1 111
订阅者
-224 小时
+57 天
+430 天
数据加载中...
吸引订阅者
七月 '26
七月 '26
+19
在0个频道中
六月 '26
+16
在1个频道中
Get PRO
五月 '26
+17
在0个频道中
Get PRO
四月 '26
+26
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+13
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+13
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+14
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+13
在0个频道中
Get PRO
十一月 '25
+18
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+23
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+30
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+28
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+27
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+8
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+15
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+35
在1个频道中
Get PRO
三月 '25
+31
在1个频道中
Get PRO
二月 '25
+17
在0个频道中
Get PRO
一月 '25
+29
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+55
在1个频道中
Get PRO
十一月 '24
+38
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+45
在1个频道中
Get PRO
九月 '24
+80
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+8
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+71
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+72
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+115
在0个频道中
Get PRO
四月 '24
+76
在0个频道中
Get PRO
三月 '24
+68
在0个频道中
Get PRO
二月 '24
+120
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+171
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+515
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 28 七月 | +1 | |||
| 27 七月 | 0 | |||
| 26 七月 | 0 | |||
| 25 七月 | +4 | |||
| 24 七月 | +1 | |||
| 23 七月 | +1 | |||
| 22 七月 | +1 | |||
| 21 七月 | +2 | |||
| 20 七月 | 0 | |||
| 19 七月 | 0 | |||
| 18 七月 | +1 | |||
| 17 七月 | 0 | |||
| 16 七月 | +1 | |||
| 15 七月 | 0 | |||
| 14 七月 | 0 | |||
| 13 七月 | 0 | |||
| 12 七月 | 0 | |||
| 11 七月 | +1 | |||
| 10 七月 | 0 | |||
| 09 七月 | 0 | |||
| 08 七月 | +1 | |||
| 07 七月 | +1 | |||
| 06 七月 | 0 | |||
| 05 七月 | 0 | |||
| 04 七月 | +2 | |||
| 03 七月 | +1 | |||
| 02 七月 | 0 | |||
| 01 七月 | +1 |
频道帖子
| 2 | 没有文字... | 89 |
| 3 | ፓርቲው ዲሞክራሲን ለማፅናትና የሕዝብን ኑሮ ለማሻሻል የጀመራቸውን ውጤታማ ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ
