ch
Feedback
ጦር ሜዳ

ጦር ሜዳ

前往频道在 Telegram

ምክንያቱም ተጋድሎአችን ከሥጋና ከደም ጋር ሳይሆን -ከዚህ ከጨለማ ዓለም ገዦች፣ -ከሥልጣናትና ከኀይላት -እንዲሁም በሰማያዊ ስፍራ ካሉ ከርኩሳን መናፍስት ሰራዊት ጋር ነው። ኤፌ 6:12 *ጦር ሜዳ ውስጥ መሆኑን ያላወቀ ሰው ለውግያ የተዘጋጀ አይደለም፡፡ ሁሌ የተማረከ እና የተሸነፈ ነው፡፡ ሰለዚህ "የእግዚአብሔርን ሙሉ የጦር ዕቃ ልበሱ ኤፈ 6:13.... ... አስተያየት ካላችሁ @endyab

显示更多
1 142
订阅者
-124 小时
无数据7
+530
帖子存档
ማራናታ-በረከት ተስፋዬ ************ የመምጣትህ ነገር የመጨረሻው የነገር ትንቢት እየሆነ ነው ናፍቆቱ አስባለኝ አሜን ማራናታ ላይህ ጓጉቻለሁ ኢየሱስ የኔ ጌታ ጌታ ኢየሱስ አትመጣም ወይ የደማልኝን ጎንህን ልይ አንተን ለማየት ዓይኖቼ ሻቱ ቶሎ ናልኝ ኢየሱስ የናዝሬቱ ካንተ ጋር ልዋል ካንተ ጋር ልደር እንደ ዩሐንስ በደረትህ ሥር ደስታዬ የምለው ትልቁ እርካታዬ አንተ ያለህበት ስኖር ነው ጌታዬ በሌለህበት ከማገኝ ድሎት ምድረ በዳ ላይ ካንተ ጋር ልሰንብት አንተን የማየት ናፍቆት ገባብኝ እንደ ጓጓሁኝ መች እቀራለሁኝ ከአመፃ ብዛት ፍቅር ቀዘቀዘ ሰው ወንድሙን ገሎ መቼ ተወቀሰ አመፀኞች በዙ ክፋቱ ጨምሮ ተላልፈው ተሰጡ ለማይረባ አዕምሮ የድሆች ዳኛ የሁሉ አለቃ ናና ከልክለው ለቅሶአችን ይብቃ የእናቶች እንባ ይላል ዋይ ዋይ ሩህሩህ ጌታ አትመጣም ወይ ቤተ ክርስቲያን ተነሺ እና አብሪ ፍቅርን ለጣሉ እንዳትዘምሪ የገሃነም ደጅ ለካ ጥላቻ ነው ማይቋቋምሽ ሰይፍሽ ፍቅር ሲሆን ነው ጦር መሳርያውን ፍቅር ያደረገ ጠላቱን ረቶ ወንድም አደረገ የሰው ጠባብ አፍ የሚጎርስ እህል ክፉ አንደበት አክሏል ሲዖል አትመጣም ወይ ማራናታ አናርፍም ወይ ማራናታ (፪x) ና ና ና ና ማራናታ (፬x) ሐሳዊ መምህራን ነብያቶች በዙ ተናገረኝ ባዮች ለገንዘብ የተገዙ ለታመመው ምስኪን እንግዳ ማረፊያ በሽታው ሳያንሰው በፀሎት ሰበብ ዝርፊያ ደምህ ተረግጦ ገንዘብ ገነነ አንተን ያወቀ ሰው ክፉ ሆነ ነዋይ ሚያፈቅር ትውልድ ተነሳ ያረክለትን ምህረት የረሳ ፈውሱ ለታይታ ለንግድ ቀረበ በአዳኙ ስም ገንዘብ ተሰበሰበ ገበያው ደርቶ በወንጌል ሰበብ ስንቱን ታዘብነው አወይ ጉድ አጀብ በሰጠው ፀጋ የሆነ ነጋዴ በፍርድ ቀን የሚል ነው ወይኔ ጉዴ መምጣቱ አይቀርም የእረኞች አለቃ ስለ በጎቹ የሚራራ ጠንቃቃ አትመጣም ወይ ማራናታ አናርፍም ወይ ማራናታ (፪x) ና ና ና ና ማራናታ (፬x) ወደ ዓለም ሂድ ወንጌልን ስበኩ ነበር የተባልነው መስክሩ ታደጉ ሰው ግን ካስማ ሰርቶ ወንበሯን ወደደ መምህርና ጌታ መባልን ለመደ ወንጌል እንስራ አንቱታው ቀርቶ ይሸለም የለ ወይ የሰራ ተግቶ ከታበይንበት ዙፋናችን እስኪ እንውረድ ለጌታችን አላወጣንም አጋንንቶችን አልፈወስንም ወይ በሽተኞችን ጌታ በስምህ ብዙ አድርገን አላውቃችሁም ስለምን አልከን ከሚሉት ወገን እንዳይሆን ሕይወቴ መብራቴን ላብራ ሳይጎድል ዘይቴ እስክትመጣልኝ ወይ እስክትወስደኝ እየጠበኩክ እፀናለሁኝ። ና ና ና ና ማራናታ (፬x)

