ch
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览

频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 336 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 651,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 347

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 336 名订阅者。

根据 26 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -104,过去 24 小时变化为 -8,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 35.99%。内容发布后 24 小时内通常能获得 12.61% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 158 次浏览,首日通常累积 1 808 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 30

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 27 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。

14 336
订阅者
-824 小时
-327
-10430
帖子存档
ኃላፊነቱንና ሥራውን ጥንቅቅ አድርጎ የሚሠራ ጠንካራና ታማኝ መንግሥት ያለን ይመስል በሁሉም ጉዳዮች ላይ "ዝም በሉ" ማለት አይነፋም። ይህ መንግሥት እንደ አሮጌ መኪና በግፊት የሚንቀሳቀስ ስለሆነ እውነተኛ መረጃዎችን ይዘን ጫና ልናደርግበት ይገባል። ከታች ያለውን ሊንክ በመጠቀም ፌስቡክ ላይ ያገኙናል። https://www.facebook.com/Asaye-Derbie-100999818947578/

ቴዎድሮስ ጸጋዬ (በአማራ ፈረስ፣ የትግራይ ንጉሥ) ➖➖➖➖ ➜የኢትዮጵያን ሥም በተደጋጋሚ ሲጠራ አገር ወዳድ ይመስልኻል። እሱ የሚወዳት አገር ግን ከህውሓት ውጭ በማንም መመራት የምትችል አይደለችም።
ቴዎድሮስ ጸጋዬ (በአማራ ፈረስ፣ የትግራይ ንጉሥ) ➖➖➖➖ ➜የኢትዮጵያን ሥም በተደጋጋሚ ሲጠራ አገር ወዳድ ይመስልኻል። እሱ የሚወዳት አገር ግን ከህውሓት ውጭ በማንም መመራት የምትችል አይደለችም። ➜"ተመሳሳይ ባሕልና ሃይማኖት ያለን ሕዝቦች ነን" በሚል ስብአት የትግራይን ንጉሥ፣ በአማራ ፈረስ አራት ኪሎ ማድረስ ይፈልጋል፤ ➜ደካማ የሚለውን ጠቅላይ ሚኒስትር አውርዶ በጥንካሬያቸው የሚታወቁትን አቶ ታምራት ላይኔ እና ስዬ አብርሐን የሚወዳት አገሩ መሪዎች ማድረግ ይመኛል፤ ➜ከወደደህ ድክመትህ አይታየውም፣ ከጠላህ ደግሞ ለተቸገሩ ወገኖች ስትረዳ ቢመለከትህ እንኳን "ሊጸድቅ ፈልጎ እንጂ ደግ ስለሆነ አይደለም" በማለት ያንቋሽሽኻል፤ ➜የዚች አገር ብቸኛ ችግር ዶክተር ዐቢይ የተባለ ጠቅላይ ሚኒስትር ነው ብሎ ያስባል። በዚህም የተነሳ "ጌታቸው ረዳ" የተባለ ወንጀለኛ በፈጸመው ወንጀል ጠሚው ላይ ማደኛ ማውጣት ይፈልጋል። ➜"ሰሜነኞቹን ማስማማት" በሚል ጭንብል አማራን እና ኦሮሞን ለማጣላት ያሤራል። ይሄውም ተንኮሉ ከተባነነበት ጊዜ አንስቶ አማራ ጠል ሆኖ በግልጽ ከመከሰትም አልፎ የዚህን ሕዝብ ጠላቶች በማሰባሰብ ላይ ይገኛል። ➜በኢትዮጵያ ባንድራ የሚንቀሳቀስ እልም ያለ የአገር ባላንጋራ #share

ሰበር መረጃ (አሳዬ ደርቤ) ➖➖➖ የአሸባሪው ድርጅት መሪ የሆኑት ዶክተር ደጺ ትናንት ለቡድናቸው ያቀረቡት የ8 ወር ሪፖርት፡- ➜ጦርነቱ እንደተጀመረ ሰሞን የጠላትን ጉዞ ለመግታት ሲባል ሰባት ድልድይ ሰብረን ከጥቅም ውጭ አድርገናል፡፡ ➜የእርሻ ሥራን በተመለከተ ከ200 ኪሎሜትር አስፓልት እና የአክሱምን ኤርፖርት ሙሉ በሙሉ ማረስ ተችሏል፡፡ ➜መከላከያ ሠራዊቱ መቀሌን ከመቆጣጠሩ በፊት በሠራነው አመርቂ ተግባር በኢፈርትና በግል ባለሃብት ተይዘው የነበሩ ፋብሪካዎችን በማውደም ለአራት ኪሎ መንግሥት ምንም አይነት ጥቅም እንዳይሰጡ አድርገናል፡፡ ➜ወደ ትግል ከሄዱ አመራሮች መሃከል አብዛኞቹ በሕይወት ያሉ ሲሆን ሥዩም መስፍንን ጨምሮ ሦስት አመራሮቻችንን ግን ተሰውረውብናል፡፡ ➜የዓለም አቀፍ ሕግጋትን ወደ ጎን በመተው ካዘመትናቸው ሕጻናትና ሴቶች መሃከል ግማሽ የሚሆኑት 31ኛ ክፍለ ጦርን 31 ጊዜ ሙሉ በሙሉ በመደምሰስ ጂጋኑ መሆናቸውን ሲያስመሰክሩ ግማሾቹ ታጣቂዎች ደግሞ መስዋዕትነት ከፍለው ንጹሐን እንዲሆኑ ተደርገዋል፡፡ ➜በአገር ውስጥ ያሰማራነው ጦር የኢትዮጵያን ሠራዊት በመማረክ ሂደት ውስጥ ያሳየውን ክፍተት ለመሙላት ሲባል በአሥር ሺህ የሚቆጠሩ ጂጋኑዎች የጠላትን ሚሊታሪ ለብሰው እንዲማረኩ ተደርጓል፡፡ ➜በስታሊን የሚመራውና በውጭ አገር ያለው ጦራችን ግን የኢትዮጵያን ሕዝብ ጨርሶ ወደምሥራቅ አፍሪካ በመዝመት ከፍተኛ ጭፍጨፋ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ➜ትግሉን ለመምራት የስንቅና የትጥቅ ችግር ቢያጋጥመንም ካይሮና ካርቱም ላይ ካለው የፌደራል መንግሥታችን ጋር በመነጋገር ችግሩን ለመፍታት በመሞከር ላይ እንገኛለን፡፡ ➜ከዚህ ባለፈም መከላከያ ሠራዊቱና የአማራ ልዩ ሃይል ለቅቆ ወደ ወጣባቸው የራያ አካባቢዎች ያሰማራነው ጦር ትጥቁን አኑሮ ስንቁን እንዲዘርፍ በማድረግ የተወሰነ ቀለብ ማግኘት ተችሏል፡፡ አንዳንዶቹንም ለመጠቃቀስ ያህል.. ➖900 ኩንታል ዱቄት ➖80 ኩንታል ሰላሱት ➖400 ሊትር ዘይት ➖20 ኩንታል ድፍን ምሥርና 10 ኩንታል ክክ ምሥር ➖400 ኩንታል ጥሬ ጨው ➖7 ኩንታል የአጥሚት እህል በቁጥጥር ስር አውለናል፡፡ #share 😁