ብልፅግና ፓርቲ ዲሞክራሲን ለማፅናት የሕዝብን ኑሮ ለማሻሻል እያከናወናቸው የሚገኙ ስኬታማ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለጹ።
በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም ግምገማና የ2019 በጀት ዓመት መሪ ዕቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል።
በዚህ ወቅትም የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ እንዳሉት በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ፓርቲውን በአሰራር፣ በሰው ሀይል እና በአደረጃጀት የማጠናከር ስራ ተሰርቷል።
በተጠናቀቀው የበጀት አመት የብልፅግና ፓርቲ ሀገር ለመምራት የሚያስችለውን ድምፅ ከማግኘት ባለፈ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒነት ያለው ምርጫ በማካሄድ እንደሀገርና ክልል ዲሞክራሲን ለማፅናት መሰረት የጣሉ ስኬታማ ስራዎች መሰራታቸውን አንስተዋል።
ገዥ ትርክትና ቅቡልነት እንዲረጋገጥ በመሰራቱም ሀገራዊ አንድነትን የሚያጎለብቱ አዎንታዊ ስኬቶች ተመዝግበዋል።
የአመራሩና የአባላት የአስተሳሰብና የተግባር አንድነት ጎልቶ የወጣበት በመሆኑ ተደራራቢ ተልዕኮዎች በስኬት መተርጎማቸውን አብራርተዋል።
የ2019 በጀት ዓመት ዕቅዶችም በተሻለ አፈጻጸም እንዲተገበሩ ሁሉም የፓርቲ መዋቅሮችና የመንግሥት ተቋማት በቅንጅት፣ በተጠያቂነትና በውጤት ተኮር አሰራር ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ አሳስበዋል።
በሚታቀዱ ስራዎች ላይም ነባራዊ ሁኔታዎችን ታሳቢ ያደረገና ያሉን ሃብቶችን ያገናዘበ እንዲሁም ሊገጥሙ የሚችሉ ተግዳሮቶችን ታሳቢ ያደረጉ መሆን ይገባቸዋል ነው ያሉት።
የፓርቲና የመንግሥት ስራዎችን በማቀናጀት በተለይም የስራ ዕድል ፈጠራን ለማስፋት፣ የገበያ መረጋጋትን በማረጋገጥ የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
እንዲሁም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት የሚያሳድጉ ስራዎች ከመተግበር በተጨማሪ ልመናንና ተረጂነትን ለመቀነስ እንደሚሰራ አብራርተዋል።
በተለይም ከተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችና ከሲቪክ ማህበራት ጋር የቅንጅት ስራዎች በማስቀጠል የተገኙ ስኬቶችን የበለጠ ማላቅ አስፈላጊ መሆኑን አመላክተዋል።
የተጀመሩ የንቅናቄ ስራዎች ባህል እንዲሆን ማድረግ ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት የማጠናከር ስራም ትኩረት መስጠት እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።
በህዝብና በመንግስት መካከል የበለጠ መተማመንን የሚፈጥሩ ስራዎች ላይም በላቀ ትኩረት ይሰራል ብለዋል።
ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማነት እየተደረጉ የሚገኙ ድጋፎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ነው ያሉት።
የአደረጃጀትና የአሰራር ክፍተቶች ስለመኖራቸው መፈተሽና ማስተካከያ ማድረግ እንደሚገባ ያነሱት አቶ ጌቱ ለዚህም የአቅም ግንባታ ስራዎች የማከናወንና የክትትልና ድጋፍ ስራዎች በትኩረት ይሰራል ሲሉ ተናግረዋል።
"አዲሱ በጀት ዓመት ህዝባችንን ይበልጥ የምናገለግልበት፣ ክልሉን የብልፅግና ተምሳሌት የማድረግ ጉዟችንን አጠናክረን ለማስቀጠል ጠንካራ ክትትልና ድጋፍ የሚደረግ መሆኑን ገልጸዋል።
የታቀዱ ግቦችን ለማሳካት በየደረጃው የሚገኘው አመራር በቁርጠኝነትና በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት መሥራት እንደሚገባውም አጽንኦት ሰጥተዋል። | 73 |
| 4 | 没有文字... | 97 |