5_Bereket_Tesfaye_ማራናታ_Maranata_በረከት_ተስፋዬ.mp36.34 MB

photo content
+1

photo content
+2

📖 መጽሐፍ ቅዱሳዊ ድነት በ3ት መንገድ ተገልጿል ➊ እንዳለፈ ሁኔታ፡- አንድ ሰው ገና በኢየሱስ ስያምን ድኗል (ቲቆ 3:5) ➋ እንደ አሁን ሁኔታ፡- ቀጣይነት ያለው የቅድስና ሕይወት (1ጰጥ 1:9, ሮሜ 6:22, ፍል 2:12, ዕብ 3:14) ➌ የወደፍት ጊዜ፡- ክርስቶስ ዳግም ሲመጣ ድነታችን ወይም ቅድስናችን ክብር በመቀዳጀት፣ ፍጹም በመሆን የሚፈጸምበት ነው (1ጴጥ 1:5, ሮሜ 8:23, ሮሜ 13:11) ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ሰለዚህ ከዘላለም ሕይወት ተሰፋ እንዳትቀሩ (እንዳትጎድሉ) ዕለት ዕለት በቅድስና በመመላለስ፣ ለክርስቶስ ቃል በመታዘዝ እና ክርስቶስን በመምሰል የጀመራችሁትን ድነት ወደ ፍፃሜ አድርሱት፡፡ የትጥቅ ልብስ ለብሳችሁ፣ ወደ ሩጫ ሜዳ ገብታችሁ፣ ሩጫችሁንም ጀምራችሁ፣ መኃል ላይ ከፍፃሜ ሳታደርሱት ሜዳውን ጥላችሁ እንዳትወጡ ተጠንቀቁ፡፡ ወታችሁ እንደሆነም መንገዳችሁን ፈትሹ፡፡ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ "...በሶስት መንገድ ከተገለጸው ድነት አንዱን ነጥለህ መዳን አትችልም፡፡ በማመን ከደንክ ዕለት ዕለት በቅድስና በመኖር ትድናለህ፡፡ ከልሆነ ከድነት ወድቀሀል ማለት ነው፡፡ ዕለት ዕለት በቅድስና በመኖር እየዳንክ ከሆነ ወደፍት ለምገለጠው ለፍጹም ድነት በጽናት እየሮጥክ ነው ማለት ነው፡፡ ሩጫውን የምትጨርሰው ከፍጻሜው ስትደርስ ነው፡፡ ድነትህ ፍጹም ምሆነው ከፍጻሜው ስትደርስ ነው፡፡" ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✦ ✅ በማመን #ትጀምራለህ ✅ በቅድስና ሕይወት #ታስቀጥላለህ ✅ የሩጫው ጀማር እና ፈጻም ከሆነው ጋር ስትገናኝ #ትፈጽማለህ፡፡

