ch
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 Assaye Derbie 的分析概览

频道 Assaye Derbie (@asayede) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 335 名订阅者,在 博客 类别中位列第 2 651,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 347

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 335 名订阅者。

根据 26 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -104,过去 24 小时变化为 -8,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 35.99%。内容发布后 24 小时内通常能获得 12.61% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 158 次浏览,首日通常累积 1 808 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 30

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 27 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 博客 类别中的关键影响点。

14 335
订阅者
-824 小时
-327
-10430
帖子存档
እንደ ግሩም ጫላ እና ቴዎድሮስ አድሃኖም ካሉ በዓለም አቀፍ ሥም ከሚንቀሳቀሱ ዘረኞች ጋር ሲነፃፀሩ ወለጋና መተከል ጫካ ውስጥ ያሉት ታጣቂዎች ምስጉን ናቸው።
እንደ ግሩም ጫላ እና ቴዎድሮስ አድሃኖም ካሉ በዓለም አቀፍ ሥም ከሚንቀሳቀሱ ዘረኞች ጋር ሲነፃፀሩ ወለጋና መተከል ጫካ ውስጥ ያሉት ታጣቂዎች ምስጉን ናቸው።

የመንግሥት መግለጫ‼️ አሳዬ ደርቤ የኑሮ ውድነት- ከአቅሜ በላይ ሆነ- እያልክ አትንጫጫ በርበሬ ያጣህ ቀን- ቀይወጡን ተውና- ተመገብ አልጫ፡፡ በሆነ ባልሆነው- መሪህን አትውቀስ- መንግሥትን አታማር
የመንግሥት መግለጫ‼️ አሳዬ ደርቤ የኑሮ ውድነት- ከአቅሜ በላይ ሆነ- እያልክ አትንጫጫ በርበሬ ያጣህ ቀን- ቀይወጡን ተውና- ተመገብ አልጫ፡፡ በሆነ ባልሆነው- መሪህን አትውቀስ- መንግሥትን አታማር ዘይት ሲቸግርህ- ቦለቄ ቀቅለህ- ንፍሮ በልተህ እደር፡፡ ጤፍ ከሰው ተወድዶ- የነጠፈ ለታ- እንጀራ ከሞሰብ ሙዝና ፓፓያ- አቦካዶ ጨምቀህ- በዳቦ ተመገብ መንግሥት ዝናብ እንጂ- ከደመና መሃል- መቼም መና አያዘንብ፡፡ የስንዴ ምርጥ ዘር- የአፈር ማዳበሪያ-‹‹አጣን›› የምትሉ በዘንድሮው ክረምት- እህሉን ተውና- ባሕር ዛፍ ትከሉ፡፡ በቤንዚን አቅርቦት- ታክሲ የጠፋ ቀን- እንደ እንጀራ ወጡ ስለ ኦጋዴን ነዳጅ- ባወራሁት ወሬ- ከምታላግጡ የኢትዮጵያ ትንሳኤ- እስቲመጣ ድረስ- ወክ ልትበሉ ውጡ፡፡ በተረፈ… በራብ እና ጥይት- እንደ ክረምት አግቢ- ሕዝባችን ቢረግፍም ማዳበሪያ ጠፍቶ- የአርሶ አደሩ ማሣ- እንዲሁ ቢከርምም ዜጎች ጠባቂ አጥተው- በአሸባሪ ጥቃት- ተጨፍጭፈው ቢያልቁም፤ ኢትዮጰያችን እንደሁ- ብልጽግናን ይዛ- መሻገሯ አይቀርም፡፡