| 5 | የክልሉ ምክር ቤት የአስፈጻሚ አካላትን ተግባራት በተቀናጀ መንገድ ድጋፍና ክትትል በማድረጉ ውጤት ተገኝቷል
የሐረሪ ክልል ምክር ቤት የአስፈጻሚውን አካላት ተግባራት በተቀናጀ መንገድ ድጋፍና ክትትል በማድረጉ ውጤት መገኘቱን የክልሉ ምክር ቤት አፈጉባኤ ሱልጣን አብዱሰላም ገለጹ።
የክልሉ ምክር ቤት አፈጉባኤ አቶ ሱልጣን አብዱሰላም፣ ምክር ቤቱ የአስፈፃሚውን አካላት የአምስት አመታት የስራ እቅድና አፈጻጸም የክትትልና የድጋፍ ስራዎችን አስመልክተው ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም ምክር ቤቱ ባለፉት አምስት ዓመታት በእቅድ የያዛቸውን ተግባራት ለማሳካት ያደረገው ርብርብ ውጤታማ እንደነበር ነው የገለጹት።
ምክር ቤቱ ባሉት አደረጃጀቶች በእቅድ የያዛቸውን ሥራዎች የክትትልና የቁጥጥር ሥራዎችም በተቀመጡ አቅጣጫዎች መሰረት በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን ገልጸዋል።
ምክር ቤቱ አስፈጻሚው አካል የህዝብን የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ የወጡ ህጎችና ደንቦች መልኩ ስራ ላይ መዋሉን ሲከታተል መቆየቱን አንስተዋል።
በምክር ቤቱ የሚወጡ ህጎች የዜጎችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንደሆነ የገለጹት አፈ ገባኤው በተለይ ምክር ቤቱ በሕግ የተሰጠውን ዋና ዋና ተልዕኮዎች ለማሳካት የሰራቸው ሥራዎች ውጤታማ ናቸው ብለዋል።
የህዝቡን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥያቄዎች በዴሞክራሲያዊ መንገድ እንዲፈታ በማድረግ የውክልና ኃላፊነትን በአግባቡ መወጣቱን ገልጸዋል።
በክልሉ በኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ህዝቡ ላነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ በመስጠት የህዝብ ውክልናን ማረጋገጥ እንደተቻለ አፈ ጉባኤ አስገንዝበዋል።
በቋሚ ኮሚቴዎቹና በሚቀርቡ ሪፖርቶች የተቀናጀ ድጋፍና ክትትል በማድረግ ውጤታማ ስራዎች እንዲከናወኑ አድርጓል ብለዋል።
በክልሉ በቱሪዝም፣ ግብርና፣ በኮሪደር ልማት፣ በስራ ዕድል ፈጠራ፣ በጤና፣ በትምህርት፣በሰላምና ፀጥታ፣ በፍትህ ስርዓት፣ በኢንቨስትመንት፣በኑሮ ውድነት ቅነሳ፣ በገቢ አሰባሰብ እና በፕሮጀክቶች አፈጻጸም የተሰራው ስራ ተጨባጭ ውጤት መመዝገቡን የገለጹት አፈ ጉባኤው ለውጤቱም የድርሻውን ማበርከቱን ገልፀዋል።
የሕግ የበላይነትን ለማረጋገጥ የፍትህ አካላት ሚና ጉልህ መሆኑን የገለጹት አፈ ኡባኤው የፍትህ ዘርፍና የዳኝነት አካሉን ሪፎርም ማድረግ አበረታች ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል የፍርድ ቤቶችን የበጀት እና በዳኞች ሹመት ላይ ቁጥጥር በማድረግም ለፍትህ ስርአቱ ስኬት የበኩሉን መወጣቱን አንስተዋል።
ምክር ቤቱ አስፈፃሚውን በመከታተልና በመቆጣጠር ውጤታማ ስራ ማከናወኑን ገልጸዋል፡፡ | 94 |
| 6 | 没有文字... | 91 |
| 7 | በ2019 በጀት ዓመት የትምህርት ጥራትን ይበልጥ ለማጎልበት ይሰራል-አቶ አርሰናል አብዲ
በ2019 በጀት ዓመት የትምህርት ጥራትን ይበልጥ ለማጎልበት በትኩረት እንደሚሰራ የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ አርሰናል አብዲ ገለፁ።
የሀረሪ ክልል ትምህርት ቢሮ በ2019 በጀት ዓመት በሚከናወኑ ጉዳዮች ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በያዝነው የበጀት ዓመት የትምህርት ጥራትን ይበልጥ በማጎልበት ሁሉን አቀፍ ስራዎች በትኩረት ይሰራሉ።
ዘርፉን ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ የትምህርት ዘርፉን ሪፎርም ከማድረግ ጀምሮ የመምህራንና ትምህርት አመራሮችን አቅም ለማጎልበት ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ገልፀዋል።
