ch
Feedback
ጦር ሜዳ

ጦር ሜዳ

前往频道在 Telegram

ምክንያቱም ተጋድሎአችን ከሥጋና ከደም ጋር ሳይሆን -ከዚህ ከጨለማ ዓለም ገዦች፣ -ከሥልጣናትና ከኀይላት -እንዲሁም በሰማያዊ ስፍራ ካሉ ከርኩሳን መናፍስት ሰራዊት ጋር ነው። ኤፌ 6:12 *ጦር ሜዳ ውስጥ መሆኑን ያላወቀ ሰው ለውግያ የተዘጋጀ አይደለም፡፡ ሁሌ የተማረከ እና የተሸነፈ ነው፡፡ ሰለዚህ "የእግዚአብሔርን ሙሉ የጦር ዕቃ ልበሱ ኤፈ 6:13.... ... አስተያየት ካላችሁ @endyab

显示更多
1 194
订阅者
-224 小时
+47
-430
帖子存档
የውይይት ሀሳብ ሐዋርያ ሥራ ምዕራፍ 15 መሠረት ጳውሎስ በወንጌል ጉዞው የገጠመው ነገር ምንድነው? የኢየሩሳሌም ጉባኤ ስለምን ነው? ይሄ የገጠመው challenge “በሕግ ሥራ አይደለም፣ በእምነት በጸጋ ነው” ለሚለው አስተምህሮ መነሻ ሆኖት ይሁን? በዚህ አሁን ባለንበት ዘመን በወንጌላውያን አማኞች ማህበር/Protestant ውስጥ ልክ በጳውሎስ ዘመን እንደነበረ “በሕግ ሥራ አይደለም” እያልን ልንሟገታቸው የምንችላቸው፣ በሐዋርያ ሥራ ምዕራፍ 15 እንደነበረ የአይሁዳውያን ዓይነት አስተምህሮ አለ?

ለምንድነው ጴጥሮስ ስለ ጳውሎስ ወንጌል የሚከተለውን የጻፈው? “የጌታችን ትዕግሥት እናንተ እንድትድኑ እንደሆነ አስቡ፤ እንዲሁም ወንድማችን ጳውሎስ እንደ ተሰጠው ጥበብ መጠን ጻፈላችሁ፤ እርሱ ስለ እነዚህ ነገሮች በመልእክቶቹ ሁሉ ጽፎአል፤ #በመልእክቶቹም_ውስጥ_በቀላሉ_ለመረዳት_የሚያዳግቱ_ነገሮች_አሉ። ዕውቀት የጐደላቸውና ጽናት የሌላቸው ሰዎች ሌሎችን ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚያጣምሙ፣ እነዚህንም ደግሞ ለገዛ ጥፋታቸው ያጣምማሉ።" 2 ጴጥሮስ 3:15-16