አማራ ባልሆን ኖሮ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ➔ለእኩልነት ጥያቄው ‹‹የአማራ የበላይነት አይመለስም›› የሚል መልስ ሰላሳ ዓመት ሙሉ ሲያስተናግድ ከኖረው… ➔በክልሉ ውስጥ ለሚገኙ ብሔረሰቦች ሐቀኛ ፌደራሊዝምን የተገበረው እሱ ሆኖ ሳለ የአማራን ንጹሐን ማጥቃት የፌደራሊስት መገለጫ ባደረጉ ሃይሎች በአሀዳዊነት ከሚፈረጀው… ➔‹‹ኢትዮጵያን የሚወድድ መሪ ሁሉ መሪዬ ነው›› በሚል መርሕ አዲስ ንጉሥ አራት ኪሎ አስገብቶ ሲመለስ ‹‹የአጼዎቹን ሥርዓት አይመለስም›› የሚል ከንቱ ንግግር ከሚያስተናግደው… ➔‹‹በልፋቴ ያገኘሁትን ንብረት አታውድሙብኝ›› ለሚል ቅሬታው በልፋቱና በጥናቱ ያገኘው ውጤት ተቀንሶ "ወደ ዩኒቨርስቲ አትገባም›› ከሚባለው… ➔‹‹በመቶዎች የሚቆጠሩ አማራዎች በአንድ ጀምበር ሲገደሉ መንግሥት የት ሄዶ ነበር?›› ብሎ ሲጠይቅ ሥልጣን ከያዙ ነፈዞች አንደበት ‹‹ይሄ ጩኸትህ ነው የሚያስገድልህ›› የሚል መልስ ከሚሰጠው… ➔በእድር ፈንታ በዶዘር ሲቀበር ከርሞ ሌሎች ሃይሎች በፈጸሙት ጥቃት ‹‹ሰው ከእነ ነፍሱ አቃጠልክ›› ተብሎ ከሚወነጀለው… ➔ለአገር ቀጣይነት ሲል በቋንቋ መስፈርት የሚያገለግልና የሚበድል ውዳቂ መንግሥት ተሸክሞ ሲያንዘፋዝፍ ከኖረው…. ➔‹‹አንዲት ሀገር›› የሚል ንግግሩ ‹‹አንዲት ሃይማኖትና አንዲት ማንነት ማለትህ ነው›› ተብሎ ከሚፈረጀው… ➔‹‹ሰለባ ያደረገኝ ሕገ-መንግሥት ይሻሻልልኝ›› ብሎ ሲጠይቅ ‹‹ሁሌ ሟችና ተፈናቃይ በመሆን ፈንታ ገዳይና አፈናቃይ ሆነህ ችግሩን አገራዊ ካላደረግከው በስተቀር ለአንድ ሕዝብ ብለን ሕገ-መንግሥት አናሻሽልም›› የሚል መልስ ከሚሰጠው… የአማራ ሕዝብ አብራክ ባልወጣ ኖሮ... ለዚህ ሕዝብ ጥያቄዎች የትኛውንም መስዋዕትነት የምከፍል የሌላ ብሔር ተወላጅ እሆን ነበር፡፡ ከአማርኛ በተጨማሪ አፍ በፈታሁበት ቋንቋ ‹‹በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈጸመው ግፍ ይብቃ›› ማለቴ አይቀርም ነበር፡፡ ልክ እንደዚሁ ሁሉ የኢትዮጵያ ፖለቲካ በአማራ ፈንታ የሆነን ብሔር በጥንት ትርክት ለመከራ እየዳረገ በደም የተቦካ እንጀራ የሚያሞሶካ ቢሆን ኖሮ… የዚያ ሕዝብ ድምጽ ከመሆን ባለፈ ልክ እንደ ጎንደር ‹‹እዚያ ማዶ የሚፈስሰው ደም የኔም ደም ነው›› የሚል አመጽ እለኩስ ነበር፡፡ ገባህ?? ግን ከአንዳንዱ ሲሳይ፣ ያንዳንዱ ስቃይ ትርጉም ስላለው እንኳንም ከዚህ ሕዝብ አብራክ ወጣሁ‼️

ለአማራዎች የቀረበ ወቀሳ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ➔እስከ መቼ ድረስ ይሆን ብአዴን፣ አዴፓ፣ የአማራ ብልጽግና እያለ ሥሙን በሚቀያይር ድርጅት ተጽዕኖ ስር ወድቀን የምንኖረው? ➔ሕዝባችን ከወራሪ እጅ ገብቶ "የመንግሥት ያለህ" ሲል የፓርቲውን ገንዘብ ዘርፎ የሚከፋፈል፣ ጀግና አመራሮች ሲፈጠሩ እርስ በእርስ የሚያገዳድል፣ የሕዝቡን የመኖር መብት ነጥቆ ሥልጣኑን የሚያደላድል... ሆዳም ድርጅት ተሸክመን የምንኖረው እስከ መቼ ድረስ ነው? ➔ላለፉት ሠላሳ ዓመታት ሕዝባችን ላይ የደረሰው ጥቃት ሁሉ በብአዴን ይሁንታ እንደተፈጸመ ሁላ የዚህ ድርጅት የሰላሳ ዓመታት የምቾት ጉዞም በአማራ ሕዝብ ፍቃድ ላይ የተመሠረተ ነው። ብአዴንም፣ ሕዝቡን ትቶ የበላይ አካልን ላለማስቀየም የሚተጋው የአማራውን ስነ ልቦና ጠንቅቆ ስለሚረዳና "በሕዝባዊ ትግል ሥልጣኔን አጣለሁ" የሚል ሥጋት ስለማይሰማው ነው። ሕይወታቸውን ለመስጠት የተዘጋጁ ፋኖዎችን ሲበላ መክረሙ አንሶ ዛሬ ደግሞ የአማራ ተማሪዎች ማሕበር መሪዎችን ለማሰር የደፈረውም የበላይ አካላት ቁጣ እንጂ የአማራ ኤሊት ጫጫታ ምንም እንደማያመጣበት ስለሚያውቅ ነው። እኔ እምለው ግን ወገን... በጠላት ጥይት ሕዝባችንን በጅምላ የሚያስጨፈጭፈው ይህ መናኛ ድርጅት ለአማራ እኩልነትና ነፃነት የሚታገሉ ግለሰቦች ብቅ ብቅ ሲሉ እንቅ እያደረገ ሲያከስማቸው ታዛቢ የምንሆነው እስከ መቼ ድረስ ነው? ➔ለሕዝብ የሚታገሉ ግለሰቦችን ከጥቃት በመጠበቅ ፈንታ ሲጠቁ እያየን ጸጥ የምንል ከሆነ ከመሀከላችን ሆዳም እንጂ ልባም ዜጋ እንዴት ሊፈጠር ይችላል? ➔የሕዝብን ጥያቄ የሚያቀነቅን ወንድምህ ሲታሰር ሕዝባዊ ትግል ለኩሰህ ካላስፈታኸው አርፎ የሚቀመጥ ካልሆነ በቀር ከወገኑ ፊት ሆኖ ጥቃትን የሚጋፈጥ ጀግና እንዴት ይኖረናል? ➔የአማራ ታጋይ የምንለው ሰው ሲገደል ከሞት ባናስነሳው እንኳን ገዳዩን አንቀን ለፍርድ ካላቀረብነው የፖለቲካ ነጋዴዎች እንጂ የሕዝብ ጠበቃዎች እንዴት ይፈጠራሉ? መልሱልኝ እስቲ... ለማንኛውም ግን እንደ ሕዝብ የመጣብንን አደጋ ማለፍ የምንችለው ጀግኖቻችንን በየተራ በማስበላት ሳይሆን ጀግና ሆነን ባንድ ላይ በመነሳት ነው። የጅምላ እልቂትን እና ጥቃትን ማስቀረት የምንችለውም በትግል ውስጥ የሚመጣን የትኛውንም መስዋዕትነት ባለመፍራት ነው" እያልኩ "ሰላማዊ ሰልፍ ጠራችሁ" ተብለው ዛሬ የታሠሩ ወንድሞቻችን ባፋጣኝ ይፈቱ ዘንድ እጠይቃለሁ።