በተለይ በትምህርት ለትውልድ ንቅናቄ የትምህርት ቤቶችን ደረጃ ለማሻሻል ብሎም በግብዓት እንዲደራጁ የማድረግ ስራ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።
በትምህርት ቤቶች የተጀመሩ የተማሪ ምገባ መርሀ-ግብርን በማጎልበት የተማሪዎች የመጠነ ማቋረጥና መቅረት ምጣኔን በመቀነስ የትምህርት ቅበላ አቅምን ለማሳደግም ይሰራል ብለዋል።
ለዚህም በክልሉ በከተማና በገጠር የሚገኙ 40 ሺ ተማሪዎችን የምገባው ተጠቃሚ ለማድረግ 46 ሚሊዮን ብር መመደቡን ገልጸዋል።
በሌላ በኩል በግል ትምህርት ቤቶች ከማህበረሰቡ ለሚነሱ ቅሬታዎችን አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ ለማረም እንደሚሰራ አክለዋል።
በተጨማሪም የትምህርት መሠረተ ልማቶች፣ የመማሪያ ፋሲሊቲዎች እና የዲጂታል ቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማሻሻል የመማርና የማስተማር ሂደት ዘመናዊ፣ ተደራሽና ውጤታማ እንዲሆን ይደረጋል ብለዋል።
በሦስቱ የገጠር ወረዳዎች ከቅድመ መደበኛ ትምህርት ቤቶች ጀምሮ የአንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ግንባታ እንደሚከናወን የገለጹት ምክትል ኃላፊው በክልሉ እየተገነባ የሚገኝው ሞዴል 2ኛ ደረጃ ትምህርት በቀጣይ መስከረም ስራ ለማስጀመር ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።
የተማሪ ውጤትን ለማሻሻል ከቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጀምሮ ትኩረት መሰጠቱ የገለፁት አቶ አርሰናል የመማሪያ መፅሀፍ ስርጭት ምጣኔን በተመለከተም ከቅድመ መደበኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች 1 መፅሀፍ ለ1 ተማሪ ተደራሽ ይደረጋል ብለዋል።
የልዩ ፍላጎትና የጎልማሶች ትምህርትን ጨምሮ ሁሉም ተማሪዎች ተገቢ፣ ጥራት ያለው፣ ፍትሃዊና ተደራሽ ትምህርት እንዲያገኙ በማድረግ በዕውቀት፣ በክህሎትና በመልካም ሥነ ምግባር የተገነቡ እንዲሁም ለሥራና ለሀገር ግንባታ ዝግጁ ዜጎችን ማፍራት እንደሚሰራ ጠቁመዋል።
በተለይም በ6ኛ፣ በ8ኛ እና በ12ኛ ክፍል የሚደረጉ ክልላዊና ሀገራዊ ፈተናዎች የማለፍ ምጣኔን የበለጠ ለማሳደግ በመማር ማስተማር፣ በትምህርት ድጋፍና በተከታታይ ክትትል ላይ ልዩ ትኩረት ይሰጣል ነው ያሉት።
በበጀት አመቱ ከቅድመ መደበኛ እስከ ሁለተኛ ደረጃ 91 ሺህ 411 ተማሪዎች ተመዝግበው ትምህርታቸውን ይከታተላሉ ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል። | 99 |
| 8 | https://www.facebook.com/100003553497859/posts/27150756774626072/?app=fbl | 116 |
| 9 | 没有文字... | 113 |
| 10 | በክልሉ በበጀት አመቱ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግና የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የሀረሪ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ሮዛ ኡመር ገለፁ።
በሀረሪ ክልል በተያያዘ የ2019 ምርትና ምርታማነትን በማሳደግና የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ታቅዶ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሮዛ ኡመር ገለፁ።
የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ልማት ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሮዛ ኡመር በ2019 ሊከናወኑ የታቀዱ ስራዎችን በሚመለከት መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸው በክልሉ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ በተሰሩ ስራዎች ውጤቶች መመዝገባቸውን ገልፀዋል።