➜ኮሮናን እንከላከል ሲሉ የነበሩ ከያኒያን አሸባሪ ሲነሳ ምነው ዝም አሉ? ➜አርቲስቱ'ስ ከናይት ክለብና ባር ወጥቶ ሑርሶ ላለው ወታደር የሚዘፍነው መቼ ነው? አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ የኪነጥበብ ፋይዳ በሰላማዊ አገር ላይ ሰላም የሚሰማው ፍጡር ሰብስቦ መድረክ ላይ በማነብነብ ብቻ የተወሰነ አይደለም፡፡ ሲጀመርም ጦርነት በሌለበት የብስ ላይ ስለ ሰላም መስበክ እርባና የለውም፡፡ ጥላቻ ከሌለ ፍቅር ርእስ አይሆንም፡፡ ኪነት ደግሞ እንደ ከያኒ በግጭትና ትርምስ ጊዜ ደብዛዋን አጥፍታ በእርጋታው ዘመን ሱፏን እና የባሕል ልብሷን ተጎናጽፋ ‹‹ብዬ ነበር›› እና ‹‹እንዲህ ሆኖ ነበር›› እያለች መድረክ ላይ የምትፏልል አይደለችም፡፡ ያለፈውን ብቻ ሳይሆን ገሃዱንም የምታወራ ናትና… አድባሯም በተወሰኑ ቲያትር ቤቶችና መድረኮች ላይ ታጥሮ የተቀመጠ ሳይሆን በመላው ዩኒቨርስ ላይ እንደ ንፋስ የሚነፍስ ነው፡፡ ይሄውም የጥበብ ንፋስ ለጸሐፊያን ርዕስና ስንኝ ያቀብላል፡፡ ለሙዚቀኞች ዜማ ሹክ ይላል፡፡ ከእነዚህም ጠቢባን መሃከል አንዳንዶቹ ሥራቸውን ለማቅረብ ምቹ ጊዜና ምቹ ስፍራ ይፈልጋሉ፡፡ ገቢ የሚያስገኝ የእራሳቸውን መድረክ ማዘጋጀት ይሻሉ፡፡ አንዳንዶች ግን ታዳሚ በመጥራት ፈንታ ሕዝቡ ወዳለበት ይሄዳሉ፡፡ በምቹ ጊዜ ብቻ ሳይሆን በአደጋ ጊዜም የጥበብን ፋይዳ ያሳያሉ፡፡ ሕዝብ ሲሸበር ያረጋጋሉ፡፡ አገር ስትታፈን ድምጽ በመሆን ፍቅራቸውን ይገልጻሉ፡፡ ወራሪና አሸባሪ ሲነሳባት ከአርበኛው ወይም ከወራሪውና ከባንዳው ወገን ተሰልፈው የጦሩ ጉልበት ይሆናሉ፡፡ ከዚህ አንጻር በአንድ ጦር ሜዳ ላይ የሚገናኙ ባላንጣዎች ሁሉ ተመሳሳይ ጥይት እንጂ ተመሳሳይ ምክንያት ያሏቸው አይደሉም፡፡ ስህተት እና እውነት፣ ባርነትና ነጻነት፣ ሰላምና ጦርነት፣ ልውረርህ ባይና አትንኩኝ ባይነት፣ አሸባሪና አረጋጊ፣ ልግደልህ ባይ እና አልሞትም ባይ ናቸው የሚታኮሱት፡፡ ይሄም ሁኔታ የኪነጥበብ ሰዎችን ገለልተኛ በመሆን ፈንታ ወገንተኛ ያደርጋቸዋል፡፡ በዚህም ሂደት ወራሪ ወይም አሸባሪ ጦሩን ሰብቆ ሲነሳ ጥቅመኛ ከያኒያን የከበደ ሚካኤልን ፈለግ ይከተላሉ፡፡ ሐቀኛ ከያኒያን ግን ብዕራቸውንና ማይካቸውን ይዘው ከአርበኛው ጎን ይሰለፋሉ፡፡ ልግደላችሁና ላፍርሳችሁ ባይ ጠላት ሲነሳ ከአገራቸውንና ከሕዝባቸው ጎን ተሰልፈው ዞር በል ይላሉ፡፡ ወስላታ ከያኒ አድዋ ሲያልፍ ጠብቆ ስለ ድሉ ሲተርክ፣ ጀግኖቹ ግን ባይዋጉ እንኳን ትግሉን ያቀጣጥላሉ፡፡ ከዚህ አንጻር ባሁኑ ሰዓት ከአገር አፍራሽ አሸባሪዎች ጋር የገጠምነውን ጦርነት ከአድዋ ጋር ማነጻጸር ተገቢ ባይሆንም አጼ ቴዎድሮስ ኢትዮጵያን በቅርጫ መልክ ከተከፋፈሉ መሳፍንቶች ጋር ሲያደርገው ከነበረው ውጊያ ግን የሚያንስ አይደለም፡፡ ይህ ዘመቻ አገራቸውን በሚወዱና ኢትዮጵያን ለማፍረስ እስከ እንጦሮጦስ ድረስ በሚወርዱ አሸባሪዎች መሃከል የሚደረግ እንደመሆኑ መጠንም… ➜ዝምታችሁን አሽቀንጥራችሁ አቋማችሁን በማስተጋባት ለአገራችሁ ያላችሁን ፍቅር ማሳየት ➜በጦር ግንባርና በማሰልጠኛ ጣቢያዎች ላይ የኪነጥበብ ድግስ በማዘጋጀት ጦሩን ማበረታታት ➜የገቢ ማስገኛ መድረኮችን ማሰናዳት ➜የብሔራዊ ቲያትር መድረካችሁን ወደ ሁርሶና ብር ሸለቆ ማሰልጠኛ ጣቢያዎች ማዛወር ➜የተነሳብን አሸባሪ ሕይወትን ብቻ ሳይሆን አገርንም የሚያሳጣ ነውና ለኮሮና ያዋላችኋትን ኪነት አሁንም ተግባራዊ ማድረግ ይጠበቅባችኋል፡፡ #Share