አምላክ ሆይ ያንተን ውሃ ለገዳዲ ላይ ገድቦ "የእኔን በረከት ነው የምትጠጡት" እያለ በሳምንት አንዴ የሚጋብዘን መንግሥት ዛሬ ደግሞ "እንደ አሜሪካ ማዕቀብ ዝናብ ጣልኩኝ" ማለት ቢጀምርም ስቀህ እለፈው።😁

ዘርፈህ የማትጠግብ ፥ ሙሰኛ ብትሆንም የተማሪ ውጤት ፥ ማርክ አይሰረቅም። ባሕር ዳር በየትኛውም ተግባር የማይታመነውን መንግሥት ማውገዝ ጀምራለች።
+3
ዘርፈህ የማትጠግብ ፥ ሙሰኛ ብትሆንም የተማሪ ውጤት ፥ ማርክ አይሰረቅም። ባሕር ዳር በየትኛውም ተግባር የማይታመነውን መንግሥት ማውገዝ ጀምራለች።

"ለኦፊኮ ፕሬዝዳንትነት የተጠቆመው አቶ ጃዋር መሓመድ 'አመራር መሆን አልፈልግም ብሎ እድሉን ለፕ/ር መረራ ሰጠ" የሚል ዜና የሰሙ የእኛ ፓርቲ አመራሮች ምን ቢሉ ጥሩ ነው? "ትግሉን ሊተወው ነው ወይ?"😁

ለአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ➔የአማራን ሞት በልምምጥ ማስቀረት የሚቻል ቢሆን ኖሮ ባንድ ወቅት የክልሉ ፕሬዝዳንት የነበሩት አቶ ተመስገን ጥሩነህ በንጹሐን ላይ ደባ ሲፈጽሙ የከረሙ አመራሮችን ወደ ክልላቸው ጠርተው ካባ የደረቡ ቀን እልባት አግኝቶ ነበር፡፡ ➔የአማራን ጥቃት በጥንቃቄ በተሞሉ ለስላሳ ቃላት መግታት የሚቻል ቢሆን ኖሮ በወለጋ ጥቃት ዙሪያ ለተነሳ ጥያቄ ‹‹በዚህ ጉዳይ ላይ የምንተነፍሰው ቃላት ከሌሎች ጆሮ የደረሰ እንደሁ ወገኖቻችንን ለጥቃት ስለሚዳርግ መጠንቀቅ ይኖርብናል›› የሚል መልስ በሰማንበት በአቶ አገኘሁ ተሻገር የሥልጣን ዘመን… በጅምላ የሚቀበር አማራ አይኖርም ነበር፡፡ ➔የአማራን ሕዝብ ስቃይ የበላይ አካል አገልጋይ በመሆን ማስቆም የሚቻል ቢሆን ኖሮ ከብአዴን ባለሥልጣናት እስከ አክቲቪስት፣ ባገሩ ከሚኖረው አማራ እስከ ዲያስፖራ ያለው ሕዝብ ከመንግሥት ጎን ተሰልፎ በቆየባቸው ዓመታት ድምጽ የለሽ የዘር ማጽዳት አይፈጸምብንም ነበር፡፡ ➔የሕዝብን የሕልውና ጥያቄ አማራዎች በጅምላ ሲያልቁ ‹‹ማን ጨፈጨፋቸው›› በማለት ፈንታ ‹‹ለምን ተጨፈጨፉ›› ብሎ በመጠየቅ፣ ሌሎች ባፈሰሱት ደም የሂስና ግለ ሒስ መድረክ አዘጋጅቶ እራስን በመገምገም እንዲሁም ለበላይ አካል በማገልገልና ጅራት በማብቀል መልስ መስጠት ቢቻል ኖሮ…. ከሁሉም ብሔር ብሔረሰቦች በላቀ መልኩ ተክብሮ የሚኖረው ብአዴን በሚባለውና ባርነት በማይሰለቸው ድርጅት የተወከለው ሕዝብ ይሆን ነበር፡፡ እናም እልዎታለሁ ክቡር ፕሬዝዳንት፡- በሕግ ያልተከበረ …. በሕይወት የመኖር መብት በሃይል ይገኛል እንጂ- 'እንቢኝ አትንኩኝ' በማለት መንግሥትን በመለማመጥ- ገዳይ ጋር አብሮ በመሥራት ልፍስፍስ ባሪያ በመሆን- አጎብዳጅ እንደ ብአዴን አማራ መብቱን ሰውቶ- ማትረፍ አይሻም ሕይወቱን፡፡ ‹‹የመግደል ፍቃድ ባለው ሃይል- የሕጻናት ደም እንዳይፈስ ሕዝቤ ሆይ በአራጅህ ጥፋት- እራስክን ወንጅለህ ክሰስ አንገትህ እንዳይቀላ- ገዳይ ጋር ተግባብተህ ሥራ" የሚል መናኛ ተግሳጽ- መስማት አይሻም አማራ፡፡ ምክንያቱም… የዜጎች የእድሜ ቆይታ- ጸባይ፣ ባሕሪን በማረም በመንግሥት የተቆጡ ቀን- እንደ ጽድ የሚከረከም ለጌቶች የሰገዱ እለት- እንደ አንቱ ሥልጣን የሚረዝም የአማራ የመኖር መብት- የካድሬ ሹመት አይደለም፡፡