ሮሜ 3:19... 19 አፍም ሁሉ ይዘጋ ዘንድ ዓለምም ሁሉ ከእግዚአብሔር ፍርድ በታች ይሆን ዘንድ ሕግ የሚናገረው ሁሉ #ከሕግ በታች ላሉት እንዲናገር እናውቃለን፤ ******** 20 ይህም #የሕግን_ሥራ_በመሥራት ሥጋ የለበሰ ሁሉ በእርሱ ፊት #ስለማይጸድቅ ነው፤ ኃጢአት_በሕግ ይታወቃልና። 21 አሁን ግን #በሕግና_በነቢያት የተመሰከረለት የእግዚአብሔር #ጽድቅ ያለ ሕግ ተገልጦአል፥ 22 እርሱም፥ #ለሚያምኑ_ሁሉ የሆነ፥ #በኢየሱስ_ክርስቶስ_በማመን የሚገኘው የእግዚአብሔር #ጽድቅ ነው፤ ልዩነት የለምና፤ ******* 23 ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል፤ 24 በኢየሱስ ክርስቶስም በሆነው ቤዛነት በኩል #እንዲያው #በጸጋው #ይጸድቃሉ። 25 እርሱንም እግዚአብሔር በእምነት የሚገኝ በደሙም የሆነ ማስተስሪያ አድርጎ አቆመው፤ ይህም በፊት የተደረገውን ኃጢአት በእግዚአብሔር ችሎታ ስለ መተው ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው፥ ********* 26 ራሱም #ጻድቅ እንዲሆን በኢየሱስም የሚያምነውን እንዲያጸድቅ አሁን በዚህ ዘመን #ጽድቁን ያሳይ ዘንድ ነው። 27 ትምክህት እንግዲህ ወዴት ነው? እርሱ ቀርቶአል። በየትኛው ሕግ ነው? በሥራ ሕግ ነውን? አይደለም፥ #በእምነት_ሕግ ነው እንጂ። 28 ሰው ያለ ሕግ ሥራ #በእምነት #እንዲጸድቅ እንቆጥራለንና። 29-30 ወይስ እግዚአብሔር የአይሁድ ብቻ አምላክ ነውን? የአሕዛብስ ደግሞ አምላክ አይደለምን? አዎን፥ የተገረዘን ስለ እምነት ያልተገረዘንም በእምነት የሚያጸድቅ አምላክ አንድ ስለ ሆነ የአሕዛብ ደግሞ አምላክ ነው። 31 እንግዲህ ሕግን በእምነት እንሽራለንን? አይደለም፤ ሕግን እናጸናለን እንጂ። ********* ሮሜ 4:1-25 1 እንግዲህ በሥጋ አባታችን የሆነ አብርሃም ምን አገኘ እንላለን? 2 አብርሃም #በሥራ #ጸድቆ ቢሆን የሚመካበት አለውና፥ ነገር ግን #በእግዚአብሔር ዘንድ አይደለም። 3 መጽሐፍስ ምን አለ? አብርሃምም እግዚአብሔርን #አመነ #ጽድቅም ሆኖ ተቈጠረለት። 4 ለሚሠራ ደመወዝ እንደ ዕዳ ነው እንጂ እንደ #ጸጋ አይቈጠርለትም፤ 5 ነገር ግን ለማይሠራ፥ ኃጢአተኛውንም #በሚያደድቅ ለሚያምን ሰው #እምነቱ #ጽድቅ ሆኖ ይቆጠርለታል። 6 እንደዚህ ዳዊት ደግሞ እግዚአብሔር ያለ ሥራ ጽድቅን ስለሚቆጥርለት ስለ ሰው ብፅዕና ይናገራል እንዲህ ሲል፦ 7 “ዓመፃቸው የተሰረየላቸው ኃጢአታቸውም የተከደነላቸው ብፁዓን ናቸው፤ 8 ጌታ ኃጢአቱን የማይቆጥርበት ሰው ብፁዕ ነው።” 9 እንግዲህ ይህ ብፅዕና ስለ መገረዝ ተነገረ? ወይስ ደግሞ ስለ አለመገረዝ? እምነቱ ለአብርሃም ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት እንላለንና። 10 እንዴት ተቆጠረለት? ተገርዞ ሳለ ነውን? ወይስ ሳይገረዝ? ተገርዞስ አይደለም፥ ሳይገረዝ ነበር እንጂ። 11 ሳይገረዝም በነበረው እምነት ያገኘው የጽድቅ ማኅተም የሆነ የመገረዝን ምልክት ተቀበለ፤ ይህም እነርሱ ደግሞ ጻድቃን ሆነው ይቆጠሩ ዘንድ ሳይገረዙ ለሚያምኑ ሁሉ አባት እንዲሆን ነው፥ 12 ለተገረዙትም አባት እንዲሆን ነው፤ ይኸውም ለተገረዙት ብቻ አይደለም ነገር ግን አባታችን አብርሃም ሳይገረዝ የነበረውን የእምነቱን ፍለጋ ደግሞ ለሚከተሉ ነው። 13 የዓለምም ወራሽ እንዲሆን ለአብርሃምና ለዘሩ የተሰጠው የተስፋ ቃል በእምነት ጽድቅ ነው እንጂ በሕግ አይደለም። 14 ከሕግ የሆኑትስ ወራሾች ከሆኑ እምነት ከንቱ ሆኖአል የተስፋውም ቃል ተሽሮአል፤ 15 ሕጉ መቅሠፍትን ያደርጋልና፤ ነገር ግን ሕግ በሌለበት መተላለፍ የለም። 16-17 ስለዚህ ከሕግ ብቻ ሳይሆን ከአብርሃም እምነት ደግሞ ለሆነ ለዘሩ ሁሉ የተስፋው ቃል እንዲጸና እንደ ጸጋ ይሆን ዘንድ በእምነት ነው፤ እርሱም፦ “ለብዙ አሕዛብ አባት አደረግሁህ፡” ተብሎ እንደ ተጻፈ፥ ለሙታን ሕይወት በሚሰጥ የሌለውንም እንዳለ አድርጎ በሚጠራ ባመነበት በአምላክ ፊት የሁላችን አባት ነው። 18 ዘርህ እንዲሁ ሊሆን ነው እንደ ተባለ፥ ተስፋ ባልሆነው ጊዜ የብዙ አሕዛብ አባት እንዲሆን ተስፋ ይዞ አመነ። 19 የመቶ ዓመትም ሽማግሌ ስለ ሆነ እንደ ምውት የሆነውን የራሱን ሥጋና የሳራ ማኅፀን ምውት መሆኑን በእምነቱ ሳይደክም ተመለከተ፤ 20-21 ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም። 22 ስለዚህ ደግሞ ጽድቅ ሆኖ ተቆጠረለት። 23 ነገር ግን፦ “ተቈጠረለት፡” የሚለው ቃል ስለ እርሱ ብቻ የተጻፈ አይደለም፥ ስለ እኛም ነው እንጂ፤ 24-25 ስለ በደላችን አልፎ የተሰጠውን እኛን ስለ ማጽደቅም የተነሣውን ጌታንችንን ኢየሱስን ከሙታን ባስነሣው ለምናምን ለእኛ ይቈጠርልን ዘንድ አለው።