የወይይት ሀሳብ ከሥር ጳውሎስ የጠቀሳቸው ሕግ ናቸው ወይስ አይደሉም? እነዚህ ሕግ አይደሉም ካልን ታድያ ሕግ ምንድነው? ሕግ ናቸው ካልን ደግሞ፣ መጽሐፍ ቅዱስ" በሕግ ሥራ አይደለም የሚለው ሕግ ምንድነው?" .....ጳውሎስ ግን በገላትያ or ኤፌሶን ያሉትን አማኞች እነዚህን የሚያደርግ የእግዚአብሔርን መንግሥት አያወርሱም ይላል...እና አይጣረስም? አዲስ ኪዳን ከሥር የተጠቀሱትን እና ተዛማጅ የሆኑ የሥጋ(የዓለም) ፍሬዎችን የምለማመድ እና የምያደርግ ማንኛውም ያላመነም ሆነ #ድኛለው የሚል ሰው የእግ/ርን መንግሥት እንደማይወርስ ይናገራል፡፡ #ዐመፀኞች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 1ቆሮ 6:9-10 #ሴሰኞች፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 1ቆሮ 6:9-10, ዕብ 13:4 #ጣዖት_አምላኪዎች፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 1ቆሮ 6:9-10, ገላ 5:19-21, ኤፌ 5:3-5, ራእይ 21:8 #አመንዝሮች፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 1ቆሮ 6:9-10, ኤፌ 5:3-5, ራእይ 21:8, ዕብ 13:4 #ወንደቃዎች፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 1ቆሮ 6:9-10 #ግብረ_ሰዶማውያን፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 1ቆሮ 6:9-10 #ሌቦች፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 1ቆሮ 6:9-10 #ስግብግቦች፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 1ቆሮ 6:9-10, ኤፌ 5:3-5 #ሰካራሞች፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 1ቆሮ 6:9-10, ገላ 5:19-21 #ተሳዳቢዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 1ቆሮ 6:9-10 #ቀማኞች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። 1ቆሮ 6:9-10 #ዝሙት፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21, ኤፌ 5:3-5 #ርኵሰት፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21, ኤፌ 5:3-5, ራእይ 21:8, ራዕይ 21:27 #መዳራት፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21 #ሟርት፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21 #ጥላቻ፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21 #ጠብ፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21 #ቅናት፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21 #ቊጣ፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21 #ራስ_ወዳድነት፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21 #መለያየት፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21 #አድመኝነት፤ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21 #ምቀኝነት፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21 #ዘፋኝነት፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21 #እነዚህን_የመሰለው_የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21 #የሚያሳፍርና ንግግር የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ኤፌ 5:3-5 #ተራ የሆነ ንግግር፣ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ኤፌ 5:3-5 #ዋዛ_ፈዛዛም ንግግር የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ኤፌ 5:3-5 #ፈሪዎች፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ራእይ 21:8 #የማያምኑ፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ራእይ 21:8 #ነፍሰ_ገዳዮች፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ራእይ 21:8 #አስማተኞች፣ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ራእይ 21:8 #ውሸተኞች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ራእይ 21:8, ራዕይ 21:27 #የእውነትን_ዕውቀት_ከተቀበለ_በኋላሆን_በኀጢአት_ጸንቶ_የምመላለስ፣የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ዕብ 10:26 #ከተፈጥሮ_ሥርዐት_ውጭ_የሆነ_ሩካቤ_ሥጋ የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ይሁዳ 1:7 #እነዚህን_የመሰለው_የምያደረጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። ገላ 5:19-21

ሕግ፣ ጽድቅ እና ድነት — የውይይት ጥያቄዎች ሕግ ምንድነው? ጽድቅ ምንድነው? ድነት ምንድነው? --- መጽሐፍ ቅዱስ ወይም ጳውሎስ “ሕግ”፣ “ጽድቅ” ሲል ምን ለማለት ፈልጎ ነው? ለምን ከጳውሎስ ውጭ ሌሎች ሐዋርያት (ዮሐንስ፣ ያዕቆብ፣ ጴጥሮስ፣ ይሁዳ...) እንደ ጳውሎስ እነዚህን ቃላት ያልተጠቀሙት? --- ጳውሎስ በወንጌል ጉዞው ላይ ምን ችግር ገጥሞት ነው እነዚህን ሊል የቻለው? --- ጳውሎስ በገላትያ ላይ “በሕግ አይደለም፣ በእምነት ነው” እያለ፣ ለምን “የሚከተሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም” ይላል? ገላ 5:21

ጽድቅ /መጽደቅ፦ ጽድቅ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት ማግኘት፤ በእግዚአብሔር ፊት ትክክል መሆን፤ በእግዚአብሔር ፊት ያለ ኰነኔ መሆንን የሚያሳይ ነው። መፅሐፍ ቅዱስ ጽድቅ በክርስቶስ ኢየሱስ #በማመን ብቻ የሚገኝ እንደሆነ በማያሻማ መልኩ ይናገራል። ማንም በክርስቶስ ኢየሱስ ካልሆነ በእግዚአብሔር ፊት ተቀባይነት የሚያገኝበት ሌላ መንገድ የለም። መፅሐፍ ቅዱስ በልጁ የማያምን በፍርድ ስር እንደሚኖር ይናገራል። 🙏ጽድቅ የመዳን የመጀመሪያው step ነው። 🙏ጽድቅ ከእግዚአብሔር ጋር መኖር እንድንችል የመጀመሪያው step ነው። 🙏ጽድቅ ከእግዚአብሔር ጋር ሰላም እንዲኖረን የመጀመሪያው step ነው። 🙏ጽድቅ የእግዚአብሔርን መንፈስ (መንፈስ ቅዱስን) ለመቀበል የመጀመሪያው step ነው። 🙏ጽድቅ የተፈጠርንበትን መልካሙን ስራ እንድንሰራ ሃይል እንድናገኝ የመጀመሪያው step ነው። ✝ስለዚህ እኛ በክርስቶስ ኢየሱስ በማመን ከጸደቅን፣ከእግዚአብሔርም ጋር ሰላም ካለን፣ ከቁጣ ካመለጥን፣ የእግዚአብሔር መንፈስ ከፈሰሰልን፤በመንፈስ ቅዱስ ሆነን መልካሙን ፍሬ እያፈራን #መዳናችንን ልንፈፅም ልንተጋ ይገባናል።