ሰበር❗️❗️ #የጌታቸው_ረዳ_ግለ_ሒስ (አሳዬ ደርቤ) ➖➖➖➖ "ከዓመታት በፊት የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች እሳትና ጭድ ናቸው" የሚለው ያልተገራ ንግግሬ ቄሮን እና ፋኖን አጣምሮ ህውሓትን ያስባረረ መሆ
ሰበር❗️❗️ #የጌታቸው_ረዳ_ግለ_ሒስ (አሳዬ ደርቤ) ➖➖➖➖ "ከዓመታት በፊት የአማራና የኦሮሞ ሕዝቦች እሳትና ጭድ ናቸው" የሚለው ያልተገራ ንግግሬ ቄሮን እና ፋኖን አጣምሮ ህውሓትን ያስባረረ መሆኑ ግልጽ ነው። ትናንት ደግሞ "የአማራ ኤሊት ላይ የምናወራርደው ሒሳብ አለን" ብዬ በነዛሁት ፕሮፖጋንዳ ድርጅታችን የሚጎዳ ተግባር ፈጽሜያለሁ። በዚህም ንግግሬ የተቆጣው የአማራ ወጣት ሰሳ እንዳዬ አቦሸማኔ ጅማቱን ቋጥሮ ከመነሳቱም በላይ "ኢትዮጵያን ለማፍረስ እንጦሮጦስም እንወርዳለን" ማለቴ ደግሞ መላውን ኢትዮጵያዊ ያንቀሳቀሰ ሆኗል። በመሆኑም የብሽቀትና የሽንፈት መንፈስ ውስጥ ሆኜ የምናገራቸው ነገሮች ሁሉ ለድርጅታችን ጠቃሚ መሆን ሲገባቸው አውዳሚ እየሆኑ ነው። በዚህ ላይ ደግሞ ፓርቲያችን በሕይወት ያለ ይመስል መቀሌና ቆላተንቤን ላይ ሆኜ "ጎንደርን እንቆጣጠር ወይስ ደብረ ብርሐንን?" እያልኩ እንደ ቀልድ የማወራቸው ነገሮች የሕዝባችንን ጆሮ በባዶ ተስፋ እየሞሉ ነው። ስለሆነም ጓዶች በገመገሙኝ መሠረት ከዚህ አስቀያሚ ስሜት እስክወጣ ድረስ ላልተወሰነ ጊዜ ካለሁበት ሃላፊነት ገለል ማለት ይኖርብኛል።" #Share

በነገራችን ላይ "ባንዳ" የሚባለው ከውጭ ወራሪ ወይም ከአሸባሪ ጋር ተባብሮ አገሩን የሚወጋው ብቻ አይደለም። ይልቅስ፦ ➜በሽምግልና ሥም ወራሪን እና አሸባሪን መታደግ ➜አገርን ከጭንቅ የሚገላግል ዘመቻ ሲካሄድ በማበረታት ፈንታ በንቀት መመልከት ➜ወጣቱ አገሩን እና ሰላሙን እንዳያስከብር "አርፈህ ቁጭ በል" እያሉ መቀስቀስ ➜አለመዝመትን የአራድነት እና የሥልጣኔ መገለጫ አድርጎ መቀላመድ ➜በአሸባሪና በተሸባሪ መሃከል የሚደረግ ትግልን "በወንድማማቾች መሃከል የሚደረግ ነው" እያሉ መቦትረፍ ➜ለአገሩ በሚዋደቅ ሠራዊት ላይ ሙድ ለመያዝ መጋጋጥ ➜በሰላም ሰባኪ ጭምብል የአሸባሪን እድሜ ለማርዘም ጥረት ማድረግ ➜በደምና በላብ አገርን ማቆም ባይቻል እንኳን በገንዘብና በሐሳብ መደገፍ ሲገባ እራስን ከጨዋታ ውጭ አድርጎ መቀመጥ . . . እነዚህ ሁሉ ባሕሪያት በግልገል ባንዳ ላይ የሚታዩ የመጀመሪያ ደረጃ የመበንደድ ምልክቶች ናቸው። 😁 ከታች ያለውን ሊንክ በመጠቀም ፌስቡክ ላይ ያገኙናል። https://www.facebook.com/Asaye-Derbie-100999818947578/

