የጁንታው አመራርም ያሰማራው ሠራዊት ግብዓተ መሬቱ መፈጸሙን ሲረዳ አበረታች እጹን ከወሳሰደ በኋላ ‹‹ከመኪና ይልቅ በእግሬ ብሮጥ እፈጥናለሁ›› በሚል ውሳኔ የሰለሞን ባረጋን ሠዓት በሚያስንቅ መልኩ የአስር ሺን እና የማራቶንን ሪከርድ እየሰባበረ እንደ ንፋስ ሲምዘገዘግ ሹፌሩም ከኋላው ተከትሎት ይሮጥ ጀመር፡፡
ድርጅታቸውን የሁለት ተሸከርካሪ ባለቤት ማድረግ የቻሉት እነ ጋሻው መርሻም የማረኩትን መኪና ታርጋ ፈትተው ፎቶ ከተነሱ በኋላ መኪናውን አስነስተው ለመሄድ ሲያስቡ መንጃ ፍቃድ እንደሌላቸው ትዝ አላቸው፡፡ ያን ጊዜም ሹፌሩን ከኋላ ከኋላ እየተከተሉ ‹‹ቅልጥምህን ከምትሰበር እጅህን ሰጥተህ በሹፌርነት ብትቀጠር ይሻልኻል›› ሲሉት ሹፌሩ እጁን በመስጠት ፈንታ እንዲህ ብሏቸው ፍጥነቱን ጨመረ፡፡
‹‹በቋሚነት ነው በኮንትራት?››😁
#share
14 336
አሸባሪው ሃይል መቀሌ ላይ ያደረሰው ጉዳቶች፦
#አሳዬ_ደርቤ
➖➖➖➖
➜ዳቦ የሚጋግሩ የዳቦ ማሽኖች የሸረሪት ድር አድርቶባቸዋል።
➜"ለሰፈሩና ለከተማው የበረሃ ከሰል ሲያከፋፍሉ የኖሩ የከባድ መኪና ሹፌሮች በብርድ የሚንገበገቡ ሆነዋል
➜መንግሥት የለሽ እና ደሞዝ አልባ መንግሥት ሠራተኞች ተፈጥረዋል፤
➜የስንዴ እንጀራ ዋጋ አምሳ ብር ሆኗል
➜ትልልቅ እንግዶችን ሲያስተናግዱ የነበሩ ባለ ኮከብ ሆቴሎች የሽብር ቡድኑ መሪዎች ነፍስ ያላወቁ ልጃገረዶችን የሚደፍሩባቸው ቤርጎዎች ሆነዋል።
➜ውስኪ የሚርከፈከፍባቸው ናይት ክለቦች ካቲካላ የሚጠርርባቸው መሸታ ቤቶች ለመሆን ተገድደዋል።
➜የእርዳታ እህል ለማግኘት የሚፈልጉ ወላጆች አሸባሪ ቡድኑ ባወጣው አዲስ ሕግ መሠረት ልጃቸውን ወደ ጦርነት መሸኘት ግድ ብሏቸዋል።
➜ቡናና ሻይ መጠጣት ውስኪ የመጠጣት ያህል ከብዷል።
➜ከጦርነቱ በፊት አሸባሪው ክላሽ አስይዞ በየአደባባዩ ሲያስጨፍራቸው የነበሩ እናቶች ዛሬ የባዶ ቤታቸውን በር ከፍተው ወደ ጦርነት የሄዱ ልጆቻቸውን የሚጠብቁ ሆነዋል፤
➜ከተማው ውስጥ ሲፏልሉ የኖሩ ዘመናዊ መኪኖች በነዳጅ እጥረት ምክንያት አንድ ቦታ ተገትረው ጎማቸው ላይ ሳር በቅሎባቸዋል፤
➜ሌባና ዘራፊ በመስፋፋቱ የተነሳ እነዚያ የጌጣ ጌጥ መሸጫ ሱቆች "ወርቅ ቤት" የሚል ታፔላ የተለጠፈባቸው መኖሪያ ቤቶች ሆነዋል፤
➜ሥልጣን ያላቸው ሰዎች መፈንጫ የነበረው ከተማ በጉልበተኞች ቁጥጥር ስር በመውደቁ የተነሳ ሽሮ የሚሸጡ ምግብ ቤቶች "ቅድሚያ ሒሳብ ይክፈሉ" የሚል ማስታወቂያዎችን ለመለጠፍ ተገድደዋል።
➜ፍራፍሬና አትክልት ከከበሩ ማዕድናት ተርታ ሰፍረዋል፤
➜ከፍተኛ የገንዘብ ዝውውር ሲያስተናግዱ የኖሩ ባንኮች የዘበኛ ቤቶች ለመሆን ተገድደዋል።
በአጠቃላይ ከጌታቸው ረዳ ንግግር ውጭ ያለው ነገር በሙሉ እጅግ የሚያሳዝን ሆኖባቸዋል።
14 336