አቶ ዮሐንስ ቧያለው የያዘውን አቋም የአማራ ብልጽግና ቢጋራው የደፈረሰውን ለማጥራት ይጠቅማል። የመንግሥት በደል እንደሁ የአማራ ልጆች ለፍተው ያገኙትን የፈተና ውጤት እስከመንጠቅ ደርሷል። በተረፈ አ
አቶ ዮሐንስ ቧያለው የያዘውን አቋም የአማራ ብልጽግና ቢጋራው የደፈረሰውን ለማጥራት ይጠቅማል። የመንግሥት በደል እንደሁ የአማራ ልጆች ለፍተው ያገኙትን የፈተና ውጤት እስከመንጠቅ ደርሷል። በተረፈ አቶ ዮሐንስ የተገፋው በዚህ እውነት ወዳድነቱና በሕዝባዊ ስሜቱ እንጂ በኪራይ ሰብሳቢነት ወይም ደግሞ በብቃት ማነስ አይደለም። እናመሰግናለን ዋና ሳጂን‼️

ኢሳቶች እና ኢትዮ 360ዎች አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ኢሳቶች ▬▬▬ ➔የአገርና የሕዝብ ፍቅርን በግለሰብ ፍቅር የለወጡ ➔የጠቅላይ ሚኒስትሩን አቋም አቋማቸው ያደረጉ ➔የወቅቱን ፖለቲካ የማይረዳ የደነዘዘ ዜጋ ለማፍራት የሚተጉ ➔አቦይ ሲታሰር ‹‹እልል በል›› ያሉት ሕዝብ አቦይ መፈታታቸውን ሰምቶ እሪሪ ሲል ‹‹የተፈታበት ምክንያት ሳይገባህ አትጩህ›› በማለት የሚቆጡ… ➔መንግሥት ወደ ጦር ግንባር ሲያመራ ‹‹ህውሓት መቀበር የሚገባው ድርጅት ነው›› እያሉ የሚዘምቱ፣ መንግሥት ከህውሓት ጋር ድርድር ሲጀምር ደግሞ ‹‹እርቅን የሚጠላ አጋንንት ብቻ ነው›› በሚል አቋም ምንጣፍ የሚጎትቱ… ➔ብልጽግና ኢትዮጵያን ፍርስርስ ቢያደርጋት እንኳን ‹‹ከዚህ መንግሥት ውጭ ኢትዮጵያን ወደነበረችበት መመለስ የሚችል ሃይል የለም›› ከማለት የማይመለሱ… ➔ለንደንና አሜሪካ ሆነው በሚሰጡት ትንታኔ አዲስ አበባ ላይ ሆነህ በዐይንህ የምታየውንና የምትኖረውን እውነት ውሸት መሆኑን ለማስረዳት የሚባክኑ… ➔በአማራዎችና በአገር ወዳድ ዜጎች የገንዘብ ድጋፍ አማራን በመታገልና መንግሥትን በማገልገል ላይ የሚገኙ ➔በብልጽግና አቀነባባሪነት የሮዋንዳ እልቂት ቢደገም እንኳን እልቂቱ ከእነሱ ትችት ባለፈ ተጠያቂነት እንዲያመጣ የማይሹ ➔በፍቅሩና በብሩ የገዛቸው መንግሥት ከህውሓት ጋር እርቅ ካወረደ የእለት አጀንዳቸውን ከአሸባሪዎች ወደ አማራዎች አዙረው የእለት እንጀራቸውን መጋገር ግድ የሚላቸው… ➔የሰሞኑን የኢዜማ ቆፍጣና መግለጫዎች ‹‹መንግሥታችን ተነካ›› የሚል ብስጭት ፈጥሮ ከናሽናል ወደ ኢንተርናሽናል ከፍ ይሉ ዘንድ ያስገደዳቸው ኢትዮ 360ዎች ▬▬▬▬▬▬ ➔የትኛውም መረጃ እውነት ሆኖ እስካገኙት ድረስ ጉዳትና ጥቅሙን ሳይመረምሩ እንደ ወረደ መዘርገፍ የሚቀናቸው፤ ➔ፖለቲካዊ ትንቢታቸው መጥፎም ሆነ ደግ ሳይሰምር ከሚቀር ይልቅ የተናገሩት ደርሶ ‹‹ብለን ነበር›› ማለት የሚመስጣቸው፤ ➔የመንግሥትን ያህል ህውሓትን የመታገል ወኔ የሚጎድላቸው ➔ሸዋ ግንባር ላይ ተገኝቶ ጦሩን መምራት የጀመረን መንግሥት ማበረታታት ያለውን ወቅታዊና ሕዝባዊ ፋይዳ ተረድተው ድጋፍ ከመቸር ይልቅ ‹‹ዘመቻውን አቋርጦት ሲመለስ መንገድ ላይ ጠብቆ መንቀፍ የሚቀናቸው… ➔ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ጋዜጠኞችና ተንታኞች ልብ ያላሉትን የጥፋት ድግስ ባሕር ማዶ ሆነው ማስተዋል የሚቻላቸው… ➔በእነ ዋልታና ፋና የማይነገሩ ሕዝባዊ ጩኸቶችን ይፋ በማድረግ በኩል ትልቅ ሚና ያላቸው፤ ➔በብልጽግና መንገድ ኢትዮጵያን ማትረፍ እንደማይቻል የገባቸው...