የመለስ ደብዳቤ አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ጌታቸው አሰፋ በተባለ የደህንነት ሰው የሚመራው ህውሓት እየፈጸመው ያለውን ጥፋት ከእነ ሥዩም መስፍን አንደበት ስለሰማሁ ‹‹ሕዝባችን ደህና ነው ወይ? አገሩስ እንዴት ነው›› እያልኩ አልዘበዝብም፡፡ ይልቅ ሰሜን እዝ ላይ ጥቃት በፈጸማችሁ ማግሥት ከመላው ኢትዮጵያዊና ኤርትራዊ ጋር ለመዋጋት የደፈራችሁት ምን ምኑን ብታጨሱት ነው?›› ማለት እፈልጋለሁ፡፡ ጦርነት የተባለውን የአጤዎች ዘመን ጥንታዊ ጨዋታ ወደዚህ ዘመን አምጥታችሁ ‹‹ባሕላዊ ጨዋታችን ነው›› ለማለት የበቃችሁት ምን አይነት አጤ ፋርስ ብታጨሱ ነው? ‹‹የሰው ልጅ ከዝንጀሮ ነው የመጣው›› የሚለውን የቻርለስ ዳርዊን ‹‹የዝግመተ ለውጥ ቲዮሪ›› ደብረ ጽዮን የተባለ ዘገምተኛ ‹‹የለም የለም የሰው ልጅ ነው ወደ ዝንጀሮ የሚመለሰው›› ብሎ ለመቀየርና ቆላ ተንቤን ዳገት ላይ ሕዝብ ለማስፈር የደፈረው ስንት አምባሻ ቢበላ ነው! በዘመኔ ካከናወንኳቸው ተግባራት ሁሉ ትልቅ ቦታ የምሠጠውን የሕዳሴውን ግድብ ከግብጽና ሱዳን ጋር ተባብራችሁ ለማውደም የተነሳሳችሁት ስንት በለስ በልታችሁ ብትጠግቡ ነው? ክልላዊ ምርጫ ለማድረግ የደፈራችሁትስ ምን አይነት በርጫ ብትቅሙ ነው? ውዳሴ ማሪያም በምትደግሙት ዘመን ‹‹ታሪክ እንደግማለን›› ብላችሁ ያንኑ ጠላት በዚያው የትግል ስልት የገጠማችሁት ብሎም በስንት ጥበብ ሕይወቱን ያሻሻልኩለትን ሕዝብ ሠላሳ ዓመት ወደ ኋላ የመለሳችሁትስ ልክ እንደ ገንዘባችሁ ሁሉ ግንዛቤያችሁን የትኛው ባንክ አስቀምጣችሁት ነው? (ስዊዝ ባንክ በከበሩ ጌጦች ፈንታ የደነቆሩ ጭንቅላቶች ማስቀመጥ ጀመረ እንዴ? ) ሲቀጥል ደግሞ በፖለቲካው ዓለም ውስጥ ቋሚ ጠላትም ሆነ ወዳጅ አለመኖሩ እየታወቀ ዐማራን ያህል ባለውለታ ሕዝብ የእድሜ ልክ ጠላት አድርጋችሁ እድሜያችሁን እንዴት ታሳጥራላችሁ? እኔ እንኳን ያኔ ፈላጭ ቆራጭ በነበርኩበት ዘመን በብሔር ብሔረሰቦች ዘንድ በጠላትነት እንዲታይ በድብቅ ማኒፌስቶ ውስጥ ውስጡን ከመስራት ባለፈ ‹‹አማራ የትግራይ ጠላት ነው›› ብዬ በአደባባይ ለመናገር አልደፈርኩም፡፡ ያንንም ያደረግኩት በአማራና ኦሮሞ መሃከል ሰላማዊ ግንኙነት በተፈጠረ ማግሥት ሥልጣናችን ስለሚንኮታኮት እንጂ ወልቃይትን እና ራያን የተቀማው ብሎም በትግሉ ወቅት ከፍተኛ ሚና የነበረው የአማራ ሕዝብ የክልላችን ጠላት ስለነበረ አይደለም፡፡ እናንተ ግን እንደ ጆርጅ ኦርዌል በጎች ‹‹አራት እግር ወዳጅ፣ ሁለት እግር ጠላት›› ተብሎ ከተነገራችሁ ያንኑ እያነበነባችሁ የምትኖሩ በመሆናችሁ አማራውን ብቻ ሳይሆን ሁለት እግር ያለውን የአገሪቱን ሕዝብ ሁሉ ጠላት በማድረግ የመጀመሪያውን ጥይት ተኮሳችሁ፡፡ የሆነ ሆኖ ግን ከመራር እውነት ይልቅ ጣፋጭ ውሸት እንደምትወዱ ባውቅም በሃይል የተወሰደ መሬት ከወሳጁ ጋር የሚቆየው የቀድሞው ጉልበት እስካለ ድረስ ብቻ መሆኑን ልነግራችሁ እፈልጋለሁ፡፡ የሃይል ሚዛን እና ዘመን ሲገለባበጥ ግን ‹‹እንኩ›› ማለት እንጂ ‹‹እንቢ›› ማለት ስለማይጠቅም በጦርም ሆነ በድርድር አሸናፊ በማትሆኑበት መሬት ላይ እልቂት መፍጠራችሁን ታቆሙ ዘንድ አሳስባችኋለሁ፡፡ ሲቀጥል ደግሞ ክልልን ለመገንጠል የሚያስፈልገው አንቀጽ 39 የተጻፈበት ሕገ-መንግሥትና ግልፍተኝነት ሳይሆን የተትረፈረፈ የተፈጥሮ ሃብትና ሊተገበር የሚችል ጠቃሚ ምክንያት ነው፡፡ እናንተ ደግሞ ስለመገንጠል የምታወሩት አልማዝና ወርቅ ወይም ደግሞ ነዳጅ አግኝታችሁ ሳይሆን በወ/ሮ አልማዝና በአቶ ወርቁ ተናዳችሁ ነው፡፡ በተፈጥሮ ሃብት በልጽጋችሁ ሳይሆን ብልጽግና ጋር ተጣልታችሁ፣ ሠላሣ ዓመት ሙሉ የተገነባውን አፍርሳችሁና የወሰዳችሁትን መሬት ተነጥቃችሁ ነው፡፡ ስለሆነም ‹‹እንገነጠላለን›› የሚል ፉከራችሁን አቁማችሁ ‹‹አንቀጽ 39 ይሰረዝልን›› ማለት እንዲትጀምሩ አሳስባችኋለሁ፡፡ . በመጨረሻም ዝና የነበረው ነገር ሁሉ እርጅና ይከሠትበታል፡፡ ሕይወት ያለው ነገር ሁሉ ይሞታል፡፡ ልክ እንደዚሁ ሁሉ የትኛውም ሥርዓት ያረጃል፡፡ ለምሳሌ ያህል ቀኀሥ (ጃንሆይ) የተወገዱት በእሳቸው መጃጀት ብቻ ሳይሆን ዘውዳዊው ሥርዓት እንዳጠቃላይ አክትሞለት ስለነበር ነው፡፡ እኔም በሕይወት ብኖር ኑሮ ሶሻል ሚዲያ ባልነበረበትና ብሔር ብሔረሰቦች ባልነቁበት ዘመን የነበረውን ‹‹የከፋፍለህ ግዛው›› ሥርዓት አወዳደቁን ላሳምረው እንጂ ላስቀጥለው አልችልም ነበር፡፡ ምክንያቱም ያረጀውን ሥርዓት ከማዳን ይልቅ ሳላረጅ የመጣብኝን ሞት ማዘግየት ይቀለኛልና፡፡ ስለሆነም ባለፈ ትዝታ እና በጌታቸው ረዳ ብሽከታ መመሰጡን ትታችሁ ሐቁን በመጋፈጥ ‹‹ችግሩን በፈጠረው አእምሮ ችግሩን መፍታት ስለማይቻል›› ሥልጣናችሁን ለወጣቶች አስረክባችሁ አራት ኪሎን በማሰብ ቃሊቲን መጋፈጥ ይኖርባችኋል፡፡ እና ደግሞ እዚህ ያለው ቅጣት በጥልቅ ተሐድሶ ብሎም በሒስና ግለ ሒስ የሚታለፍ ስላልሆነ ወደ ጥልቁ ከመወርወራችሁ በፊት የዘረፋችሁትን መልሳችሁና የገደላችሁትን ሕዝብ ክሳችሁ ስትጨርሱ ‹‹አምላክ ሆይ ማረን›› እያላችሁ ቀንና ሌሊት ታለቅሱ ዘንድ እመክራችኋለሁ፡፡ #Share በማድረግ ፌስቡክ ላይ ያጋሩት

