Assaye Derbie
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览
频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 333 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 647,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 350 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 333 名订阅者。
根据 25 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -108,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.62%。内容发布后 24 小时内通常能获得 12.61% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 538 次浏览,首日通常累积 1 808 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 33。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 26 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。
14 333
订阅者
-424 小时
-317 天
-10830 天
帖子存档
14 333
ዋዛ እና ቁምነገር
አሳዬ ደርቤ
ከሚኖሩበት ቤት እና ከሚሠሩበት መሥሪያ ቤት ታፍነው የተወሰዱ ጋዜጠኞችና የሕዝብ ድምጾች ለጋዜጣዊ መግለጫ የተጠሩ ይመስል ዘና ባለ መንፈስ ውስጥ ሆነው ከእስር ቤት ቅጽር ግቢ ውስጥ ተቀምጠዋል፡፡ ከመስከረም አበራ ውጭ ያሉት ታፋኞችም መታሰራቸውን ዘንግተውታል፡፡ መስኪ ግን ለሰባት ቀናት ያህል መታሰሯን ሳይሆን የሰባት ወር ልጇን መርሳት ተስኗታል፡፡
ከእነዚህም ታፋኞች መሀከል አንዱ የሆነው ጋዜጠኛ ሰሎሞን ሹምዬ ‹‹ዛሬ ቀኑ ማን ነው›› በማለት ሲጠይቅ ‹‹ባግባቡ አልተከበረም እንጂ ግንቦት ሃያ ነው›› በማለት ያየሰው ሽመልስ መለሰለት፡፡
ይሄንንም መልስ መስኪ ስትሰማ ‹‹‹‹የግንቦት ሃያ ቀንን በደማቁ ለማክበር ጋዜጠኞችን እና የመብት ጥያቄ ያነሱ ዜጎችን አሰልፎ ወደ እስር ቤት ማስገባት እንጂ ሕዝብን አሰልፎ ወደ አደባባይ ማውጣት አይጠይቅም›› በሚል መልስ ከወትሮው በላቀ መልኩ ግንቦት ሃያ መከበሩን ታስረዳው ጀመር፡፡ አቦይን በምሕረት በፈታው መንግሥት የታሰሩት አቶ ታዲዮስ ታንቱም ‹‹እዚህ እስር ቤት የተገኘነው እኮ አጥፍተን ሳይሆን የግንቦት ሃያ በዓልን አክብሩ ተብለን ነው›› በማለት በመስኪ ሐሳብ መስማማታቸውን ገለጹ፡፡
በወሬው መሀከልም ከፊት ለፊታቸው ካለ ግድግዳ ላይ የተሰቀለው ቴሌቪዥን ‹‹ከአፍታ በኋላ ልዩ ልዩ ዜናዎች ስለሚኖሩን ባሉበት ይጠብቁን›› የሚል መልዕክት አስተላለፈ።
ያን ጊዜም በወያኔ ዘመን ወደ እስር ቤት ከገባ በኋላ የታሰረበትን ጥፋት ከተመስገን በየነ አንደበት ሲያዳምጥ የኖረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ‹‹ከመኮነን መንትያ ልጆች አንዱ ወንጀሌን ቢነግረኝ…›› ከሚል ንግግር ጋር ሪሞቱን አንስቶ ቻናል ይቀያይር ጀመር፡፡