በአሜሪካ ተረቅቆ የወጣው HR6600 በብልጽግና ጸድቆ አማራዎች ላይ ተጥሏል‼️ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ የአሜሪካ መንግሥት ያረረቀውን ማዕቀብ የብልጽግና መንግሥት አጽድቆ አማራ ሕዝብ ላይ ተግባራዊ ካደረገው ቆይቷል፡፡ ለምሳሌ ያህል ለአማራ ሕዝብ ርሐብ ማለት ‹‹የትግራይ ገበሬዎች እንዲያርሱ›› በሚል ምክንያት የጦርነት ሜዳው ተገትቶ የተጣለበት እለት… ብሎም ከመተከልና ወለጋ ጥቃት አምልጦ የተፈናቀለ እለት ከመንግሥት እጅ የተቀበለው አስከፊ ክስተት እንጂ ካድሬዎች እንደሚያወሩት ከማዕቀቡ ጋር ተያይዞ የሚመጣ የወደፊት ስጋት አይደለም፡፡ እንደ ደረጀ ሃ/ወልድ የተንገፈጠጠ ቦርጫቸው የሕዝብን ርሐብ ማየት የጋረዳቸው ካድሬዎች ግን ‹‹በሠራሁት ጎጆ እና በኖርኩበት ቀዬ ላይ እጦቴን እና ርሐቤን ችዬ እኖር ዘንድ ፍቀዱልኝ›› ለሚል ጥያቄው ‹‹በኩታ ገጠም የዘራነው ስንዴ ሲደርስ በእርዳታ መልክ እንልክልኻለን እንጂ አርሰህ መብላት አትችልም›› ተብሎ በአገሩ ውስጥ አገር የሚፈልገውን ሕዝብ ወደፊት በሚመጣ ርሐብ እያስፈራሩት ነው፡፡ ሲቀጥል ደግሞ በወልቃይትና ራያ ጉዳይ የአሜሪካ አቋም ‹‹ሕገ-መንግሥቱን መሠረት አድርጎ መፈታት አለበት›› የሚል መሆኑ ይታወቃል፡፡ ይሄንንም የአሜሪካ አቋም መንግሥት አሻሽሎ በራያ ላይ ተግባራዊ በማድረጉ የተነሳ ከጠላት እጅ ወድቀው በጥይትና በርሐብ ሲንገበገቡ የከረሙ የራያ ተወላጆች አካባቢያቸውን ጥለው መፈናቀል ጀምረዋል፡፡ በወልቃይት ጉዳይም መንግሥት ከአሜሪካ የተለየ አቋም እንደሌለው በግልጽ ተናግሯል፡፡ ወራሪው ቡድንም ራያን ከራያዎች ማጽዳት እንደቻለው ሁሉ ወልቃይትንም ከወልቃይቶች እጅ ነጥቆ ለመውሰድ ዝግጅት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ‹‹ማዕቀቡ የአማራን ፋኖ እና ልዩ ሃይል ተጠያቂ ያደርጋል›› የሚለው ጉዳይም ሥጋት ሳይሆን ተግባራዊ መሆን የጀመረ ፕሮጀክት በመሆኑ የልዩ ሃይሉን አመራሮችን ገለል የማድረግ ሥራ ከተሰራ በኋላ ባልተሳተፈበት ተንቀሳቃሽ ምሥል የልዩ ሃይሉን ሥም ማጠልሸት ተጀምሯል፡፡ የፋኖ መሪዎችንም ‹‹ኢ መደበኛ ሃይል›› በሚል ፍረጃ መግደሉ የተለመደ ዜና ሆኗል፡፡ ከዚህ ባለፈ ደግሞ ፋኖን እና ልዩ ሃይሉን የመምታት ፕሮጀክት ያሳካ ዘንድ ተስፋ የተጣለበት የህውሓት አሸባሪ ሰፊ ዝግጅት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ‹‹ከህውሓት ጋር ድርድር አይታሰብም›› የሚለው አቋምም የኢሳት ጋዜጠኞችን እንጂ የመንግሥትን አቋም አያንጸባርቅም፡፡ በዘመቻው እኩሌታ ላይ የተኩስ አቁም ያደረገው መንግሥትማ ወደ ድርድር ለመግባት የህውሓት ተደራዳሪ ልዑክ ወደ ወልቃይት ምድር የሚገባበትን ቀን በመጠባበቅ ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህ ባለፈ ግን መንግሥት ለታጠቃቸው ድሮኖች ያለን አተያይ አሜሪካና አውሮፓ ለራሽያ ኑውክሌር ካላቸው አተያይ የተለየ ስላልሆነ የጦር መሳሪያ ግዢ ላይ የሚጣለው ማዕቀብ የሚያሳስብ አይደለም፡፡ እናስ… የአሜሪካንን ሐሳብ ከመቀበልም አልፎ በሒደት ላይ ያለውን ማዕቀብ አጽድቆ አማራዎች ላይ ከጣለ በኋላ ‹‹ኖ ሞር የሚል ጩኸታችሁን አቁሙልኝ›› የሚል ትዕዛዝ ያስተላለፈው መንግሥት የትኛውን ትዕዛዛቸውን ሳያስፈጽም ቀርቶ ነው ‹‹HR-6600 የተባለ ማዕቀብ የሚጣልበት?›› ደግሞስ በውጭ አገር የሚኖረው ዲያስፖራ ሁሉ የአማራ ማንነት ያለው ይመስል ‹‹በወገኔ ላይ ማዕቀብ በጣለው መንግሥት ላይ የሚጣለውን ማዕቀብ እቃወማለሁ›› የሚል መፈክር ይዞ እንዲወጣ የሚለመነው ስለምን ይሆን? Share