ክቡራትና ክቡራን የቀድሞ አካውንታችን ለ30ቀን በመታገዱ የተነሳ አዲስ የፌስቡክ ገጽ ከፍተናል። ስለሆነም ከሥር ያለውን ሊንክ በመጫን ፎሎው እንድታደርጉና ገጹንም እንድታስተዋውቁ ከወገባችን ጎንበስ ብለን እንጠይቃለን። https://www.facebook.com/Asaye-Derbie-100999818947578/

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለትግራይ ሕዝብ ቀርቶ ለአሸባሪው ሃይልም ቢሆን ባለውለታ ነው" የምንልባቸው ምክንያቶች፦ አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ➜አሸባሪው ከፌደራል መንግሥቱ ምንም ዓይነት ትዕዛዝ በማይቀበልበት ሁኔታ
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለትግራይ ሕዝብ ቀርቶ ለአሸባሪው ሃይልም ቢሆን ባለውለታ ነው" የምንልባቸው ምክንያቶች፦ አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ➜አሸባሪው ከፌደራል መንግሥቱ ምንም ዓይነት ትዕዛዝ በማይቀበልበት ሁኔታ ከNGO ባለፈ መደበኛ በጀቱን እየላከ ይደግፋቸው ነበር ➜መቀሌ ላይ ተቀምጠው ውስኪ እየጠጡ በተለያዩ የሽብር ጥቃቶች ኢትዮጵያን ሲያምሷት ጠሚው ተመሳሳዩን በማድረግ ፈንታ አገሪቷን ትቶ ቤተ-መንግሥቱን ያሰማምር ነበር። ➜ህውሓት ክልላዊ ምርጫ አድርጎ ዳንኪራውን ሲረግጥ ጠሚው ችግኝ ይተክል ነበረ፤ ➜ጌታቸው ረዳ በየቀኑ በቲቪ እየቀረበ "ጨቅላው" እና "ወፈፌው" ሲለው፥ ጠሚው "ደብረ ጽዮንን እገዙት" እያለ ይመልስ ነበር 😁 ➜ጁንታው በየሳምንቱ እሁድ ወታደራዊ ትርዒት ሲያሳይ ጠሚው ቀበናን እያለማና ቀይ ቀበሮ እያላመደ ነበረ ➜አሸባሪው ሃይል ከፌደራል ተሹመው የሚላኩ የሰሜን እዝ አዛዦችን በመጡበት አውሮፕላን እየሸኘ ያለመጠን ሲጨማለቅ፥ ጠሚው አቅሙን ከማሳየት ይልቅ አቅም አልባ መባልን መርጦ ነበረ፥ ➜ትሕነግ ገዳም መግባት የሚገባቸውን አሮጊቶች መሳሪያ አስይዞ በቲቪ እያቀረበ ጥጋባቸውን ሲያሳይ፥ ጠሚው ከትሕነግ ጋር አስታርቁኝ" ከሚል ልመና ጋር ሽማግሌዎችን ሰብስቦ ወደ መቀሌ ይልክ ነበረ። ➜ከግብጽና ሱዳን ጋር መሥራታቸው አልበቃ ብሎ "ግድቡን ሽጦታል" እያሉ ሲያብጠለጥሉት ጠሚው በሩ ላይ ያለችውን ፒኮክ አሻግሮ እያዬ "ጌታ ይቅር ይበላችሁ" ይል ነበረ። 😁 ➜እንዳጠቃላይ አሸባሪው ሃይል ሰሜን እዝን ጨፍጭፎ በቅራቅርና በራያ በኩል ወደ ሸገር መገስገስ እስኪጀምር ድረስ ጠሚው ፓርክ ልማት ላይ ነበረ፥ . . ስለዚህ የትግራ ሕዝብ ጠምዶ መያዝ ያለበት ከውስጡ የወጣውን አሸባሪ እንጂ አራት ኪሎ ያለውን መሪ አይደለም። Share