እድል ፋንታዬ እግዚአብሔር-ሶፍያ ሽባባው *********************** እድል ፋንታዬ እግዚአብሔር (፪x) ሰማያትን ጥሶ ህዋውን ሰንጥቆ ከፀሐይ ሰባት እጅ ይልቅ አብረቅርቆ ከማደሪያው መጣልኝ በማለዳ ፈለገኝ በምህረቱ በራልኝ አብረቀረቀለኝ አዝ እድል ፋንታዬ እግዚአብሔር የሌዊ አምላክ እግዚአብሔር እድል ፋንታዬ ምስጋናዬ የዳዊት አምላክ ዝማሬዬ (፪x) ስትመርጥ አትከለከልም አስታዋሽ እንዳንተ አላየሁም ጌታዬ አንተኮ ልዩ ነህ ለኔስ እድል ፋንታዬ ነህ (፪x) (እድል ፋንታዬ እግዚአብሔር) አዝ እድል ፋንታዬ እግዚአብሔር የሳሙኤል አምላክ እግዚአብሔር እድል ፋንታዬ መኖሪያዬ የዳንኤል አምላክ ዝማሬዬ/መመኪያዬ (፪x) እድል ፋንታዬ እግዚአብሔር እድል ፋንታዬ ምስጋናዬ እድል ፋንታዬ መኖሪያዬ እድሌን ከመረጥክ እንድሆን በፊትህ ክብርህንም እንዳይ እንድዘምርልህ አሜን አሜን እያልኩ እንበረከካለሁ ቅዱስ ቅዱስ እያልኩ እሰግድልሃለሁ አዝ እድል ፋንታዬ እግዚአብሔር የሌዊ አምላክ እግዚአብሔር እድል ፋንታዬ ምስጋናዬ የዳዊት አምላክ ዝማሬዬ እድል ፋንታዬ እግዚአብሔር የሳሙኤል አምላክ እግዚአብሔር እድል ፋንታዬ መኖሪያዬ የዳንኤል አምላክ መመኪያዬ (፪x) እድል ፋንታዬ እግዚአብሔር እድል ፋንታዬ ምስጋናዬ እድል ፋንታዬ እግዚአብሔር እድል ፋንታዬ መኖሪያዬ

የአዲስ ኪዳን አማኞች ህግ አልባ አይደለንም፤ ሰው ህግን በመፈጸም አይድንም። ነገር ግን በክርስቶስ አምኖ የዳነ ሰው ህግን በመንፈስ ቅዱስ ሃይል ይፈፅማል። ሮሜ 8:4

Repost from LOGOS
#ቅድስና ወደ ኢየሱስ ያመጣን መንገድ አይደለም፤ #ኢየሱስ ነው ወደ ቅድስና ያመጣን። ••••••••••••••• ቻርልስ ስፐርጀን ••••••••••••••• #ኢየሱስ ትላንት ያገኘንህ የማትወሰድ ፅድቃችን ነህ ፤ #ኢየሱስ ዛሬን ያቆምከን የማትነቃነቅ ዓለታችን ነህ ፤ #ኢየሱስ የማትጨልምብን የሚትመጣ ተስፋችን ነህ ። 🔒ዋሴ አንተ ነህ ለዘላለም አልጠፋም ፤( ዮሐ 10:28) በማይፋቅ ቀለም በደምህ ተፅፏል ስሜ በሕይወት መዝገብ ፤ ማነው የሚደመስሰኝ ! እኔ ነኝ ወይስ ልዩ ፍጥረት ! #ሉራ(ከቶ) ✍️ወንድም አሻግሬ