ምክንያቱም በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን የሚባሉት ለሕጉ #የሚታዘዙ እንጂ፣ ሕጉን #የሚሰሙ አይደሉም። ሮሜ 2:13

ኃጢአት ወደ ጥፋት፤ ክርስቶስ ወደ ሕይወት ***** ኃጢአት ጨካኝና ጨቋኝ የባሪያ ጌታ ነው፤ ክርስቶስ አፍቃሪና መሐሪ ነው የኃጢአት ቀንበር ከባድና አስጸያፊ ነው፤ የክርስቶስ ቀንበር ግን “ልዝብ” ነው፣ ሸክሙም ቀላል ነው። (ማቴዎስ 11፥30) ኃጢአት ባሪያዎቹን በጨለማና በሞት አጥምዶ ይይዛቸዋል፤ ክርስቶስ ግን በእርሱ ላሉት ሁሉ በብርሃኑ ሕያዋን አደረጋቸው። (ቆላስይስ 2፥13) ኃጢአት ወደ ጥፋትና ስህተት ይመራል፤ ክርስቶስ ግን “መንገድና እውነት ሕይወትም ነው።” (ዮሐንስ 14፥6) የኃጢአት ባርነት ጥላቻ፣ ስብራት፣ ፍርሃትና ውርደት የተሞላ ሲሆን፣ የክርስቶስ ባርነት ግን በቸርነት፣ በክብር፣ በሐሴት፣ በእውነትና በቅንነት የተሞላ ነው። ክርስቶስ ኃጢአትንና ሰይጣንን በመስቀል ላይ ድል ነሥቷል። በእርሱ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔርን ቁጣ ሙሉ ቅጣት ተቀብሏል። የእርሱ ሞት ከኃጢአት፣ ከኩነኔ እና ከፍርሃት ነፃ አውጥቶናል። ከኃጢአት ባርነት ነፃ ወጥተናል። ይህም ማለት ለመታዘዝ፣ በጽድቅ ለመኖር እና ቅድስናን ለመከተል ነፃ ወጥተናል ማለት ነው። አሁን የክርስቶስ ባሪያዎች ነን። በጣም አስደማሚውና አስደናቂው ነገር ደግሞ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ መሆን እውነተኛ ነፃነት መሆኑ ነው። — John MacArthur 📖 Slave ✍️ @Gospel_of_God