በዚህም የግብርና ልማትን በማሳደግ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር በተከናወኑ ተግባራት አበረታች ውጤቶች መገኘቱን ጠቅሰዋል።
በተለይም ዓመቱን ሙሉ መልማት ከሚችሉ ምርቶች መካከል በቆሎ አንዱና ዋነኛው መሆኑን ጠቅሰው የቦቆሎን ምርት በበጋና በበልግ ወቅቶች የማልማት ሥራ ሲከናወን መቆየቱን አንስተዋል።
በ2019 የበጀት አመትም ምርትና ምርታማነትን በማሳደግና የኑሮ ውድነቱን ለማረጋጋት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
በክልሉ በ2018 የበጀት አመት 2 ሺህ 160 ሄክታር መሬት በቦቆሎ መሸፈን መቻሉን ገልጸው፤ በዘንድሮው የመኸር እርሻ ወደ 2 ነጥብ 378 ሺህ ሄክታር ለማሳደግ ታቅዷል ብለዋል።
በክልሉ በተጠናቀቀው የበጀት አመት ስንዴ በሄክታር ከነበረበት 32 ኩንታል በያዝነው በጀት ዓመት ወደ 33 ኩንታል ለማሳደግ መታቀዱን ገልጸው 14 ሺህ 850 ኩንታል ይጠበቃል ብለዋል።
በተያዘው የበጀት አመት በመኸር እርሻ 11 ሺህ 956 ሄክታር መሬት በዘር እንደሚሸፈንና ከዚህ ውስጥ 2 ሺህ 378 ሄክታር መሬት በቦቆሎ ምርት የሚሸፈን መሆኑም ገልጸዋል።
በበልግና መኽር እርሻ የዝናብ እጥረትን ተቋቁመው በአጭር ጊዜ ምርት የሚሰጡ የማሽላ እርሻ ስራ በእጥፍ እንዲያድግና የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ ይሰራል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪም 4 ሺህ 700 ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ልማት የተለያዩ የአትክልትና ስራስር ሰብሎች እንደሚሸፈን የገለጹት ምክትል ርዕሰ መስተዳድሯ በከተማ ግብርና 537 ሄክታር ይሸፈናል ብለዋል።
አርሶ አደሩ የክረምት ወቅትን ብቻ ጠብቆ ከሚሰራው የግብርና ልማት እንዲላቀቅና አማራጮችን እንዲጠቀም ማድረግ ላይም እንዲሁ።
ለዚህም የግብዓት አቅርቦት፣ የመሬት ዝግጅትና የሙያተኛ አቅም ማጎልበት ሥራዎች ተከናውነዋል ነው ያሉት።
የእንስሳትና ዓሳ ምርትና ምርታማነት የሚያሳድጉ ስራዎች በልዩ ትኩረት ይሰራሉ ብለዋል።
እንዲሁም የአርሶ አደሩን ምርትና ምርታማነት የሚያሳድጉ ግብዓቶችን ከማቅረብ በተጨማሪ በገጠሩ አካባቢ የሌማት ትሩፋት መርሃግብር ውጤታማነት ለማሳደግ 18 የዶሮ መንደሮችን የመመስረት ስራ ይሰራል ሲሉ አብራርተዋል።
ከዚህ በተጨማሪም 600 ሄክታር ህብረተሰቡን ያሳተፈ የተፈጥሮ ሃብት ጥበቃ ስራዎች እንደሚከናወኑም አብራርተዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ተረጂነትን ዜሮ ለማድረስ የተጀመሩ ስራዎች ይጠናከራሉ ነው ያሉት። | 111 |
| 11 | 没有文字... | 128 |
| 12 | የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የመደጋገፍ እና ወንድማማችነት እሴት በሚያጠናክር መልኩ ተጠናክሮ ቀጥሏል
በክልሉ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የመደጋገፍና ወንድማማችነት እሴት በሚያጠናክር መልኩ ተጠናክሮ መቀጠሉን በብልፅግና ፓርቲ የሀረሪ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አስታውቋል።
በክልሉ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ በሰጡት መግለጫ እንዳሉት የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀት በማስተባበር በራስ አቅም የመልማት እድልን የሚፈጥር ነው ብለዋል።