Repost from LOGOS
ይቅር ለተባለ ኃጢአተኛ ሲዖል የለም። እግዚአብሔር እንደ አባት ያቅፈዋል እንጂ እንደ ፈራጅ አይኮንነውም። ••••••••••••••• ቻርልስ ስፐርጀን ••••••••••••••• ...ስለዚህ በክርስቶስ ኢየሱስ ያሉት አሁን ኵነኔ የለባቸውም፤ (ሮሜ 8:1)                                                       ✍️ወንድም አሻግሬ

በሰው ልብ ብዙ አሳብ አለ፤ የእግዚአብሔር ምክር ግን እርሱ ይጸናል።                                            ምሳሌ 19:21

photo content

አቤቱ በህዝብህ ሞገስ አስበን ******* አቤቱ በህዝብህ ሞገስ አስበን በመድሃኒትህም ጐብኘን ህዝብህ ለአርባ አመታት ሲጓዝ ምድረ በዳ ሞገስ ስለሆንከው ከቶ ሳይጐዳ እያዘነብክለት ከሰማያት መና ስትጠብቅ ስትመራው በእሳት በደመና ሞገስህን አግኝቶ ህዝብህም በርትቶ ድል በድል አድርጓል ጠላቶቹን ረግጦ ህዝብህን ባሰብክበት ሞገስህ አስበን ማምለጥ እንድንችል ከከበበን ነገር አዝ፦ በህዝብህ ሞገስ አስበን (፬x) በህዝብህ ሞገስ አስበን (፬x) ያየ የጋለው ፍቅርህ የቀድሞው ሕይወታችን ዛሬ ቀስሞብናል ቀዝቅዟል ልባችን አንድነት ሲጠፋ መለያየት በዝቶ ስም ብቻ ሆነናል ሕይወታችን ሞቶ ዛሬ ግን ጌታ ሆይ ጐብኘን በ??? ባሰብክበት ምህረት ልክ እንደህዝቦችህ እጆቿን ወደ አንተ ኢትዮጵያም ትዘርጋ ጊዜው አሁን ይሁን ሞገስህ ይብዛና አዝ፦ በህዝብህ ሞገስ አስበን (፬x) በህዝብህ ሞገስ አስበን (፬x) በአንደበት ፍቅር የለበጥ አንድነት ቤትህን አረግነው ተንኮል የሞላበት በአፋችን ሌላ በልባችን ሌላ የያዝነውን እምነት አረግነው ደካማ መግባባት ይኑረን ቃላችን አንድ ይሁን እንደተናገርነው እንዲሁ እንድንኖር ዛሬ ለውጥን ስጠን ጌታ ለሁላችን በሞገስህ አስበን ይቀየር ልባችን አዝ፦ በህዝብህ ሞገስ አስበን (፬x) በህዝብህ ሞገስ አስበን (፬x) @btlfld