‹‹የመኮነን መንትያ ልጆች እነማን ናቸው›› ተብሎ ሲጠየቅም ‹‹መሳይ መኮነን እና ናትናኤል መኮነን ይባላሉ›› የሚል መልስ ሰጥቶ በየቻናሉ ሲፈልጋቸው ከቆየ በኋላ ከአቶ ደመቀ መኮነን ውጭ ማንንም ማግኘት ስላልቻለ ቻናሉን ፋና ላይ አድርጎ ሪሞቱን አስቀመጠው፡፡
በዚህም ቻናል ‹‹በሕግ ማስከበር ዘመቻው በዝርፊያ፣ በሕገ-ወጥ መሳሪያ ዝውውር፣ የሕብረተሰቡን ሰላም በማወክና በኮንትሮባንድ ንግድ… የተጠረጠሩ ከአምሥት ሺህ በላይ ዜጎች በቁጥጥር ስር ዋሉ›› የሚል ዜና ሲከታተል ከቆየ የኮንትሮባንድ ዜናው እሱን የሚወክል ሆኖ ስላላገኘው ቻናሉን አሚኮ ላይ አድርጎ ‹‹ሕገ መንግሥቱን በመናድ የተጠረጠሩ…›› የሚል ዜና ይጠብቅ ያዘ፡፡
በዚህ መሀከልም ወደ ታፋኞቹ የመጣ አንድ የፖሊስ አዛዥ ‹‹በአንዳንድ ነገሮች ላይ ላነጋግራችሁ ስለምፈልግ ሰብሰብ ብላችሁ ተቀመጡ›› የሚል ትዕዛዝ ከሰጣቸው በኋላ ማስታወሻ ደብተሩን ገልጦ ከፊታቸው ተቀመጠ፡፡ ከአስር በላይ ከሚሆኑ ታዋቂ ጋዜጠኞች መሀከል እራሱን ያገኘው የፖሊስ አዛዥም ‹‹መቅረጸ ድምጽና ካሜራ ሳትይዙ የመጣችሁት ለምንድን ነው?›› ብሎ ሊቆጣቸው ካሰበ በኋላ ከፊቱ የተገኙት ታስረው እንጂ ለጋዜጣዊ መግለጫ ተጠርተው አለመሆኑ ትዝ ሲለው ‹‹የእስረኛ አያያዛችን እንዴት ነው?›› በማለት ጠየቀ፡፡
ለዚህም ጥያቄ አቶ ታዲዮስ ታንቱ የሰጡት መልስ እንዲህ የሚል ነበረ፡፡
‹‹እኔ መቼም የታፈንኩበት መንገድ ከኮቪድ ጋር የሚመሳሰል መሆኑ ቢታወቅም ኤካ ሆስፒታል ሳልገባ ማገገም በመቻሌ ፈጣሪን አመሰግነዋለሁ››
14 333
እኔን ጨምሮ በአምስት የአማራ ልጆች ላይ የእስር ማደኛ (ማፈኛ) ወጥቷል፡፡
ያም ሆኖ ግን እንደ ሕዝብ ሊጠብቀኝ የሚገባው መንግሥት እንደ ሕዝብ ሊያፍነኝ ጉዞ መጀመሩን ብረዳም ‹‹አማራ›› ከመሆኔ ውጭ ጥፋት ስለሌለኝ እራሴን ልጠብቅም ሆነ ልደበቅ አልሞክርም፡፡
ይሄን ስልህ ‹‹አማራ መሆን ጥፋት ነው እንዴ?›› ልትለኝ ትችላለህ፡፡
እኔ ግን ‹‹ቅጣትም ጭምር…›› እልኻለሁ፡፡ ካላመንክ አማራ በመሆናቸው ብቻ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው ሲገደሉና ሲፈናቀሉ የከረሙ ወገኖችህን ቁጠራቸው፡፡ "ለሕዝብ በማሰብ ወንጀል" ተጠርጥረው በየእስር ቤቱ የተጠቀጠቁ ወንድሞችህን አስታውሳቸው፡፡
በተረፈ የመታፈኛ ተራዬ እስኪደርስ ድረስ ወደ ልቤ ገብቼ ውስጤን ሳስስ እንዲህ የሚል ክስ የሚመሠርትብኝ ይመስለኛል፡፡
'አማራን በማተራመስ- ኢትዮጵያን ማፍረስ' ሲፈለግ
ብእሩን ከእሳት ውስጥ ማግዶ-
ባርነት የሚረከቡ ፥ ልጆቹን እንደማሳደግ፤
የወገኖቹ ድምጽ ሆኖ- የሚቻለውን በማድረግ፡፡››
ከዚህ ውጭ ግን በሎሬት ጸጋዬ ብዕር ያደረው አጼ ቴዎድሮስ የገብርዬን ሕልፈት ሲሰማ፡-
‹‹ያለፈ ጥረታችንን- ሳስታምመው- ትዝ ሲለኝ
ከሞከርነው ነገር ይልቅ- ያልሞከርነው ነው- እሚቆጨኝ›› በማለት እንደተናገረው.... ወራዶች ዝቅ ላደረጉት ለዚያ ታላቅ ሕዝብ ካደረግኩት ኢምንት ነገር ይልቅ ያላደረግኩት ነው የሚቆጨኝ፡፡
ዝንታለም አማራ!