ከሀገራዊ ከለውጡ ወዲህ ትኩረት የተሰጠው ይህ የበጎ ፈቃድ አገልግሎትም የህብረተሰቡ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች በማቃለል ረገድ የማይተካ ሚና እየተጫወተ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል።
በክልሉ በተጀመረው የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎትም የማጠናከሪያ ትምህርት በመስጠት፣ ችግኝ ተከላ፣ የነፃ ሕክምና አገልግሎት፣ ደም በመለገስ፣ የትምህርት ቤት ቁሳቁስ ድጋፍ የማሰባሰብ፣ የአቅመ ደካሞችን ቤት የመገንባትና የማደስ እንዲሁም ሌሎች ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን አስረድተዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ማዕድ ማጋራት፣ አዲስና ነባር የመማሪያ ክፍል ግንባታ እና እድሳት ፣ የትምህርት ቤቶች የተማሪ ወንበሮች ጥገና፣ ጽዳትና ውበት ስራዎችን ጨምሮ የማጣቃሻ መጽሀፍት የማሰባሰብ ስራ በበጎ ፍቃድ አገልግሎቱ የትኩረት የተሰጣቸው ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸዋል።
በመርሃግብሩም ከ344 ሺህ በላይ ማህበረሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በጎ ፈቃድ አገልግሎት የእርስ በእርስ መተሳሰብን እንዲሁም ሁለንተናዊ ትብብርና መተጋገዝን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ያበረክታል ብለዋል።
ከዚህ በተጨማሪም የዜጎችን አብሮነትና ወንድማማችነት የበለጠ እንዲጎለብት በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው የገለፁት ኃላፊው በዘንድሮው መርሃግብርም ይህንን እሴት በተግባር በሚያሳይ መልኩ እየተተገበረ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
የተጀመረው የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ሥራ የተለዩ የትኩረት መስኮች መነሻ ያደረገና ተጨባጭ ለውጥ ሊያመጣ በሚችል አግባብ እንዲፈጸም የክትትል እና ቁጥጥር ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል። | 120 |
| 13 | 没有文字... | 140 |
| 14 | የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ሐረር ፖሊስ ሆስፒታል ማስፋፊያ ፕሮጀክትን ጎበኙ
የሀረሪ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ እና ፌደራል ፖሊስ ጠቅላይ አዛዥ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የሐረር ፖሊስ ሆስፒታል የማስፋፊያ ፕሮጀክትን ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱ ወቅትም በፕሮጀክቱ የሚቀሩ ስራዎች በጥራትና በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ተገልጿል።
የማስፋፊያ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅም ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ተደራሽ ከማድረግ ባለፈ ሐረር ከተማን የጤና ቱሪዝም ማዕከል በማድረግ ረገድ የጎላ ሚና እንደሚያበረክት ተጠቁሟል።
በጉብኝቱ ላይም የክልሉ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስና የድሬዳዋ ከተማ ስትራቴጂክ የፖሊስ አመራሮች ተገኝተዋል። | 129 |
| 15 | 没有文字... | 133 |
| 16 | በክልሉ በክረምት የበጎ ፈቃድ የህጻናት፣ ታዳጊዎችና ወጣቶች የስፖርት ውድድር ተጀመረ
በሀረሪ ክልል በክረምት የበጎ ፈቃድ የህጻናት ታዳጊዎችና ወጣቶች የስፖርት ውድድር ተጀምሯል