ኢየሱስ ካለማ ***** ገዢና ተገዢ መኳንንት ሹማምንት የአገሬው ህዝብ ሁሉ የተሳተፉበት እምቢልታ መሰንቆ በገናና ዋሽንት ሁሉም ተሰለፎ ለአንድ ሰው ትዕቢት አቤት ትዕቢት (፪x) የአንድ ንጉሥ ትዕቢት አገር ሲያሰግድ ህዝቡን ሲያንቀጠቅጥ ሶስት ደፋር ሰዎች ጣዖት ያለመዱ አንሰግድም ሲሉ በዓል አበላሹ ንጉሡም ሲሰማ በትዕቢት ተቆጣ እቶኑን ጨመረው እጥፍ እንዲነድ ሌላ ጉድ ፈላ አንሰግድም ያሉ በትዕቢት በጋለ እቶን ውስጥ ተጣሉ ወድቀው ተቃጥለው አረው ተኮማትረው መች ቀሩ መች ቀሩ ምንም ቢታሰሩ ተፈታ ገመዱ እያለ አዳኙ ጭራሽ ወዲህ ወዲያ ይራመዱ ጀመር የተስማማ እስኪመስል እንዴትስ አይመች እንዴትስ አይድላ ኢየሱስ ካለማ (፪x) ትዕቢቱ ተመታ የንጉሡ ሲበለሻሽ በት ድግሱ ሶስት ሰዎችን ጥሎ አራት ሲሆኑበት ነገር ግራ ሆነበት ንጉሱም እንዲህ አለ አዋጁን ቀየረ እየደነገጠ እነዚያን ብሩካን አውጧቸው ከእሳት እናምልከው በቃ የእነርሱን አምላክ (፪x) ሁሉም ሰው ያምልከው ይስገድለት ፊቱ ያስደንቃልና የማዳን ጉልበቱ እንደፋ ፊቱ እስቲ ጐምበስ (፪x) ይባልለት ይሰገድለት እስቲ ጐምበስ (፪x) ይባልለት ይሰገድለት አያልቅበት (፪x) ማዳኑ አያልቅበት አያልቅበት መታደጉ አያልቅበት አያልቅበት ምህረቱ አያልቅበት እስቲ ጐምበስ (፪x) ይባልለት ይሰገድለት እስቲ ጐምበስ (፪x) ይባልለት ይሰገድለት (፪x) @btlfld

መስቀልህ ስር ***** ተስፋ ቆርጬ ወደኋላዬ አልልም በጥቂቱ ዝዬ አልመለስም ብትገድለኝም ብታድነኝም ብትሰጠኝም ብትነሳኝም እጅህን እጠብቃለሁ ከፊትህ አልሄድም አንተን የለመነህ በፊትህ ጠብቆ ሁሉን እንደምትችል እንደምትሰጥ አውቆ ጊዜውን ብታረዝምም እምነቱን ልትፈትን እርሱን የጠበቀው መች አጣው ባርኮቱን አግኝቷል ከጌታ አጽንቶ እምነቱን እኔም መስቀልህ ስር ሆኜ እጠብቃለሁ ምን እንደምትሰራ እጅህን አያለሁ ጉልበቴን በፊትህ አምበረክካለሁ ቃሌንም በቤትህ ዝም አሰኘዋለሁ አንተ ምትሰራውን በሙሉ አያለሁ አንዲት ከነአናዊት ሴት ወደ ኢየሱስ መጥታ 'የዳዊት ልጅ ጌታ ሆይ ልጄ በእርኩስ መንፈስ ተይዛ ትስቃያለችና እባክህ እራራልኝ' እያለች ጮኸች እርሱ ግን አንድም ቃል ሳይመልስላት ዝም አለ በዚያን ጊዜ ደቀ መዛሙርቱ ወደ እርሱ ቀረብ ብለው 'ይሂች ሴት እየተከተለችን ስለምትጮህ እባክህ አሰናብታት' ሲሉ ለመኑት እርሱም 'እኔ የተላኩት ከእስራኤል ቤት እንደበጐች ለጠፉት ብቻ ነው' ሲል መለሰ። ሴትዬዋ ግን ቀርባ በእግሩ ስር ተንበረከከችና 'ጌታ ሆይ እባክህ እርዳኝ አለችው'። ኢየሱስም 'የልጆችን እንጀራ ወስዶ ለውሾች መጣል የተገባ አይደለም' አለ። እርሷም 'ጌታ ሆይ እርግጥ ነው። ነገር ግን ውሾችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዐድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ' አለችው። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ 'አንቺ ሴት እምነትች ትልቅ ነው። ስለዚህ እንደፍላጐትሽ ይሁንልሽ አላት'። የሴትየዋም ልጅ በዚያን ሰዓት ዳነች። በለእርሱን የጠበቀ ፍሬዋን ይበላል ከጌታው ሚጠብቅ እርሱ ደግሞ ይከብራል እኔም ከአንተ ብቻ እጠብቃለሁኝ የአማረውን ፍሬ ለመብላት ጓጓሁኝ አይቀርም አንድ ቀን ደግሞ እከብራለሁኝ ብትሰጠኝም ብትነሳኝም እጅህን እጠብቃለሁ ከፊትህ አልሄድም ቃሌንም በቤትህ ዝም አሰኘዋለሁ አንተ ምትሰራውን በሙሉ አያለሁ @btlfld