14 333
መታፈንን ፈርተህ ለታፈንከው ወገኔ‼️
አሳዬ ደርቤ
ከሞት በላይ ባርነትን እና ትርጉም አልባ ሕይወትን ተጠየፍ፡፡
የምታስበውን መተግበር ቢሳንህ እንኳን ለመናገር አትስነፍ፡፡
ጥፋት መፈጸምን እና ግፍ መሥራትን ተጠየፍ እንጂ ፍትሐዊ ላልሆነ ቅጣት አትሸነፍ፡፡
ከፊታችን እኔና አንተን የሚፈትን ከባድ ቀን እየመጣ ነው፡፡ እናም ይህ ቀን መከራ አሸክሞህ እንዲሄድ ከፈለግክ ‹‹እንዴት ልችልው ነው›› እያልክ አካብደህ ተቀበለው፡፡ ጠንካራ አድርጎህ ያልፍ ዘንድ ከፈቀድክ ግን ‹‹አልፈዋለሁ›› በሚል መንፈስ ብርቱ ሆነህ ጠብቀው፡፡
‹‹ፈሪ ልብ›› ጠላቱን ቀርቶ ጥላውን ያሳድዳል፡፡ ለስጋት የዳረገውን ሁሉ በማሰርና በመቅበር ከፍርሐት ስሜቱ ለመንጻት ይጋጋጣል፡፡
ጀግና ግን ከትርጉም የለሽ ሕይወት ይልቅ ምክንያታዊ ሞትን ይመርጣል፡፡ እንደ ቴዎድሮስ ‹‹እጄን አልሰጥም›› ብሎ እርሳስ ይጎርሳል፡፡ እንደ እሸቴ ሞገስ ‹‹ልጄን ጥየ አልሄድም›› ብሎ መላዕከ ሞትን ግብግብ ይገጥማል፡፡
ኪሳራን የሚፈራ ነጋዴ ትርፋማ መሆን ይሳነዋል፡፡ እስራትንና እንግልትን የሚጠላ ዜጋ ነጻነቱን ሰውቶ ለባርነት ይንበረከካል፡፡ ጠላት በተነሳበት ወቅት ትግልን የሚፈራ ሕዝብ በቀላሉ ድል ሆኖ ከጦር ሜዳ የከፋ መራር ፍዳ ያስተናግዳል፡፡
በተረፈ…
‹‹በጋራ የሚፈትነን የአፈና ቀን መምጣቱን ስነግርህ ‹‹እራስህን ጠብቅ›› አትበለኝ፡፡ አንተ ጠብቀኝ እንጂ እኔማ ያንተ እረኛ ነኝ፡፡
ምክንያቱም…
እንደ ግለሰብ በተናጠል እራሱን ወይም ደግሞ ቤተሰቡን የሚጠብቅ ፍጡር ድምጹን አጥፍቶ ጎረቤቱ ሲጠቃ እያዬ እንደ ሕዝብ ይወድማል፡፡ እርስ በእርስ የሚጠባበቅ ሕዝብ ግን በጋራ የመጣበትን አደጋ መክቶ በተናጠልም ሆነ በጋርዮሽ ከመጠቃት ይድናል፡፡
ከዚህ ውጭ ግን ጸሐፊው ሁሉ ባደፈጠበትና በሚሳደድበት ጊዜ እዚህ እየመጣሁ የምቸከችክህ ልጆቼን አቅፌ በማደር ፈንታ ወህኒ ቤት ገብቼ ትኋን ማባረር አምሮኝ እንዳይመስልህ፡፡
ያላንዳች ጥፋት እንደ ሕዝብ የተላለፈብንን ቅጣት እንደ ግለሰብ በመፍራት ማለፍ እንደማይቻል ገብቶኝ እንጂ….‼️
ወላጅን ቀርቶ ሕጻናትን ሳይቀር የሚያፍን መዳፍ እንዳያፍነኝ ፈርቼ እራሴን ማፈን ስለማልፈልግ እንጂ…‼️
እናም እልኻለሁ…
አለመታፈን የምትፈልግ ከሆነ እራስህን በመለጎም ፈንታ ‹‹አፈናው ይቁም›› ብለህ ተቃወም!