የክልሉ ስፖርት ኮሚሽን ኮሚሽነር ሙራድ አብዲ የክረምቱን ወቅት የስፖርት ውድድሩን ለማድረግ ትርጉም ያለው ዝግጅት መደረጉን ገልጸዋል።
በዚህም በዘንድሮው የክረምት መርሀግብር ስፖርቱን ከማህበራዊ ልማት ጋር የማስተሳሰር ሰፊ ስራዎችን ለመስራት መታቀዱን ገልጸዋል።
የስፖርት ኮሚሽኑ ከወረዳና ቀበሌ ጀምሮ ባሉ መዋቅሮች ህጻና፣ ታዳጊዎችና ወጣቶችን በአንድ የጥላ ስር ለማሰባስብ እየሰራ ይገኛል ብለዋል።
ስፖርት ሁሉንም የማህበረሰብ ክፍል የሚያቀራርብ ድልድይ ነው ያሉት ኮሚሽነር ሙራድ ማህበራዊ ትስስርን በማጠናከር ብቁና ጤናማ ትውልድ ግንባታ ያለውን አስተዋጽኦ ከፍ ያለ መሆኑን ገልጸዋል።
የስፖርት ውድድሩ ከመዝናኛነት ባለፈ በሃገር አቀፍና አለምአቀፍ የስፖርት ተወዳዳሪ አትሌቶችን ለማፍራት የሚቀረጹበት እድል ይፈጥራል ብለዋል።
ህጻናት፣ ታዳጊና ወጣቶች ከትምህርት ነጻ ሆነው ሚቆዩበትን ጊዜ ከተለያዩ አልባሌ ተግባሮች ርቀው ጊዜያቸውን በአግባቡ መጠቀም የሚያስችል መሆኑንም አክለዋል።
በተለይም ማህበራዊ ሃላፊነትን ከስፖርታዊ ጨዋነት ጋር በማስተሳሰር ከስፖርቱ ባለፈ ማህበራዊ ሃላፊነታቸውን እንዲሁም በተለያዩ የልማትና የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ ተሳታፊ እንደሚሆኑ ገልጸዋል።
በዚህም በክረምቱ የስፖርት መርሀግብሩ ጎን ለጎን የስፖርት ቤተሰቦች እንደ ችግኝ ተከላ፣ የጽዳት ዘመቻና የደም ልገሳ ባሉ በጎ ተግባራትም እንደሚሳተፉ ገልጸዋል።
በዘንድሮ ክረምት ውድድር በተለያዩ የእድሜ እርከኖች የሚካሄዱ የአትሌቲክስ፣ ቅርጫት ኳስ፣ ቦክስ ጨምሮ ማርሻል አርትና የተለያዩ ውድድሮችን አካቶ እንደሚካሄድ ተገልጿል።
በመርሃግብሩ የሀረሪ ክልል የሴቶች ወጣቶችና ህጻናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ረምዚያ አብዱልወሃብ ለሴት ስፖርተኞች የንጽሕና መጠበቂያ ቁሳቁስ ድጋፍ አድርገዋል። | 132 |
| 17 | 没有文字... | 150 |
| 18 | 没有文字... | 115 |
| 19 | ታሪካዊ ቅርሶችን ከመታደግ እስከ ተመራጭ የቱሪስት መዳረሻነት የሐረር አስደናቂ የቱሪዝም ስኬት
መንግሥት ካስቀመጣቸው አምስት ቁልፍ የሀገር በቀል ኢኮኖሚ ማሻሻያ ምሰሶዎች መካከል አንዱ የሆነውን የቱሪዝም ዘርፍ ለማሳደግ፣ በታሪካዊቷ የሐረር ከተማ ሰፊ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
ጥንታዊ ውበቷን ከዘመናዊ ገጽታ ጋር በማሰናሰል አዲስ ገጽታን የተላበሰችው ሐረር፣ አሁን ላይ እየተተገበረ ባለው የኮሪደር ልማትና የቅርሶች እድሳት ስራ የቱሪዝም ዘርፉን ይበልጥ ተነቃቅታለች።
የዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ሀብት የሆኑት የሐረር ጀጎል ጥንታዊ፣ ሃይማኖታዊና ታሪካዊ ቅርሶች ይዘታቸውን ጠብቀው እንዲለሙና ለትውልድ እንዲተላለፉ የ"መደመር" እሳቤ ያመጣው ህያው ትሩፋት ነው።
ይህ በዘርፉ የተሰጠው ልዩ ትኩረት ለአደጋ ተጋርጠው የነበሩ ቅርሶችን ከማዳኑም ባሻገር፣ የቱሪዝም መዳረሻዎችን በማስፋትና የጎብኚዎችን ቆይታ በማራዘም ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ አቅም በእጅጉ አሳድጎታል።
በክልሉ የተከናወኑት ስኬታማ የቱሪዝም ማጎልበት ተግባራት፣ ከውጭ ሀገር ቱሪስቶች በተጨማሪ የሀገር ውስጥ ጎብኚዎች እና የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ሐረርን በስፋት እንዲጎበኙና አስደናቂ ውበቷን ለዓለም እንዲያስተዋውቁ ሰፊ ዕድል ፈጥሯል።
የመደመር ትውልድ የትናንትን ታሪክ ከዛሬ ጋር በማስተሳሰር፣ ከትናንት ወረቶቻችን መልካሙን ወስዶ በማላቅ፣ የዛሬውን ጥረት አክሎበት ለነገው ትውልድ የሚያኮራ ቅርስ እያስተላለፈ ይገኛል።
በአዲስ መልክና ቀለም የተዋበው ጀጎል የሀረርን ቀደምት ስልጣኔ እየመሰከረ የሀገርንም ገፅታ እየገነባ ይገኛል። | 131 |
| 20 | 没有文字... | 148 |