‹‹ታሪክ እራሱን ይደግማል ወይ?›› ለሚለው ጥያቄ መንጌ የሰጠን አስገራሚ መልስ አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ‹‹አዎ ታሪክ እራሱን ይደግማል፡፡ ኢትዮጵያ ላይ ደግሞ በተመሳሳይ ታጋዮችና በተመሳሳይ የትግል ስልቶች ተመሳሳይ ታሪኮች ሲደገሙ እያየን ነው፡፡ ለማስረጃም ያህል... እኔ ኢትዮጵያዊ መሪ ብሆንም እነዚያ የእፉኝት ልጆች ግን አማራ መሆን ኩራት እንጂ ውርደት ያመጣ ይመስል ያለኝን ዜግነት ቀምተው የሌለኝን ማንነት በመስጠት እኔን ብቻ ሳይሆን ሥርዓቱንም ‹‹የአማራ ነው›› እያሉ ያጥላሉት ነበር፡፡ ባሁኑ ሰዓትም በእነሱው ሕገ-መንግሥት የሚመራውን ሥርዓትና የአራት ኪሎውን መንግሥት ‹‹የአማራ ነው›› እያሉ ያንኑ ስብከት ይደግሙት ይዘዋል፡፡ በሁለተኝነት ደግሞ ይህ አሸባሪ ሃይል የእኛን ሥም ለማጉደፍ ሲል የወለደውን ሕዝብ በቦንብ በመጨፍጨፍ እኛን ጠልቶ ከእሱ ጎን እንዲሰለፍ ያደርግ ነበር፡፡ አሁንም ወደ ጦርነት አስገብቶ እራሱ ባስገደላቸው ሕጻናት አስከሬን እየነገደ ነው፡፡ በሦስተኝነት ያኔ የዚህ ቡድን ደጋፊ የነበረችው አሜሪካ አሁንም የዚያው ጥገኛ ቡድን ደጋፊ ሆና ያንኑ ታሪክ ለመድገም እየጣረች ትገኛለች፡፡ ሌላው ደግሞ ይህ ቡድን በወቅቱ የነበረውን ርሐብ እንደ ትግል ስልት ይጠቀምበት ነበር፡፡ እኛም ድሃው ሕዝባችን በርሐብ እንዳያልቅ በሚል ስጋት በተዘዋዋሪ መልኩ አሸባሪውን ሃይል የሚደያደልብ ስንቅ ስናቀብል ነበር፡፡ አሁንም የተለመደው ርሐብ የትግል ስልት ሆኖ በዚያው ሕዝብ እነዚያው ግለሰቦች ያንኑ ታሪክ ለመድገም ሲሞክሩ የወቅቱ መንግሥትም እኛ በተሸነፍንበት መንገድ በመጓዝ ለትጥቅና ስንቅ መግዣ የሚውል መቶ ቢሊዮን ብር ሲጎዘጉዝ ከርሟል፡፡ በመጨረሻም ይህ አሸባሪ ቡድን ከእራሱና ከከርሱ ባለፈ አገር ቀርቶ ብሔር እንደሌለው ብናውቅም፣ ቡድኑ ግን ‹‹ብሔር ብሔረሰቦች›› እና ‹‹ዲሞክራሲያዊ መብቶች›› በሚሉ የትግል አጀንዳዎች ያጭበረብር ነበር፡፡ ይሄም ፕሮፖጋንዳው እኛ ጋር ከነበረው ድክመት ጋር ተዳምሮ የአማራውን እና የሌሎችንም ድጋፍ ስላስገኘለት ድል ማድረግ ቻለ፡፡ የሚገርመው ነገር ታዲያ 27 ዓመት ሙሉ ሥልጣን ላይ ሲቆይ ከእኛ የተረከባቸውን ብሔር ብሔረሰቦች መብትና ማንነታቸውን ሊያስከብር ቀርቶ ቁጥራቸውን ሳያውቅ ነው ከሥልጣኑ የተባረረው፡፡ ‹‹ምን ይሉኝን›› የማያውቀው በዝባዥ ሃይል ግን በዚያው የውሸት ትግል ተመሳሳይ ድል ለማግኘት እየዳከረ ነው፡፡ ሆኖም ግን ቻይናዊው የጦር ጄኔራል ሳን-ዙ ‹‹ተመሳሳይ ታጋዮች፣ በተመሳሳይ የትግል ሜዳ ላይ ከሚተገብሩት ተመሳሳይ የትግል ሥልት የሚገኝ ውጤት ሽንፈት ይባላል›› እንዳለው ወመኔው ሃይል የለኮሰው ጦርነት ሽንፈቱን ብቻ ሳይሆን የሞት ጽዋውንም የሚጎነጭበት ነው፡፡ . ምክንያቱም በተመሳሳይ የውሸት ፕሮፖጋንዳ ተታሎ ሁለት ጊዜ አገሩን የሚጎዳ ሕዝብ ስለሌለ ብሔር እያለ ሲያታልላቸው የኖሩት ሁሉ አሁን ላይ አገር ሆነው በሕብረት ዘምተውበታል፡፡ ያን ጊዜ በትከሻው አዝሎ ወደ ቤተ-መንግሥት የሸኘው የኤርትራ ጦርም አሁን ላይ ወደ መቃብር ቤት የሚሸኘው ሆኗል፡፡ በትግል ማኒፌስቷቸው ላይ ጠላት ብለው የፈረጁት አማራም ያኔ ከዜግነቱ ባለፈ አማራነቱን የማያውቅ በመሆኑ መንግሥት ሆነው ይገድሉት ዘንዳ ሲረዳቸው ነበር፡፡ ባሁኑ ሰዓት ያለው አማራ ግን እራሱን ብቻ ሳይሆን ጠላቱንም ለይቶ የተደራጀ በመሆኑ በዚያው ማኒፌስቶ ያንኑ ውጊያ ደግመው ጦርነት የለኮሶትን አሸባሪዎች ‹‹ትግሉን እንጂ ድሉን መድገም አትችሉም›› ብሎ እየደቆሳቸው ይገኛል፡፡ እኛም በሽብር ቡድኑ መቃብር ላይ የምንወዳት አገር አሸናፊነት እውን ሆኖ እስክናይ ድረስ ሞት እንዲታገሰን በመጸለይ ላይ እንገኛለን፡፡ ኢትዮጵያ ትቅደም!" #ሼር በማድረግ ለሌሎች ያጋሩት)

"መንግሥት ለመሆን በያዙት ሃላፊነት ሕዝብን ማገልገል እንጂ ገዢ ፓርቲ ሆኖ መመረጥም ሆነ 'የሽግግር መንግሥት መስርቻለሁ' እያሉ ማረጥረጥ አያስፈልግም" ብለው የሚያምኑት የአብን አመራሮች የክተት አ
"መንግሥት ለመሆን በያዙት ሃላፊነት ሕዝብን ማገልገል እንጂ ገዢ ፓርቲ ሆኖ መመረጥም ሆነ 'የሽግግር መንግሥት መስርቻለሁ' እያሉ ማረጥረጥ አያስፈልግም" ብለው የሚያምኑት የአብን አመራሮች የክተት አዋጁን ተቀብለው ከአሸባሪ ጋር የሚደረገውን ትግል በመምራት ላይ ይገኛሉ። ለአገራቸውና ለሕዝባቸው እውቀታቸውን፣ ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን የገበሩት ድንቅ የአማራ ልጆች ሕይወታቸውንም ጭምር ለመስጠት በራያና ወልቃይት ግንባር ተሰልፈው አሸባሪውን በመደምሰስ ላይ ይገኛሉ። ሥልጣን እና ጥቅም ፈላጊ ፖለቲከኞች ለእነሱ ወንበር የሚታገልላቸው እና የሚሞትላቸው ሕዝብ ያደራጃሉ። እንደ አብን ያሉት ግን ለሕዝባቸው ይታገላሉ። ለአገራቸው ይዘምታሉ! በጣም ነው የምንኮራባችሁ❗️ "ሐቅ ነው" የምትሉ ፌስቡክ ላይ Share አድርጉት!

ከአሸባሪው ቡድን ፍርፋሪ የሚጣልላቸው አሽከሮች "ቄሮ ሆይ ተነስ፥ ጁንታውን መልስ" እያሉ ይጠሩታል። የአቢቹ እና የአብዴሳ አጋ ልጆች ግን አሸባሪውን ለመደምሰስ መከላከያ ሠራዊቱን እና ልዩ ሃይሉን
ከአሸባሪው ቡድን ፍርፋሪ የሚጣልላቸው አሽከሮች "ቄሮ ሆይ ተነስ፥ ጁንታውን መልስ" እያሉ ይጠሩታል። የአቢቹ እና የአብዴሳ አጋ ልጆች ግን አሸባሪውን ለመደምሰስ መከላከያ ሠራዊቱን እና ልዩ ሃይሉን በመቀላቀል ላይ ይገኛል። የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልሽ አብዴሳም በሚገርም አቋም ተከስቶ የአሸባሪውን ውድቀት የሚያፋጥን ሆኗል። እንደ አጠቃላይ... በጌታቸው ረዳ ተብታባ አንደበት "እሳትና ጭድ" የተባሉት የአማራ ፋኖ እና የኦሮሞ ቄሮ እሳት ሆነው በመነሳት የአሸባሪውን ቡድን ጭድ እና አመድ ሊያደርጉት በሕብረት ተነስተዋል። የሲዳማው ኤጀቶ የፈጸመውን ገድል በኋላ እመለስበታለሁ። #Share