ሰው ከንቱ – ታምራት ኃይል ******************* እንገናኝ ነገ እንገናኝ ደህና ዛሬን ለማደሩ መች አወቀውና ሰው ከንቱ (፪x) መንገዱን ሲያረዝም እቅዱን ሲያሰፋ ዘንግቶት ይሆናል ታይቶ እንደሚጠፋ ሰው ከንቱ (፪x) አዝ:- ሰው ከንቱ (፮x) ጌታ ብቻ ብርቱ (፪x) ጀግና ወጥቶ ሲቀር ጐበዙ ሲቀጠፍ ነገን እያሰቡ ከዛሬ አለማለፍ ሰው ከንቱ (፪x) ብዪ ጠጪ እያለ ነፍሱን ሲያዝናና ሞት እንደ ደራሽ ወንዝ ድንገት ይመጣና ሰው ከንቱ (፪x) አዝ:- ሰው ከንቱ (፮x) ጌታ ብቻ ብርቱ (፪x) ይህ ለእኔ ያ ለእኔ እዚም እዚያም እኔ ካለው ካገደመው ሲቅበዘበዝ ዓይኔ ሰው ከንቱ (፪x) የነገሌ ዘር ነኝ ሃብቴም እንዳፈር ማንና ምን ይሆን አብሮኝ ሚቀበር ሰው ከንቱ (፪x) አዝ:- ሰው ከንቱ (፮x) ጌታ ብቻ ብርቱ (፪x) በውበት መመካት ዕውቀት አለኝ ማለት ህልም ሆኖ ሊቀር ከአፈር የገቡ እለት ሰው ከንቱ (፪x) አስተዋይ ከዛሬ የነገን ይመርጣል እግዚአብሔርን ማወቅ ከሁሉም ይበልጣል ሰው ከንቱ (፪x) አዝ:- ሰው ከንቱ (፮x) ጌታ ብቻ ብርቱ (፪x)

ሰለውለታህ-ሙሉቀን መለሰ ******************* ስለምሕረትህ ስለጥበቃህ ስለውለታህ ጌታ ሆይ ምንስ ልክፈልህ ከበርት ወይፈኑን ከአዝርትም ምርጡን ከሐብት ከበረክት ከአስራት ምጽዋቱን ነፍሰእንም ጨምረእ ሚዛን ላይ ብሰፍረው ጌታ ለውለታህ እጅግ ያነሰ ነው በተለምዶ ቃላት ተመስገን ልበልህ ሌላማ ምን አለኝ ላንተ የምሰጥህ አምላክ ሆይ ውለታህ እጅግ የበዛ ነው ቤት አልሰራልህም ዙፋንህ ሰማይ ነው ብር ወርቁ ያንተ ነው ምን እሰጥሃለሁ ብቻ በአንደበቴ ተመስገን እላለሁ እንደዳዊት ልዝለል ልዘምር ልጨፍር አዳኝነትህን ገድልህን ልናገር ጌታ ለውለታህ የለም የምከፍልህ የኔ ታሪክ ድርሻ አንተን ማሞገስ ነው ሐጥያት መስራት ትቼ ወዳንተ ብመለስ በአለም ዙሪያ ሮጬ ወንጌልን ባዳርስ ሰማይና ምድርን እንደ ንስር ባስስ ጌታ ውለታህን አልችልም ልመልስ