ስለ HR 6600 አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ የአማራ ግፉዓን ድምጽ ለመሆን ሳስብ የመናገር ነፃነት ስለተሰጠኝ ሳይሆን ከአቶ ደመቀ ወንበር ይልቅ የአሳምነው ጽጌ መቃብር ምቹ መሆኗን ተረድቼ ስለሆነ የትኛውም
ስለ HR 6600 አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ የአማራ ግፉዓን ድምጽ ለመሆን ሳስብ የመናገር ነፃነት ስለተሰጠኝ ሳይሆን ከአቶ ደመቀ ወንበር ይልቅ የአሳምነው ጽጌ መቃብር ምቹ መሆኗን ተረድቼ ስለሆነ የትኛውም አይነት ዛቻ አያሰንፈኝም። እናም እንደ የአማራ ተወላጅ HR6600ን እንዲቃወም ከፈለጋችሁ የሚከተሉትን ጥያቄዎቼን መመለስ ይገባችኋል። ➔በሕይወት የመኖር መብታቸውን ማስከበር ሲገባችሁ በትሕነግ፣ በኦነግና በጉምዝ ታጣቂ ሲገደሉ የኀዘን መግለጫ ነፍጋችሁ፣ ከጋዜጠኞች ካሜራ ደብቃችሁ፣እልቂታቸውን በሰበር ዜና ሸፋፍናችሁ... በዶዘር በቀበራችኋቸው ዜጎች ሥም የአማራን ሕዝብ ይቅርታ እንዲትጠይቁ፥ ➔የኦነግ ሸኔ አመራር ሆነው መንግሥት መር ጭፍጨፋ ይካሄድ ዘንድ መንገድ ሲጠርጉ የከረሙ የብልጽግና አመራሮች በቁጥጥር ስር እንዲውሉ፤ ➔እነ ጌታቸው ረዳን የማደን ተግባር ተጀምሮ እንዲቀጥል፤ ➔ የትምህርት ውጤታቸው እንዲበላሽ የተደረገባቸው የአማራ ተማሪዎች ውጤት ተስተካክሎ ይቅርታ እንዲጠይቁ፤ ➔የጦር መሳሪያ ግዢ ልንከለከል ነው ከሚል ለቅሶ በፊት "ኢመደበኛ ሃይል" በሚል ፍረጃ በድሮን የምትዝቱበት "ፋኖ" ከአማራ ልዩ ሃይልና ሚኒሻ ጋር ላደረገው ተጋድሎ እውቅና እንዲሰጠው፤ ➔ወደ አገራቸው ከተጠሩ በኋላ በክህደት አርጩሜ ተገርፈው የተባረሩ ዲያስፖራዎች ይቅርታ እንዲጠየቁ፤ ➔ማሳ ለማሳ በመዞር ፈንታ የተራቡ ዜጎችን እንዲትጎበኙና የእለት ጉርስ እንዲታደርሱ እጠይቃለሁ። ከዚህ ውጭ ግን ፋኖን በኢመደበኛ ሃይልነት የፈረጀ ሃይል "ጥይት መግዛት ተከለከለ" ብዬ የምጮህበት አፍ የለኝም።

ለአማራ ዲያስፖራ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ዓመቱን ሙሉ የምዕራባውያንን ሤራ ሲያፈራርሱና ዶላር ሲለግሱ ከከረሙ ዲያስፖራዎች መሀከል አብዛኞቹ አማራዎች መሆናቸውን ያወቀው ከንቱ መንግሥት "ኑ በአገራችሁ በ
+2
ለአማራ ዲያስፖራ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ዓመቱን ሙሉ የምዕራባውያንን ሤራ ሲያፈራርሱና ዶላር ሲለግሱ ከከረሙ ዲያስፖራዎች መሀከል አብዛኞቹ አማራዎች መሆናቸውን ያወቀው ከንቱ መንግሥት "ኑ በአገራችሁ በዓልን አክብሩ" ብሎ ከጠራቸው በኋላ የገና ቀን አቦይ ስብሐትን በመፍታት የዳውን ዳውኖች መሳቂያ አደረጋቸው። እንደ ፋኖ ከባድ ክሕደት ፈጸመባቸው። አሁን ደግሞ "HR 6600 የተባለ ማዕቀብ ሊጣልብኝ ስለሆነ 'ዲያስፖራ' በሚል ሥም የምጠራህ 'አማራ' ሆይ እባክን ድረስልኝ" እያለ ነው። እናም... ያለ እኛ ድጋፍ የትም አትደርስም ብለህ ንገርልኝ‼️ ይሄን ባንድራ ይዞ መውጣት ለግድያ ስለሚዳርግ የኦነግን ባንድራ እስክትልክልኝ ድረስ አልሰማህም በልልኝ‼️ Share