የክልላችን ፕሬዝዳንት የክተት አዋጅ ካወጁበት ቅጽበት አንስቶ መላው የአማራ ወጣት ቀፎው እንደተነካ ንብ ገንፍሎ በመውጣት ላይ ይገኛል። የአማራ ወጣት በዚህ ልክ ለሰላማዊ ሰልፍ ጥሪም ምላሽ ሰጥቶ አያውቅ!! ሸዋ ገነፈለ፥ ወሎ ታጥቆ ወጣ ጎጃም ዘራፍ አለ፤ ጎንደሬ ተቆጣ ድርድር አያውቅም ወትሮም የአማራ ሕዝብ፤ በአገሩ ለመጣ። #Share

ስለ ሶማሌ ልዩ ሃይል የደረሰን መረጃ፦ (አሳዬ ደርቤ) ➖➖➖ ➜ሰሜን ኢትዮጵያ ላይ የነጠፈውን አገራዊ ስሜት ወደ ምስራቅ ወስደው ነፍስ ዘርተውበታል፤ ➜የአሸባሪውን ሠራዊት ሲመለከቱ አጋንንት ያዩ ይ
ስለ ሶማሌ ልዩ ሃይል የደረሰን መረጃ፦ (አሳዬ ደርቤ) ➖➖➖ ➜ሰሜን ኢትዮጵያ ላይ የነጠፈውን አገራዊ ስሜት ወደ ምስራቅ ወስደው ነፍስ ዘርተውበታል፤ ➜የአሸባሪውን ሠራዊት ሲመለከቱ አጋንንት ያዩ ይመስል "አውዚቢላህ" እያሉ በሚገርም ቅልጥፍና ይረፈርፉታል፤ ➜ለአገር የሚከፈልን መስዋዕትነት እንደ ጽድቅ ይቆጥሩታል ➜ለደረት አልመው ትከሻ ሲመቱ የሳቱ ያህል ይሰማቸዋል፤ ➜የጀግንነታቸውን መጠን ስትመለከት "በሶማሌኛ ቋንቋ ውስጥ ፍርሐት የሚባል ቃል የለም ወይ?" ብለህ እንድትጠይቅ ያስገድዱኻል ➜የሞት ትርጉሙ ለአሸባሪው እጅ መስጠት ነው በማለት ይነግሩኻል **ስለሌሎች ልዩ ሃይሎች የደረሰንን መረጃ ደግሞ ነገ የምንለጥፈው ይሆናል! ሰላም እደሩ #Share

የኮሎኔል ደመቀ መልዕክት- ከወልቃይት (አሳዬ ደርቤ) ➖➖➖ በየትኛውም ጦርነት ላይ ከጦር ሠራዊት እና ከጦር መሳሪያ ብዛት ባልተናነሰ መልኩ አሳማኝ የትግል ምክንያትና ድል የማድረግ ጽኑ እምነት አሸናፊ ለመሆን ያስችላል፡፡ በዚህም መሠረት ‹‹ሕልውና›› የሚባል አሳማኝ የትግል ምክንያት ያለው ሕዝብ ልክ እንደኛ ክላሽ ይዞ ሲሰማራ፣ ምክንያት የለሽ ቡድን ግን በውጊያ ላይ ለመሳተፍ ከክላሽ በተጨማሪ ሃሺሽ ያስፈልገዋል፡፡ በሕልውናው እና በአገሩ ላይ የጥፋት እልቂት የተደገሰለት ሕዝብ ማንኛውንም መስዋዕትነት ከፍሎ አገሩንና ወገኑን አሸናፊ ሊያደርግ በአርበኝነት መንፈስ ሲነሳ፣ ባንዳውና አሸባሪው ሃይል ግን ከሞት ጋር ለመጋፈጥ የሚያስችል አበረታች እጽ ያስፈልገዋል፡፡ በገሃድ የሚያጋጥመውን ሽንፈት የሚያስተባብልበትም የውሸት ፕሮፖጋንዳ ማሰራጨት ይኖርበታል፡፡ ይህ የውሸት ፕሮፖጋንዳ ግን እራሱንና መንጋውን ከመደለል አልፎ በሕዝባችን እና በአገራችን ላይ ቅንጣት ታክሎ ተጽእኖ መፍጠር የለበትም፡፡ ሊፈጥርም አይችልም፡፡ ምክንያቱም ሕዝባችን እንኳን በፈጠራ ወሬ ይቅርና በገሃድም ‹‹ወንድምህን ገደሉት›› ሲባል ክላሹን ላጥ አድርጎ ወደ ገዳዩ ዘንድ በመገስገስ የወንድሙን ደም የሚያብስ እንጂ ‹‹እኔንም ይገድሉኛል›› ብሎ የሚሸሽ አይደለም፡፡ የጥይት ድምጽ ሲሰማም ተኩሱን ወደሰማበት ስፍራ ተንደርድሮ የሚሄድ እንጂ ጆሮውን አፍኖ ወደኋላ ለመሸሽ ባሕሉ አይፈቅድለትም፡፡ በተረፈ ያለነው ከጥይት በተጨማሪ በውሸት በሚደገፍ ጦርነት ላይ እንደመሆኑ መጠን አሸባሪው ለሚነዛው ወሬ መደንገጥ ይቅርና ጆሮ ሰጥቶ ማዳመጥም ተገቢ አይሆንም፡፡ ይልቅ ‹‹ቆቦ ተያዘ›› ከሚል ጨዋታ ወጥተን በአካባቢው ያለውን ፍጡር ሁሉ ያዘመተብንን አሸባሪ እንደ ሕዝብ ልንመክተው ግድ ይለናል፡፡ በውሸት እና በሐሺሽ ሱስ የተለከፈውን አሸባሪ በእውነተኛ እርሳስ ግንባር ግንባሩን በመበርቀስ ሙሉ ለሙሉ መደምሰስ ይገባናል፡፡ ይሄውም አይቀሬ ድል በአጭር ጊዜ ትግል ይሳካ ዘንድ ሽንፈትና ባርነት ካዘለ ሕይወት ይልቅ ለአሸናፊነትና ለነጻነት የሚከፈል መስዋዕትነት የላቀ ነውና ከአገራችን ጎን በጎን መላው የክልላችን ወጣት ሆ ብሎ እንዲዘምት መቀስቀስ ይገባናል፡፡ ከአሸባሪው ጋር በሚደረገው ትግል ላይ በአካል መሳተፍ የማይችለው አካል ደግሞ ያላንዳች ልማት ሲፈስስ ለኖረው ውሃችን የአቅማችንን አዋጥተን ግድብ እንደሠራነው ሁሉ ያላንዳች ምክንያት ደማችንን ሊያፈስና አገራችን ሊያፈርስ ከተነሳው አሸባሪ ጋር ለሚደረገው ትግልም ከአባይ ባልተናነሰ መልኩ ድጋፉን መቸር ይገባዋል፡፡ በተለያዩ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንም ለወገናችሁና ለአገራችሁ ያላችሁን አለኝታነት የምታሳዩበት ከዚህ የከፋ ወቅት ሊኖር እንደማይችል አውቃችሁ በገንዘብ እና በሐሳብ ትግሉን ትደግፉ ዘንድ አደራ እላለሁ፡፡ ኮፒ በማድረግ ፌስቡክ ላይ ያጋሩት!