14 333
ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
➔የተቀበለውን ሥልጣን ባግባቡ በማስረከብ አብንን በዲሞክራሲያዊ የሥልጣን ሽግግር ማዕቀፍ ውስጥ ያስቀመጠ፤
➔ከግላዊ ፍላጎት ይልቅ ለድርጅታዊና ሕዝባዊ ፍላጎት ቅድሚያ የሠጠ፤
➔መነሻውን እና ትናንትናውን እረስቶ በትልቅነትና በእቡይነት ስሜት ልቡ ያላበጠ፤
➔ሥልጣን ላይ ሳለ ባጋጠሙት ትችቶች ይቅርታ ከመጠየቅ ባለፈ "መንጋዎች" በሚል የአምባገነኖች ፍረጃ ወገኑን ያላንጓጠጠ፤
➔"የትናንት ጥቅም እና ሥም ቀነሰ" በሚል ኩርፊያ የጎጥ እሳቤ ውስጥ ያልተሸጎጠ፤
➔ትሕትናን እና በጎነትን የተሠጠ፤
.
.
.
እንዳንተ አይነት ቅን እና ሐቀኛ ታጋዮች በብዛት ያስፈልጉናል ወንድማለም‼️
14 333
አቤቱታ‼️
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
ዳኛ ባገር ጠፋ- ሕግጋት ተሻረ- ፍትሕ ተረገጠች
በሐምሌ ደመና- በነሐሴ ጭጋግ- መስከረም ታፈነች፡፡
ምክንያት ታመመ- እውነት ኮሰመነ- ይሉኝታ ቆሰለ
ወንጀለኛ ያልነው- ፍርጅ ሰጪ ሆኖ- ወንበር ላይ ቁጭ አለ
ከዘራፊው በረት- ከእነ እንቶኔ ፍራሽ- 'ተፈራ' ተጣለ፡፡
ውሸት በለጸገ- ቅጥፈት ባሕል ሆነ- ክሕደት ተለመደ
በፈርጣጭ አፈሙዝ- አርበኛ ታወከ- ፋኖ ተሳደደ፡፡
በሕዝብ መዋጮ- አገር እንዲጠብቅ- የተገዛ ድሮን
ጠላት ችላ ብሎ- ማስጨነቅ ጀመረ- የገዛ ወገኑን፡፡
በእስተርጅና ወራት- የልጅነት ዘመን- ዳግም ተመለሰ
አባይ ሳይደፈርስ- እቃቃ ቤት ሆኖ- አገር ፈራረሰ
ሰው ባገሩ ጠፍቶ- አንድ ሕጻን ታሰረ- አንድ ሕጻን ነገሰ፡፡
Share
14 333
በአብን ገጽ ላይ የወጣው የበለጠ ሞላ መግለጫ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
➔በአማራ ፋኖ ላይ እየተወሰደ ያለውን የማሳደድ ዘመቻ ሊቃወም ቀርቶ የፋኖን ሥም ሳይጠራ በቸልታ ያለፈ፤
➔ከአብን አባላት ውጭ ባለው የአማራ ኤሊትና ወጣት ላይ እየተወሰደ ያለውን አፈሳ የደገፈ፤
➔አፈናውን የሚቃወሙ አክቲቪስቶችን፣ ጋዜጠኞችንና ሚዲያዎችን "የወያኔ ተከፋዮች" በማለት የነቀፈ፤
➔"ተጠርጣሪዎች የሚያዙበት መንገድ ጥንቃቄ የተሞላበት አለመሆኑ መንግሥታችንን እያስተቸ ነው" የሚል መልዕክት ያስተላለፈ፤
➔የአባላቱን እና የሕዝብን ግብረ መልስ ላለመቀበል የሐሳብ መስጫ ሳጥኑን የቆለፈ፤
➔ከአብን በተጨማሪ ሕዝብን ወርውሮ ብልጽግናን ለመቀላቀል በወሰነ አመራር በብስጭት መንፈስ የተጻፈ..... እጅግ አሳፋሪ መግለጫ ሆኖ አግኝቸዋለሁ።
እናመሠግናለን ክቡር ሚኒስቴር‼️
14 333
በአማራ ታጋዮች የተሞሉት እስር ቤቶች
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
አፋኙ አካል ‹‹አምሥት ሺህ ሰዎችን ተቆጣጥሬያለሁ›› እያለ በበናውን ይነፋል፡፡
ታሳሪዎቹ ግን ከሰፊው ወህኒ ቤት በተሻለ መልኩ የነጻነት ቀንድል መጎናጸፋቸውን እንጂ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን አይቀበሉም፡፡ በሤራ ከተበተበውና ከእረፍት አልባው የኢትዮጵያ ፖለቲካ የመገላገል ስሜት ካልሆነ በቀር የጥፋተኝነትና የጸጸት መንፈስ አይዳብሳቸውም፡፡
ወንጀለኞች አለመሆናቸውን ታሳሪዎቹ ቀርቶ አሳሪዎቹም ሆነ ከሳሾቹ አሳምረው ስለሚያውቁ... ሥጋታቸውም ‹‹እኛን ማገት ያስፈለገው የአማራን ቅስም በማነኳኮት ከትሕ-ኦነግ ጋር አብሮ ለመሥራት ወይስ ወልቃይትን ለመስጠት?›› የሚል እንጂ ‹‹ከተከሰስንበት ወንጀል ነጻ መውጣት ካልቻልን በስንት ዓመት እንቀጣ ይሆን›› የሚል አይደለም፡፡ አፍሶ ያስገባቸው አካል በሕዝባዊ ቁጣ ተገድዶ ባይለቃቸው እንኳን በአማራ ላይ ያቀደውን እኩይ ሤራ በስኬት ወይም ደግሞ በውድቀት ባጠናቀቀ ማግስት በነጻ እንደሚያሰናብታቸው ስለሚያውቁ የፍትሕ ሒደቱም አያሳስባቸውም፡፡
➔ለወገናቸው ነጻነትና እኩልነት ሲታገሉ ተይዘው...