ካልተቀጠቀጠ- አይበላም ቋንጣ የዋግ ሹሞች አገር- ላስታና ሰቆጣ ……………..ይባል ነበር ወትሮ ይሄው ቋንጣ ሆነ- የሰው ልጅ ዘንድሮ፡፡ ጥጋበኛ መንግሥት- ሰርክ የሚፈተፍት- ሁሌ የሚደግስ በቢሊዮን
+1
ካልተቀጠቀጠ- አይበላም ቋንጣ የዋግ ሹሞች አገር- ላስታና ሰቆጣ ……………..ይባል ነበር ወትሮ ይሄው ቋንጣ ሆነ- የሰው ልጅ ዘንድሮ፡፡ ጥጋበኛ መንግሥት- ሰርክ የሚፈተፍት- ሁሌ የሚደግስ በቢሊዮን በጀት- አበባ የሚያለማ- ቢሮውን የሚያድስ ካልተዘራ ማሣ- ስንዴ ኤክስፖርት አርጎ- ዶላር ዩሮ የሚያፍስ የተረገመ ሕዝብ- ሳልሞት ድረሱልኝ- ለሚል ማመልከቻው ስንዴ ሲጠባበቅ- ስንፍና የሚል መልስ- መንግሥት የለገሰው ያልታደለ ሕጻን- ሰው ሰራሽ ቸነፈር- ባቄላ አሹቅ ነፍጎት ርሐብ ሲግጠው - እንደ በቆሎ እሸት ሞት ከመንግሥት ብሶ ፥ እንዴት ጨከነበት? (የአንድ ወር ደሞዜን በዚህ ሳምንት ውስጥ ልኬ የአንድ ሕጻን ነፍስ አተርፋለሁ፡፡ እናንተስ?)

ቢመርህም ዋጠው... አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ በኢትዮጵያም ሥም ተደራጅቶ ለመጣ ፓርቲ ሁሉ ልቡን እና ገንዘቡን ሲሰጥ የኖረው የአማራ ሕዝብ አንድ እንኳን ጠንካራ ድርጅት መፍጠር ያልቻለው... በእርሱ ችግር ሳይሆን አብዛኞቹ ፓርቲዎች "በሕዝብና በአገር ሥም የቤተሰብ ጥቅም ማረጋገጥ" የሚል ራዕይ ይዘው የሚመሠረቱ የንግድ ድርጅቶች በመሆናቸው ነው። "ልንታገልልህ መጥተናል" ብለው በውጭም ሆነ በአገር ውስጥ የሚኖረውን ሕዝብ ገንዘቡን ሲያልቡትና በስብሰባ ሲያዝጉት ከኖሩ በኋላ አንዳንዶቹ በውስጣቸው በሚፈጠር የጥቅም ግጭት እራሳቸውን ሲያከስሙ፣ አንዳንዶቹ ደግሞ "ፓርቲዬን ሽጨልኻለሁ" ብለው ከመንግሥት ጋር የሚፈራረሙ በመሆናቸው ነው። ስለዚህ ከፕሮፌሰር አስራት እና ከእስክንድር ነጋ ውጭ የትኛውም ፖለቲከኛ እራሱን እንጂ ሕዝብን የሚወቅስበት ሞራል የለውም። ፊደል የቆጠረውና በአባልነት የታቀፈው ሃይልም ወደ ትችት የሚገባው ከብዙ ድጋፍ እና እገዛ በኋላ በመሆኑ ታጋይ ነኝ ብሎ ለመጣ ድርጅት የእድሜ ልክ አገልጋይ ባለመሆኑ ሊወቀስ አይችልም።

ብልጽግና ባደራጀው ሃይሎች ንጹሓን ሲጨፈጨፉ ወይም ደግሞ ጥምቀት ለማክበር የወጡ ምዕመናን በኦሮሚያ ፖሊስ ሲቀጠፉ መንግሥትን የምትቆጣ አንዲት ቃል ተንፍሶ አያውቅም። ጳጳሱ ህውሓትን ወክለው አለቆቹን
ብልጽግና ባደራጀው ሃይሎች ንጹሓን ሲጨፈጨፉ ወይም ደግሞ ጥምቀት ለማክበር የወጡ ምዕመናን በኦሮሚያ ፖሊስ ሲቀጠፉ መንግሥትን የምትቆጣ አንዲት ቃል ተንፍሶ አያውቅም። ጳጳሱ ህውሓትን ወክለው አለቆቹን ሲያጠቁበት ግን ፓትርያርኩን የሚወነጅሉ የድፍረት ንግግሮችን ይዞ Live ይገባል። እንደ እውነቱ ከሆነ ግን የዚህ እኩይ መንግሥት አማካሪ ሆኖ ከመሥራት በላይ ትልቅ ጥፋት የለም። የሉሲፈርን ማንነት በመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችና በሚያማምሩ ጽሑፎች እየጋረዱ ከማኖር በላይ የከፋ ወንጀል የለም።

ድሮ ያለ ትምህርት መንጃ ፍቃድ ማውጣት የሚሹ አማራዎች ኦህዴድ ከሚመራው ክልል ሄደው ይገዙ ነበር። ወደፊት ደግሞ ይህ ትውልድ ገዳይ ድርጅት ልክ እንደ መንጃ ፍቃድና መሬት የማትሪክ ውጤት መሸጥ ይጀምራል።