Repost from N/a
ጸልዩለት🥺🥺🥺

sticker.webp0.39 KB

"ተመልከቱ የገረጣ ደረቱ፣የቀላ ጎኑን፣በጥም የደረቀ አንጀቱን፣በሞት የማቀቀ ውብ አይኖቹን፣ክንዶቹ ተወጥረዋል፣የከበረ ፊቱ በደም ተጨማልቋል፣ባቶቹ ተዘርግተዋል፣የተቸነከረው እግሮቹ በከበረው ደሙ እርሰዋል።ተመልከቱ ክቡር አባቱ የውድ ልጁን ሰውነት ሲያይ ደቋል፣ቆስሏል፣ተቦጫጭቋል። አቤቱ፥ እንዲሁ ሰዎችን ወዶ ልጁን መስጠቱን፣ ያለምክንያት አለምን አፍቅሮ ውዱን መሰዋቱን፣ አይቼ አላቅም ያንተን ቅዱስ ፍቅርህን፣ በመስቀል ደም ዋጋ እኔን መግዛትህን። እዩት ውድ መድሀኒቴን በኔ ቦታ የሆነውን፣ በኔ ድርሻ የከፈለውን። አቤት ያንን ፅዋ፣ አቤት ያንን ቁጣ፣ ከእኔ ተቀበሎ ወስዶት የጠጣ ለእኔ አይደለም ወይ? ለጠላቱ ብሎም ለገዳዩ። ይገርመኛል በእኔ ወንጀል አንተ መገረፍህ፣በኔ ትዕቢት አንተ መዋረድህ፣በኔ ትምክህት ራስህን ባዶ ማድረግህ፣በኔ አመፅ እስከሞት መታዘዝህ፣በኔ ሆዳምነት መራብና መጠማትህ።እኔ በበላሁት ፍሬ አንተ ታመምክ፣እኔ በደስታ ስንደባለል አንተ በጦር ተወጋክ፣በእኔ አፍ ውስጥ ያለው ማር በአንተ ሆድ ውስጥ ወደ ሀሞት ተቀየረ።"       አውግስጢኖስ        ፊልጵስዩስ 2:7-8 “... ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥ 8 በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ። ”

"ተመልከቱ የገረጣ ደረቱ፣የቀላ ጎኑን፣በጥም የደረቀ አንጀቱን፣በሞት የማቀቀ ውብ አይኖቹን፣ክንዶቹ ተወጥረዋል፣የከበረ ፊቱ በደም ተጨማልቋል፣ባቶቹ ተዘርግተዋል፣የተቸነከረው እግሮቹ በከበረው ደሙ እርሰዋል።ተመልከቱ ክቡር አባቱ የውድ ልጁን ሰውነት ሲያይ ደቋል፣ቆስሏል፣ተቦጫጭቋል። አቤቱ፥ እንዲሁ ሰዎችን ወዶ ልጁን መስጠቱን፣ ያለምክንያት አለምን አፍቅሮ ውዱን መሰዋቱን፣ አይቼ አላቅም ያንተን ቅዱስ ፍቅርህን፣ በመስቀል ደም ዋጋ እኔን መግዛትህን። እዩት ውድ መድሀኒቴን በኔ ቦታ የሆነውን፣ በኔ ድርሻ የከፈለውን። አቤት ያንን ፅዋ፣ አቤት ያንን ቁጣ፣ ከእኔ ተቀበሎ ወስዶት የጠጣ ለእኔ አይደለም ወይ? ለጠላቱ ብሎም ለገዳዩ። ይገርመኛል በእኔ ወንጀል አንተ መገረፍህ፣በኔ ትዕቢት አንተ መዋረድህ፣በኔ ትምክህት ራስህን ባዶ ማድረግህ፣በኔ አመፅ እስከሞት መታዘዝህ፣በኔ ሆዳምነት መራብና መጠማትህ።እኔ በበላሁት ፍሬ አንተ ታመምክ፣እኔ በደስታ ስንደባለል አንተ በጦር ተወጋክ፣በእኔ አፍ ውስጥ ያለው ማር በአንተ ሆድ ውስጥ ወደ ሀሞት ተቀየረ።"       አውግስጢኖስ ፊልጵስዩስ 2:7-8 “... ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥ 8 በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ። ”