➔ይከስም ዘንድ የተፈረደበትን ሕዝብ ሲታደጉ ተገኝተው...
➔የመንግሥትን አገር አፍራሽ ድርጊት ሲያጋልጡ እጅ ከፍንጅ በቁጥጥር ስር ውለው...
➔በሕዝባችን ላይ የተፈጸመው ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመት መደገም የለበትም›› በሚል አቋም ጠብመንጃ ወይንም ደግሞ ብዕር ይዘው ሲንቀሳቀሱ ከአፋኙ ቡድን እይታ ውስጥ ወድቀው…. ወደ ማጎሪያ ካምፕ የተወረወሩ በመሆናቸው ከምቹ መኝታ ቤታቸው ውስጥ አጥተው የከረሙትን እንቅልፍ ከብጣቂ ፍራሽ ላይ ተጎናጽፈው በሰላም ያሸልባሉ፡፡
‹‹በምን አይነት ስልት እንፈናቸው›› እያሉ ሲጨነቁ የከረሙት ኃይሎች ግን ‹‹በምን አይነት ጥፋት እንክሰሳቸው? በወሰድነው እርምጃ ሕዝቡ ምን እያሰበ ነው? ይሄንን ታሪካዊ ክህደት ያስፈጸመን አካል ፊቱን ያዞረብን ቀን ከሕዝብ ጋር ተቀላቅለን መኖር የምንችለው እንዴት ነው?›› እያሉ ሲጨነቁና ከበረከት ስምዖን ክፍል ውስጥ በሐሳብ ገብተው ሲማቅቁ ያድራሉ፡፡
ከሚለሰልስ ብርድ ልብስና ትራስ ውስጥ ሆነው እየኮሰኮሰ ያስቸገራቸውን ኅሊና በመጠጥ ኃይል ድባቅ ለመምታት ውስኪና ቮድካ ሲያንቃርሩ ያነጋሉ፡፡
14 333
በዓለም ድንቃ ድንቅ መዝገብ ሊሰፍር የሚገባው ትንግርት
▬▬▬▬▬▬
ከቀናት በፊት ጋዜጠኛ ሰሎሞን ሹምዬን ሊያፍኑ ወደ ቤቱ ያመሩ ኃይሎች እሱን ማግኘት በተሳናቸው ጊዜ እኅቱን አፍነው ወሰዱ፡፡ ይሄንንም አሳፋሪ ድርጊት የሰማው ጋዜጠኛ ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሄዶ ‹‹ሰሎሞን እስኪመጣ ፥ ሰላማዊት ትቀጣ የሚል ሕግ መኖሩን አላውቅም ነበር›› በሚል ስላቅ እኅቱን አስፈትቶ ታፋኙን ማሕበረሰብ ተቀላቀለ፡፡
ይሄንንም ምርጥ ተሞክሮ ወደ ክልሉ የወሰደው ብአዴን መቶ አለቃ አበበን ለመቆጣጠር ወደ ቤቱ ሲያመራ በተፈላጊው ግለሰብ ፈንታ ጡጦ የሚጠባ ሕጻን ልጅ አገኘ፡፡
እናም ‹‹ይሄን ሕጻን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ብንወስደው ተፈላጊው ሰውዬ ልጁን ፈልጎ መምጣቱ አይቀርም›› በሚል ውዳቂ አስተሳሰብ አፉን ያልፈታውን ብላቴና አፍኖ በመውሰድ በዓለም ድንቃ ድንቅ መዝገብ ላይ ያልሰፈረ አዲስ ገድል ፈጸመ፡፡
ይሄውም አስነዋሪ ድርጊቱ ይፋ የወጣበት ነውረኛ ቡድን አመሻሽ ላይ በቴሌቪዥን ቀርቦ ‹‹የክልሉ መንግሥት የፋኖ ልጆችን አግቶ የሚወስደው ከረሜላና ብስኩት ለመግዛት እንጂ ወደ አስር ቤት ለማስገባት አይደለም›› ከሚል ማስተባባያ ጋር ሕጻኑን በአንቀልባ አዝሎ ወደ ቤቱ ሲያደርስ እንመለከት ይሆናል፡፡
14 333
በአባቱ ፈንታ የታገተው የየጁቤው ፋኖ የመቶ አለቃ አበበ ሕፃን ልጅ...‼️
@አስረስ ማረ ዳምጤ
ከመበስበስም አልፎ በቅማል የተወረረ ሥርዓት‼️ቱፍ!