እስቲ ልለምነው ጌታዬን ********* እስቲ ልለምነው ጌታዬን ስለአገሬ ስለህዝቤ የራሴን የግሌን ነገር ትቼ እስቲ ልለምነው ጌታዬን ስለአገሬ ስለምድሬ የራሴን የጸሎት ርዕስ ትቼ ለሹማምንት ለገዢዎች ለአለቆች ፊቱ ልቅረብ ልጸልይ ተግቼ ስለሌሎች ለሹማምንት ለገዢዎች ለአለቆች ፊቱ ልቅረብ ልጸልይ ተግቼ ስለሌሎች (፪x) የአገሬ መፍትሄዋ የእንቆቅልሿ መፍቻዋ ቁልፉ ያለው ሰው ጋር አይደል ታዲያ ማንም አይታለል ስለእልቂቷ ወሬን ትቼ ስንበረከክ ተደፍቼ ይሰማኛል አምነዋለሁ ከዚም በፊት አይቻለሁ ሁሉም ነገር ያበጀዋል ዝብርቅርቁን ያሳምራል አዝ፦ እስቲ ልለምነው ጌታዬን ...... ለሹማምንት .... በችግሯ ከምሳለቅ ይልቅ እኔ ፊቱ ልውደቅ ባለምነው ባልጠይቀው እዳው በእኔ ጫና ላይ ነው መፍትሄ ላይሆን ወሬን ትቼ ልንበረከክ ፊቱን ሽቼ ሰሚ አምላክ እያመንኩኝ ለምን መፍትሄ አጣለሁኝ እትልቅም ለውጥ አመጣለሁ ለምድሬም ፈውስ እሆናለሁ አዝ፦ እስቲ ልለምነው ጌታዬን ...... ለሹማምንት ..... ብለምነው ስለአገሬ ሸክም ቢኖረኝ ለምድሬ ያለባትን ችግር ሁሉ ይዤ ብቀርብ ከመስቀሉ ጌታዬ እኮ ያደምጠኛል እንደሃሳቡ ይመልሳል ሳልታክት ፊቱ እቀርባለሁ ቃሉም ይላል ጸልያለሁ ሸክሟን ሳሳየው የምድሬን ይፈውሳታል አገሬን አዝ፦ እስቲ ልለምነው ጌታዬን .... ለሹማምንት ለገዢዎች ለአለቆች ፊቱ ልቅረብ ልጸልይ ተግቼ ስለሌሎች ለሹማምንት ለገዢዎች ለአለቆች ፊቱ ልቅረብ ልጸልይ ተግቼ ስለሌሎች (፪x) ኢትዮጵያን ግብኛት ተመልከታት በቃል ኪዳንህ አስባት (፬x) @btlfld

አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ******** ስለዚህ ምክንያት በሰማይና በምድር ያለ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ከአብ ፊት እምበረከካለሁ" አዝ፦ አባትነት ሁሉ ከሚሰየምበት ዙፋንህ ካለበት እምበረከካለሁ ጉልበቴ ይታጠፋል ሸክሜ ይራገፋል (፪x) የሕይወቴንና የኑሮዬን ሸክም ቀኑን ሙሉ ይዤው አልመላለስም ጠዋት ተነስቼ ስደፋ በፊቱ ሸክሜ ተራግፎልኝ እሆናለሁ ብርቱ ያለምክንያት አይደል የምምበረከከው ሰምቶ የሚመልስ አምላክ ስላለኝ ነው (፪x) አዝ፦ አባትነት ........... ያለኝን የልቤን ለማውራት በፊቱ ከእግሩ በቀር??? ስሆን ይመጣል መንፈሱ መልስ እንኪመጣልኝ በፊቱ ያለ እረፍት??? መንፈሱ ያግዘኛል ከልቤ??? እንድቃትር??? አምናለሁ ይራገፋል በእኔ እያለው ሸክም በፊቱ ወድቄ ያለ መልስ አልሄድም (፪x) አዝ፦ አባትነት ...... አባቴ ነውና ይሰማኛል ብዬ ልጠይቅ ልረዳ ያለኝን ከልቤ ፊቱ ስንበረከክ ደስታን አሞላለሁ ለጠየቅሁት ሁሉ መልስን አገኛለሁ እንዲሁ አይደለም በፊቱ መውደቄ ማንነቱን በደምብ ገብቶኝ ነው አውቄ (፪x) አዝ፦ አባትነት ...... ተነስ የእኔ ጌታ ስራ እንደቀድሞ ይብቃ ይህ ድካሜ ይወገድ ፈጽሞ ከከበበኝ ነገር መፍትሄ እንድትሆነኝ ወደ አንተ እጣራለሁ ኢየሱሴ ምትሰማኝ ልጥራህ በማለዳ ልጥራህ በጠዋቱ (፪x) ዛሬም ምታድሰኝ ኢየሱስ የናዝሬቱ ኢየሱስ የጥንቱ (፪x) @btlfld