Repost from SoulEchoes🪶
ስለ ኪንሱጊ እንደምታውቁ አስባለሁኝ ግን እንዲሁ አጭር ማብራሪያ ይኧው፥ (Kintsugi) ወይም "በወርቅ ማያያዝ" የሚባለው ጥበብ፣ የተሰባበሩ የሸክላ ዕቃዎችን በወርቅ፣ በብር ወይም በፕላቲኒየም ዱ
ስለ ኪንሱጊ እንደምታውቁ አስባለሁኝ ግን እንዲሁ አጭር ማብራሪያ ይኧው፥
(Kintsugi) ወይም "በወርቅ ማያያዝ" የሚባለው ጥበብ፣ የተሰባበሩ የሸክላ ዕቃዎችን በወርቅ፣ በብር ወይም በፕላቲኒየም ዱቄት ከተቀላቀለ የማጣበቂያ ቀለም (lacquer) ጋር በማገናኘት የመጠገን ጥንታዊ የጃፓን ጥበብ ነው። ​ይህ ጥበብ ስብራትን ወይም ጥፋትን ከመደበቅ ይልቅ፣ እንደ ዕቃው ታሪክ አካል አድርጎ በክብር ጎልቶ እንዲታይ ያደርገዋል። ኪንሱጊ ፍልስፍናዊ በሆነ መልኩ "ዋቢ-ሳቢ" (Wabi-sabi) ከሚባለው የጃፓን አስተሳሰብ ጋር የተያያዘ ሲሆን፣ ይህም በጎደሎ ወይም ፍጹም ባልሆነ ነገር ውስጥ ውበትን መፈለግ ማለት ነው።
ብቻ ትላንት ጊቢ ስለ አውግስጢኖስ lecture ነበረን እና ይህን የ ኪንሱጊ ሀሳብ ተነስቶም ነበር ምናምን፥ በብዙ ጉዳይ ተሰብረን ሊሆን ይችላል በብዙ ወድቀን ተንኮታኩተን ደቀንም ሊሆን ይችላል እግዚአብሔር ግን ሊጠገን የማይችል ስብራትን አያውቅም! ይሄ ከኔ በላይ ነው የሚለው ነገር የለም! በነጠፈና በደረቀ ህይወት የለውም በተባለበት ስፍራ ላይ ነፍስን መዝራት ህይወትን ማብቀል ይችላል። አይዞን እግዚአብሔር ይራራልናል ይጠግነናል እንደገና ይሰራናል✨

sticker.webp0.28 KB

Repost from N/a
💥 ከማክስ ሉካዶ መፅሀፍ አንድ ሃሳብ ወስጄ ላካፍላችሁ፡ 👉 እስቲ ዛሬ ኢየሱስ እኔን ቢሆን ብላችሁ አስቡ‼️ ለ24 ሰዐታት ኢየሱስ እኔን ሆነ ወይም የእኔ ልብ በእርሱ ልብ ተተካ ብላችሁ አስቡ። አስተውሉ፡ በህይወታችሁ ሌላ ምንም አልተቀየረም፡ የእናንተ አለቃ የእርሱ አለቃ ሆኗል፣ የእናንተ ቤተሰብ የእርሱ ቤተሰብ ሆኗል፣ የሚያማችሁ ከሆነም የተቀየረ ነገር የለም፣ የዛሬ እቅዳችሁ እንዳለ ነው፣ ቀጠሮዎቻችሁ አልተቀየሩም። ብቻ ምንም ከህይወታችሁ አልተቀየረም። የተቀየረው አንድ ነገር ብቻ ነው.. የእናንተ ልብ ወጥቶ የኢየሱስ ልብ ገብቶላችኋል። ስለዚህ የእርሱን ሃሳብ ብቻ እየኖራችሁ ነው። 👉 በዚህ ቀን በህይወታችሁ ምን አይነት ለውጥ የሚመጣ ይመስላችኋል? ኢየሱስ ከጓደኞቻችሁ፣ ከቤተሰቦቻችሁ፣ ከስራ አጋኖቻችሁ ጋር የተለየ አይነት ግንኙነት ይመሠርት ይሆን? ይቅር ያላላችኋቸውን ይቅር ይል ይሆን? እነርሱስ ለውጥ ያስውሉባችሁ ይሆን? ከዛሬ እቅዶቻችሁ የትኞቹን ይተው ይሆን? ከያዛችኋቸው ቀጠሮዎችስ የቱን ይሰርዝ ይሆን? ወይስ መያዝ የነበረባችሁ ያልያዛችሁትን እቅድ ይጨምር ይሆን? መንገዳችሁ እንዴት ይሆን ይሆን? * እስቲ ቆም ብላችሁ በህይወታችሁ በእናንተ ቦታ ኢየሱስ ቢሆን ኖሮ የማይኖራቸውን ሰዐታት፣ የማያስባቸውን ሃሳቦች፣ የማያደርጋቸውን ድርጊቶች፣ የማይናገራቸውን ንግግሮች፣ የማይሰማቸውን ወሬዎች አስቡ። 👉ኢየሱስን መምሰል እኮ ይሄ ነው! ኢየሱስ የማይኖራቸውን ህይወቶች ከውስጣችን ማስወገድ። ህይወታችንን ኢየሱስ እንደሚኖረው አድርጎ በጥንቃቄ መኖር። ❤ 📖📖 1 ቆሮንቶስ 2:16 📖📖❤ “... እኛ ግን የክርስቶስ ልብ አለን።” ✍️https://t.me/mere_protestantism