ጌታቸው ረዳ መቃብር አፋፍ ላይ ሆኖ የአራት ኪሎን ወንበር እያሰበ ‹‹እኛ የምንገድለው ሁሉንም ኤሊት ሳይሆን ይሄን ዘመቻ የደገፉትን ነው›› እያለ ሲቀላምድ በባዶ ድስኩሩ እንደሚያስደስታቸው ደጋፊዎቹ ሳቅ ሳቅ ይለኛል፡፡
የሞት መልዓክ ክንፍ ላይ ተቀምጦ ‹‹በስቅላት እና በእስራት በሚቀጣቸው ኤሊቶች ዙሪያ›› ማብራሪያ ሲሰጥ…. በሙሥና ወንጀል የሞት ፍርድ ከተበየነበት በኋላ ‹‹በመጨረሻ የምታስተላልፈው መልዕክት አለህ ወይ?›› ሲባል ‹‹ከዚህ ስቅላት የማገኘው ትምህርት በቀጣይ ለምኖረው ሕይወት ያለው ፋይዳ የጎላ ነው›› ያለውን ፖለቲከኛ ያስታውሰኛል፡፡ ወይም ደግሞ "ዳኛው ላይ የቅጣት ውሳኔ ያስተላለፈውን እስረኛ" ትዝ ያስብለኛል። 😆
በሌላ መልኩ ግን በፍጡሩም ሆነ በፈጣሪ ተስፋ የቆረጡት መንጋዎች የጌቾን ባዶ ቃላት እንደ ትንቢት ቆጥረው በደስታ ሲፈነድቁ "እነዚህ ሰዎች ጌታቸው ረዳን እንደ ሰማያዊ ጌታ ተቀብለውት ይሆን?" እያልኩ እጠይቃለሁ።
14 336
ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የተጻፈ የወቀሳ ደብዳቤ
(አሳዬ ደርቤ)
➖➖➖➖
የምንወዳት አገር መሪ እንደመሆንዎ መጠን ጠላታችንን ድባቅ መትተን ድል ልናስጨብጥዎ ብዙ ጊዜ ሞከርን፡፡ ፓርቲዎና እርስዎ ግን በዜጎች መስዋዕትነት የተገኘውን ድል ወደ ትግል እየቀየራችሁ አስቸገራችሁን።
እያንዳንዱን ውጤት ወደ ስኬት በመቀየር ፈንታ የትግሉ እኩሌታ ላይ ‹‹የአገራችን ቀንደኛ ጠላት የተበተነ ዱቄት ሆኗል›› የሚል ድል እያበሰሩ የሚያዘናጉ ሆኑብን፡፡ ጂራቱን እና ወገቡን የተመታውን እባብ ጭንቅላቱን ፈጥፍጦ ዳግም እንዳይነሳ ማድረግ ሲቻል ‹‹ጂራቱን ከተመታ መሞቱ አይቀርም›› ብለው ወደኋላ እየተመለሱ በጠበጡን፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡-
በጦር ሜዳ ላይ ይቅርና በሩጫው ሜዳም ላይ አትሌቶች ወደ ፊት እየገሰገሱና ወደኋላ እየተመለሱ ተጋጣሚያቸውን ያዳክማሉ፡፡ የተሻለ ጉልበትና ፍጥነት ያላቸውም በውድድሩ ፍጻሜ ላይ ድል ያደርጋሉ፡፡
እርስዎ ግን አትሌቶቹ ውድድሩን እስኪጨርሱ በመጠበቅ ፈንታ በሩጫው መሃከል ላይ ‹‹ይሄን ያህል ከፊት ከፊት በመገስገስ አቅማችሁን ካሳያችሁ በቂ ስለሆነ ወደኋላ ተመለሱ›› ወይም ‹‹አቋርጧችሁ ውጡ›› የሚሉ አሰልጣኝ ሆኑብን፡፡ በሆነ ስቴዲየም ላይ ጎል አግብቶ መምራት የቻለ ቡድኑን ‹‹ቀሪውን አርባ አምሥት ደቂቃ ደግሞ የምንጫወተው በሌላ ስቴዲየም ነው›› ብሎ በእረፍት ሰዓት ከእነ ቡድኑ የሚጠፋ አሰልጣኝ ሆነው አስቸገሩን፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡-