ጄኔራል ሳሞራ የኑስ ለአሸባሪዎቹ ያስተላለፈው መልዕክት.. አሳዬ ደርቤ "አማራን ልትጠላው ትችላለህ። የምትንቀው ሕዝብ ግን አይደለም። ለምን? እራሱን ቀርቶ አገሩን ማስከበር የሚችል መብረቅ የሆነ ሕ
ጄኔራል ሳሞራ የኑስ ለአሸባሪዎቹ ያስተላለፈው መልዕክት.. አሳዬ ደርቤ "አማራን ልትጠላው ትችላለህ። የምትንቀው ሕዝብ ግን አይደለም። ለምን? እራሱን ቀርቶ አገሩን ማስከበር የሚችል መብረቅ የሆነ ሕዝብ ስለሆነ! እናንተ ግን በውሸት ፕሮፖጋንዳ የእራሳችሁን ጉጅሌ ጥይት የማይመታውና ሞት የማይነካው አድርጋችሁ አማራውን ለመሞት የተፈጠረ ሕዝብ አደረጋችሁት። ውሸት አይሰለቻችሁም? ውርደት አይታክታችሁም? ይሄ ድሃ ሕዝብ አያሳዝናችሁም? አንድ ነገር ልንገራችሁ? መለስ አንገቱን ቀና አድርጎ የምትፈጽሙትን ክህደት የመመልከት እድሉን ቢያገኝ አማራ ጋር ተሰልፎ እናንተ ላይ እንደሚዘምት አልጠራጠርም " ጄኔራል ሳሞራ የኑስ # Share

ወደ ትግራይ የእርዳታ እህል ጭነው የሚበርሩ የWFP አውሮፕላኖች የመቀሌ ዩኒቨርሰቲ ተማሪዎችን ይዘው የሚመለሱበት መንገድ ይመቻች! የእራሱን ሕፃናት የሚያዘምት አሸባሪ የማያደርገው አይኖርም❗️

ለምርጫ ቅስቀሳ በየወረዳው ተበትኖ የነበረ የፌደራልና የክልል ካድሬ ወደተመረጠበት ወረዳ በመሄድ መላውን አማራ መቀስቀስና ማዝመት ያለበት ይመስለኛል። ያለንበት ጊዜ ባለ ኮከብ ሆቴል ውስጥ ተቀምጠን የምንዝናናበት አይደለም❗️❗️

ኢሳይያስ አፈ-ወርቂ፡- አሳዬ ደርቤ ➖➖➖ ➜የጁንታው አሸባሪ ሳይወድ በግዱ እንደ መለስ የሚያከብረው፣ እንደ ጭራቅ የሚፈራው ➜እሱ ላይ የምትፈጸም ትንኮሳ ድምሰሳ እንደምታስከትል ለአሸባሪዎች ማስተማር የተቻለው ➜አስፈሪ ሥሙን ላለማንሳት አረመኔ እና ጨካኝ እያለ የእኛው አረመኔ ሃይል የሚጠራው ➜ለየትኛውም ምድራዊ ሕግና ሃይል ተላልፎ የማይሰጥ ባውንደሪ ያለው ➜ለዓለም አቀፍ ሕግ ተገዥ የማይሆን ሽብርተኛን በእራሱ የጨዋታ ሕግ በማስተናገድ ማርበድበድ የሚቻለው ➜የሚኖርባት ዓለም ቀርቶ የሚያስተዳድራት አገርም በጦርነት ላይ ደካማ ሆኖ የተገኘ መንግሥቷን ‹‹ዞር በል›› ብላ ለብርቱ ጠላቷ እንደምትገብር የሚገባው… ➜በራያና በወልቃይት አቅጣጫ ወረራ የፈጸመው አካል ‹‹ያ ሰውዬ እንዳይወርረኝ›› በሚል ስጋት ወደ ፊት እየተኮሰ ወደ ጀርባው እንዲመለከት ማድረግ የተቻለው… ➜ጦር ሰብቆ የመጣበትን ጠላት ሕጻናት እና ሴት እያለ መከፋፈል የማይቻለው፣ ቀይ መስመሩን አልፎ የመጣን አሸባሪ ምን እንደሚያጨስ በመተንተን ፈንታ አጫሹን ማጨስ የሚያሰኘው ➜ለየትኛውም አይነት ውጫዊ ጫናና ማዕቀብ የማይገዛ መሪ ሆኖ በመገኘት የጁንታውን የፕሮፖጋንዳ ጨዋታና ውንጀላ ገና ድሮ ማክሸፍ የተቻለው… ➜አሸባሪ ባደራጀው መንጋ ተከበብኩ ብሎ እራሱን በሚሰዋና በሚማረክ ወታደር ፈንታ እራሱን የሚያስከብር ጦር ባለቤት ሆኖ በመገኘት… ጁንታው ‹‹ሂድና ውጋው›› የሚል ትዕዛዝ ቢሰጥ እንኳን ‹‹እንቢየው›› ብሎ የሚመልስ መንጋ መፍጠር የተቻለው… ➜በእንዲህ ያለ ወቅት፣ እንዲህ ያለ እድፋም ጠላት ሲያጋጥምህ በረኪና ሆኖ የምታገኘው..

በሠራዊት ቁጥር እንጂ በሕዝብ ቁጥር አሸባሪ ሃይሎችን ማሸነፍ አይቻልም። ከዚህ አንፃር በሕዝብ ቁጥር 110 ሚሊዮን ብንሆንም ያዘመትነው ሠራዊት ግን ከአሸባሪው ጋር የሚነፃፀር አይደለምና ትኩረት ይደረግበት።