♥#ሕግ_እና_ፀጋ♥  ♥እንግዲህ እንዲህ ያለ ተስፋ ካለን #እጅግ_ገልጠን_እንናገራለን፥ 2 ቆሮንቶስ 3 ፡12፤♥ ✍️በብሉይ/በአሮጌው ኪዳን እና በአዲስ ኪዳን ✍️በሙሴ እና በክርስቶስ ✍️በሕግ እና በፀጋ ✍️በእንስሶች ደም እና ክቡር በሆነው በኢየሱስ ደም መካከል ያለውን ልዩነት ያልተረዳ እና ጠንቅቆ የማያውቅ ሰው ብዙ እውነቶችን ያበላሻል።  📌2 ጢሞቴዎስ 2 (2 Timothy) 15፤ የእውነትን ቃል በቅንነት(በትክክል)የሚናገር የማያሳፍርም ሠራተኛ ሆነህ፥ የተፈተነውን ራስህን ለእግዚአብሔር ልታቀርብ ትጋ። ✍️ሕግ ከሰወች ፅድቅን ይጠይቃል ❤️ፀጋ የተገለጠ የእግዚአብሔር ፅድቅ።      ሮሜ 10፡3- ✍️ሕግ ትእዛዝ ይሰጣል ነገር ግን ለሃጢያተኛው ሰው አቅም አይሰጥም። ❤️ፀጋ ሲሰበክ ግን ቅዱሳን አቅም ያገኛሉ። ቲቶ 2:11-14 ✍️ሕግ አድርግ እና አታድርግ ሲል ❤️ፀጋ ግን ተደርጎልሀል በማለት የምስራች ይናገራል። ✍️ሕግ ራስህን እንድታይ ሲያደርግህ  ❤️ፀጋ ግን የተሰቀለውን ክርስቶስን ያሳያል። ገላ 3፡1- ,4፡19 ✍️ሕግ ባሪያይቱ አጋር ልጆችንም ለባርነት የሚወልድ ❤️ፀጋ ነፃይቱ ሳራ የሚወረሱ ጨዋ ልጆችን የምትወልድ። ገላ 4፡21-31 ✍️ሕግ ወንጌልን ለሚቃወሙ ሰወች የተሰራ  ❤️ፀጋ በኢየሱስ ክርስቶስ ለሚያምኑት የሆነ። 1ጢሞ1፡8-11, ሮሜ 3፡24 📌 2 ቆሮንቶስ 3 (2 Corinthians) 4፤ በክርስቶስም በኩል ወደ እግዚአብሔር እንዲህ ያለ እምነት አለን። 5፤ ብቃታችን ከእግዚአብሔር ነው እንጂ፥ በገዛ እጃችን እንደሚሆን አንዳችን እንኳ ልናስብ ራሳችን የበቃን አይደለንም፤ 6፤ እርሱም ደግሞ በመንፈስ እንጂ በፊደል ለማይሆን ለአዲስ ኪዳን አገልጋዮች እንሆን ዘንድ አበቃን፤ ፊደል ይገድላልና መንፈስ ግን ሕይወትን ይሰጣል። ✍️For_Christ_is_the_end_of #the_law for righteousness to every one that believeth. Romans 10፡4 (KJV)

Story

Repost from N/a
photo content