እስካሁን ድረስ ኢትዮጵያ መቆየት የቻለችው የእርስዎ ፓርቲ ሕዝብና አገርን ማስተዳደር ስለቻለ ሳይሆን መንግሥቱን እና አገሩን የሚያስተዳድር ሕዝብ በመፈጠሩ ነው፡፡ መንግሥት ሲቸገር የእለት ጉርሱን ሰጥቶ ጦሙን የሚያድር፣ አገር ስትደፈር ሕይወቱን የሚገብር፣
ሊያፈርሱት ሲሞክሩ እንቢኝ ብሎ የሚጣመር፣ መንግሥት የተወሰደበትን የዲፕሎማሲ ብልጫ ለማስመለስ ትዊተር ላይ ሲዘምት የሚያድር፣
የኢትዮጵያ ጠላቶችን የሚያጓጓ ምርጫ ሲዘጋጅ በሚፈልገው ፈንታ የማይፈልጉትን መርጦ እቅዳቸውን የሚያጨናግፍ፣
ምዕራባውያን በደካማ መንግሥቱ ላይ ሲያሴሩበት ማንም ሳይጠራው ‹‹እጃችሁን አንሱ›› ብሎ በአደባባይ የሚሰለፍ፣ አሸባሪ ሲነሳ ስንቅና ትጥቁን ችሎ እንደ ወታደር የሚሰለፍ "መንግሥታዊ ሕዝብ" በመፈጠሩ ነው፡፡
በበቂ ምክንያት ከትግራይ ወታደርዎን ባወጡ ማግሥት ያላንዳች ምክንያት ከኮረምና ከአላማጥም ሲደግሙት ‹‹ለምን?›› በማለት ፈንታ ‹‹ከባድ አደጋ አጋጥሞት ይሆናል›› በሚል ምክንያት ግራካሶ ላይ ዳግም ለመሰዋት ተሰልፎ የሚወጣ ሕዝብ በየስፍራው በመፈጠሩ ነው፡፡
የእርስዎ መንግሥት ግን…
ዛሬ ከሕዝቡ፣ ነገ ከምዕራቡ ጋር እየተሰለፈ የሚወዛገብ፣ ከድክመቱ ተምሮ ጠንካራ በመሆን ፈንታ በቁማርና በሤራ ጨዋታ የሚተበተብ፣ በማፈግፈግ ሰበብ ወታደሩን እየሳበ ሕዝቡንና አገሩን ለአሸባሪ የሚያስረክብ፣ በደገፉት ቁጥር እራሱን አንቅፎ እየጣለ መሬት ለመሬት የሚሳብ፣
ጦር ሜዳ ላይ ክላሹን ጥሎ ችግኝ መትከል የሚያስብ፣ በእራሱ አመራር እንዝላልነት መሳሪያውን እና ጦሩን ለጠላት የሚያስረክብ፣ በአሉላ ሥም የተሰየመ የክህደት ዘመቻ ሲሰነዳ የችግን ተከላ ዘመቻ አውጆ የሚያነጅብ… ሆኖ አሸናፊውን ሕዝብ ተሸናፊ ለማድረግ ጥረት ማድረጉን ቀጥሏል፡፡
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡- ጠላታችን ጠላትዎ መሆኑን እረዳለሁ፡፡ ትግላችን ግን ትግልዎ ነው ወይ? ድላችንስ ድልዎ አይደለም ወይ?
➜ለምን ይሆን በስንት ትግል የተገኘውን ድል ወደ ሌላ ትግል የሚቀይሩብን?
➜ለምን ይሆን አገሩን እና ሕዝቡን በመጠበቅ ፈንታ ‹‹ትተኸን አትሄድም›› እየተባለ በሕዝብ የሚጠበቅ ወታደር የፈጠሩብን?
➜አሸባሪው ክላሽ አስይዞ ያዘመታቸውን ሕጻናት ላለመጉዳት ቤታቸው ውስጥ ጡጦ ይዘው የተቀመጡት ለጥቃትና ለስዴት የሚዳረጉት እስከ መቼ ድረስ ነው?
➜የተናጠል ተኩስ አቁሙን ሰርዘው በሙሉ አቅምዎ የምድርና የአየር ጦርዎን በማንቀሳቀስ ለአሸባሪው የሚመጥን መልስ የሚሠጡት ጦርነቱ የትኛው ከተማ ላይ ሲደርስ ነው?
➜አላማጣና ቆቦ ሆኖ ወልድያን ለማውደም የሚመኘውን ርሃብተኛ መንጋ ወደ ጉሬው መመለስ ያልተቻለው ከአሸባሪው ያነሰ ሕዝብ ወይስ ገንዘብ፣ ወታደር ወይስ አመራር፣ ትጥቅ ወይስ ስንቅ? ስላለዎት ነው?