14 333
ዛሬ ከአማራ ፋኖዎች እና ተሟጋቾች ባለፈ የአብን አመራሮች እየታፈኑ ወደ እስር ቤት ሲጋዙ አንተ ምቹ ወንበር ላይ ተቀምጠህ በዝምታ ብቻ ሳይሆን በፈገግታ እየታዘብክ ነበር።
ነገ ደግሞ እነሱ በነፃነት ስሜት እየሳቁ ሲወጡ በጸጸት እየታመስክ አቀርቅረህ ስትጓዝ መንገድ ላይ ትገናኙ ይሆናል።
በተረፈ በጥቅም ተሸንግለው ከተለጎሙ ልሂቃን ይልቅ የሕዝብን ሕመም በመጋራታቸው የተነሳ በአምባገነን መዳፍ ታፍነው ከእስር ቤት የሚጣሉ ደቂቃን የነፃ መንፈስ ባለቤቶች መሆናቸውን ማስታወስ እወዳለሁ‼️
14 333
ብአዴን ባንድ ሳምንት ውስጥ ባካሄደው ዘመቻ የአማራ ልዩ ኃይልን አዛዥ ጨምሮ 5 ሺህ ፋኖ ማፈኑን የሚገልጽ ዜና በቲቪ ሲተላለፍ የሰማው አቶ ጌታቸው ረዳ ምን ብሎ ቢዘፍን ጥሩ ነው?
"ያለብኽን ሒሳብ ፥
አወራርድ ተብሎ ፥ በአፈሙዝ ሲጠየቅ፤
በክትክታ ዱላ ፥
ማርኮ ያባረረን፥የታጠቅነውን ትጥቅ፤
ያ ተስፋፊ ኤሊት ፥ ያ የአማራ ፋኖ
ዛሬ ከፈለ አሉ ፥
በእኅት ድርጅቴ ፥ በአዴፓ ታፍኖ"
14 333
መስኪ "የአማራ ክልል መንግሥትን እና የፌደራል መንግሥቱን ለመነጣጠል በመሞከር ወንጀል" ተጠርጥራ መታፈኗን ሰማን 😆
እድሜ ይስጠን እንጂ ከወራት በኋላ ደግሞ አንዳንድ አክቲቪስቶች "በመንግሥት እና በህውሓት መሀከል የነበረውን ጊዜያዊ ግጭት በማቀጣጠል ወንጀል ተጠርጥረው ሲታሠሩ እንመለከት ይሆናል።
መስኪ ግን ይሄን ክስ ስትሰማ እንዲህ ብላ የምትጠይቅ ይመስለኛል።
"በአማራ ክልል መንግሥት እና በፌደራሉ መሀከል ያለው ግንኙነት በአማልክት ተዓምር ካልሆነ በቀር በአክቲቪስት ንግግር እንዴት ሊፈራርስ ይችላል?"
14 333
አንዳንዶች የሕዝብን ሕመም ተጋርተው ይታፈናሉ። አንዳንዶች ደግሞ የመንግሥትን ጥቅም ተቃምሰው...‼️
ያጋቱት አንቺን ብቻ አይደለም! የሰባት ወር ልጅሽንም ጭምር እንጂ‼️
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