የኦነግ ወይም የትሕነግ አክቲቪስቶች በአቶ ሙስጠፌ ሥም የሀሰት አካውንት ከፍተው "የሶማሌው ፕሬዝዳንት የአብን ፕሬዝዳንት ሆኑ እንዴ?" የሚል ጥያቄ የሚፈጥሩ ጽሑፎችን እየለጠፉ ነው። የእነዚህም ጽሑ
የኦነግ ወይም የትሕነግ አክቲቪስቶች በአቶ ሙስጠፌ ሥም የሀሰት አካውንት ከፍተው "የሶማሌው ፕሬዝዳንት የአብን ፕሬዝዳንት ሆኑ እንዴ?" የሚል ጥያቄ የሚፈጥሩ ጽሑፎችን እየለጠፉ ነው። የእነዚህም ጽሑፎች ዋነኛ ዓላማ በክልሉ ውስጥ ጤናማ ፖለቲካን ተግብሮ ለሁሉም ዜጎች ምቹ የሆነ ምቹጌ የፈጠረውን ፕሬዝዳንት፤ በአማራ ጠል ኃይሎች ጥርስ ውስጥ ማስገባት መሆኑ ቢታወቅም... እኛ ደግሞ በሐሰት አካውንት የሚፃፉትን እኒህን ጽሑፎች እያጋራን አቶ ሙስጠፌ ማስተባበያ ይሰጡ ዘንድ እያስገደድናቸው ነው።

ለፕሮፌሰሩ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ በከባድ መሣሪያ ተኩስ እየተናጡ እና በኩራዝ ጭስ እየተጨናቦሱ እንደ ነገሩ አንብበው ለፈተና የቀረቡ የአማራ ክልል ተማሪዎች ውጤት ከሌሎች ክልሎች በተለየ መልኩ ሆን ብ
ለፕሮፌሰሩ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ በከባድ መሣሪያ ተኩስ እየተናጡ እና በኩራዝ ጭስ እየተጨናቦሱ እንደ ነገሩ አንብበው ለፈተና የቀረቡ የአማራ ክልል ተማሪዎች ውጤት ከሌሎች ክልሎች በተለየ መልኩ ሆን ብሎ እንዲሳሳት መደረጉ ተረጋግጧል፡፡ ተፈታኞቹ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት መልስ ፈንታ ክልልን እና ሥምን መሠረት አድርገው ውጤት በሚተምኑ ከንቱዎች እጅግ አስነዋሪ ተግባር ተፈጽሞባቸዋል፡፡ እናም ለተፈጸመው አሳፋሪ ድርጊት ተቋሙን እንጂ እርስዎን በዚያ ልክ አውርጄ መወንጀል ባልሻም እንደ አንድ ዜጋ ግን ለሚከተሉት ጥያቄዎች አፋጣኝ መልስ እንዲሰጡ እጠይቃለሁ፡፡ ➔እንደ ኮንዶሚንየም እጣ የተቋሙን ቴክኖሎጂ በመጥለፍ የተማሪዎችን ውጤት በእነሱ ችሮታ ላይ እንዲመሰረት አድርገው በአማራ ክልል ውስጥ የተፈተኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን ውጤት ዝቅ ያደረጉ ባለሙያዎችና ሃላፊዎች... ለሌሎች ደግሞ የፈተና መልስ ሲሰጡ እንደነበረው ሁሉ ከፍ ከፍ ያለ ውጤት የማይሰጡበት ምክንያት አይኖርም፡፡ ስለዚህ ቅሬታ ባቀረቡ ተማሪዎች ውጤት ፈንታ የሁሉም ተማሪ ውጤት እንደገና እንዲታረም ማድረግ ይጠበቅብዎታል፡፡ ➔ሲቀጥል ደግሞ የተማሪዎች ውጤትን ከፍ እና ዝቅ አድርገው በማዛባት ትውልዱ ላይ ጥቃት የፈጸሙ የተቋሙ ባለሙያዎችና አመራሮች ላይ የማጣራት ሥራ ከተሠራ በኋላ እርምጃ ወስደው ለሕዝብ ማሳወቅ ይገባዎታል። ➔በመጨረሻም በዲሸቃ እና በሙዚቃ ድምጽ ሲያጠኑ የከረሙ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡበትን ነጥብ ተመሳሳይ ማድረግ ተገቢ አለመሆኑን ተረድተው ማስተካከያ እንዲያደርጉ እንደ አንድ ዜጋ እጠይቃለሁ፡፡ ይሄን ማድረግ ካልቻሉ ግን በእርስዎ የሥልጣን ዘመን የተፈጸመው ይህ አስነዋሪ ድርጊት የተማሪዎቹን እጣ ፈንታ የሚያበላሽ ብቻ ሳይሆን የእራስዎን ሥም እና ታሪክ ሙሉ ለሙሉ የሚያጠለሽ መሆኑ እርግጥ ነው፡፡

ወደ ዩኒቨርስቲ ከሚገቡ 152,000 ተማሪዎች መሀከል 130,000 ከኦሮሚያ ክልል መሆኑ ታውቋል።😁 ከጠሚው ንግግር ውስጥ ኦሮሚያን፤ከተግባሩ ውስጥ ደግሞ ኢትዮጵያን ማግኘት አይቻልም የምልህ በምክንያት ነው!