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር፡- የምር ግን እርስዎም ሆነ ፓርቲዎ ይሄን ጦርነት በድል አጠናቅቆ የአገርን ቀጣይነት የማስቀጠል ፍላጎት አለው ወይ? እኔ አይመስለኝም፡፡ ምክንያቱም፡-
አገር መምራት የሚፈልግ መንግሥት እርሻውን አስትቶ ለውጊያ የጠራውን ገበሬ ጦር ሜዳ መሃከል በትኖ አይጠፋም፡፡ ጦር መሣሪያ አስይዞ ያስገባውን ወታደር በቅጽበታዊ ውሳኔ ባዶ እጁን እያስወጣ ጠላቱን አያስታጥቅም፡፡ ሕዝቡን እና ከተማውን ለተራበ ጅብ አያስረክብም፡፡ በአሸባሪ የተሞላውን ቀጠና ማጽዳት ሲገባው የጨዋታውን ሜዳ ቀይሮ ደጀኑን አያስወጋም፡፡ በጦርነት መሃከል ሠራዊት ምልመላ ውስጥ አይገባም፡፡
የሆነው ሆኖ ግን ከአሸባሪ ጋር የሚደረገው ውጊያ መንግሥታዊና አገራዊ ነው በማለት እስካሁን ብዙ ዋጋ ከፍለናል፡፡ ከእንግዲህ በኋላ ግን ይብላኝ ለአገራችን እንጂ በእኛ ላይ የመጣውን ጥቃት ስደተኛ በመሆን ፈንታ አርበኛ ሆነን እንመክተዋለን፡፡
በተመረጠው ደካማ መንግሥት ፈንታ የጎበዝ አለቆቻችንን መርጠን ለእራሳችን ጥያቄ የእራሳችንን መልስ እንሰጣለን፡፡ በእኛ ሕይወት የሁሉንም አሸናፊነት ማረጋገጡ ቢቀርም በእራሳችን ትግል የእራሳችንን ድል እንደምንጎናጸፍ አንጠራጠርም፡፡ ያንንም ማድረግ ጀምረናል፡፡
አበቃሁ፡፡
14 336
#ስለአፋር_ልዩሃይል_ከስፍራው_የተላከ_ምስክርነት
አሳዬ ደርቤ
➖➖➖
➜ለተጠማ ወተት፣ ለጠገበ ወራሪ ጥይት የሚያጠጡ፤
➜አገራቸውና ክብራቸው በተደፈረ ማግሥት እንደ እሳት ገሞራ እየተንተከተኩ ገንፍለው የወጡ፤
➜ጥይታቸው መክሸፍ፣ እርሳሳቸው ዒላማውን ስቶ በየቦታው ማቸፍቸፍ የማያውቅ፤
➜በእንበር ተጋዳላይ ሚዚቃ እየጨፈረ የገባውን መንጋ በታጣፊ ክላሻቸው ተቀብለው "ዋይ ዋይ" ያስባሉ፤
➜መዋጋት ብቻ ሳይሆን ማዋጋት የሚችሉ፤
➜ድንበራቸውን ጥሶ የገባውን አሸባሪ ደረቱ ተቦዳድሶ እንዲቀር በማድረግ ሰተት ብሎ ከሰው ክልል መግባትና በሰላም መውጣት የሚለያዩ መሆናቸውን ያሳዩ፤
➜በጠላት ጦር መማረክን፣ በውጊያ ላይ ሽሽትን የማያውቁ፤
➜የአሸባሪውን ሠራዊት ወደ አጽምነት በመቀየር ለወደፊቱ ነዳጅ የማምረት እድል ያለው ምድር የፈጠሩ፤
➜በመጀመሪያው ዙር የሕግ ማስከበር ዘመቻም ሆነ በሁለተኛው ዙር ዘመቻ አሸባሪውን በመደምሰስ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ መሆናቸውን ያስመሰከሩ፤
#Share በማድረግ ክብራችንን እንግለጽላቸው
14 336
ጫት ይታገድልን
(አሳዬ ደርቤ)
➖➖➖
ጫቱን እያላመጠ ጠላቱን ከሚጠብቅ ዜጋ ይልቅ ጭሳ ጭሱን እየሳበ ባላንጣውን የሚያራውጥ መንጋ እጅግ የተሻለ ነው።
ጋሌሳውን ሲጨፈጭፍ ውሎ ምርቃናና ፍርሐት ሲሰማው "አሸባሪው እየመጣ ነው" ብሎ ቤቱን እና ሰፈሩን ጥሎ ከሚሸሽ ወጣትም፣ አጤ ፋሪሱን ምጎ የሚዋደቀው ወጣት የተሻለ ምራል አለው።
እናም እንላለን....
ከአሸባሪው ጋር የሚደረገው ጦርነት እስኪጠናቀቅ ድረስ አማራ ክልል ላይ ምንም ዓይነት ጫት እንዳይጓጓዝ መደረግ አለበት። ያኔ በሱስ የተለከፈው ሁላ ፍርሐቱን አሽቀንጥሮ አሸባሪው ላይ መተኮስ ይጀምራል።
#Share አድርጉት
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