በግ የሆነከው ******* በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምሥጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ" ስለ እራሴ ስለ ግሌ ስለ ቤቴ ስለ አገሬ ስለ ኑሮ ስለ ሕይወት ስለ ያዝኩት አገልግሎት የማዋይህ አለኝና ልምበርከክ ፊትህ እንደገና የማዋይህ አለኝና ልምበርከክ ፊትህ እንደገና (፪x) የእግዚአብሔር በግ የሆንከው ልቤን በፍቅርህ ያደስከው ጓዴ/ጌታ ኢየሱስ እስቲ ና የማዋይህ አለኝና (፪x) *"ያዕቆብ ግን ለብቻው ቀረ አንድ ሰው እስኪነጋ ድረስ ይታገለው ነበር እንዳላሸነፈውም ባየ ጊዜ የጭኑን ሽሉዳ??? ነካው ያዕቆብም የጭኑን ??? ሲታገለው ደነዘዘ እንዲህም አለው 'ሊነጋ አቅላልቷልና ልቀቀኝ' እርሱም 'ካልባረከኝ አለቅህም' አለው እንዲህም አለው 'ስምህ ማነው?' እርሱም 'ያዕቆብ ነኝ' አለው ከእንግዲህ ወዲህ ስምህ እስራኤል ይባላል እንጂ ያዕቆብ አይባልም' በዚያም ስፍራ ባረከው።" በረከትህን ልጥራ በእኔ ላይ በዚህ ማለዳ በረከትህን ልጥራ በቤቴ ላይ በዚህ ማለዳ በረከትህን ልጥራ በአገሬ ላይ በዚህ ማለዳ በረከትህን ልጥራ ቤተሰቤን ላይ በዚህ ማለዳ በረከትህን ልጥራ ስራዬ ላይ በዚህ ማለዳ በረከትህን ልጥራ ትምህርቴ ላይ በዚህ ማለዳ በረከትህን ልጥራ ትዳሬ ላይ በዚህ ማለዳ በረከትህን ልጥራ በእኔነቴ በዚህ ማለዳ ካልባረከኝ አለቅህም (፬x) ካልዳሰስከኝ አለቅህም (፪x) ካልፈወስከኝ አለቅህም (፪x) ካለወጥከኝ አለቅህም (፪x) ካላደስከኝ አለቅህም (፪x) ካልባረከኝ አለቅህም (፪x) @btlfld

ማሳዘን አልፈልግም አንተን *************** ማሳዘን አልፈልግም አንተን (፪x) ማስቀየም አልፈልግም አንተን (፪x) ላሳዝንህ አልፈልግም አንተን (፪x) ላስቀይምህ አልፈልግም አንተን (፪x) ብዙ ውለታ አለብኝ ያደረከው ለሕይወቴ ለቤቴ ለኑሮዬ (፪x) ማሳዘን አልፈልግም አንተን (፪x) ማስቀየም አልፈልግም አንተን (፪x) ብዙ ውለታ አለብኝ ያደረከው ለሕይወቴ ለቤቴ ለኑሮዬ (፪x) የሞላኸው አለ ጐድሎብኝ የጠገንከውም አለ ተሰብሮብኝ የአደስክልኝ ብዙ ነው አርጅቶብኝ የመለስከውም አለ ግራ ገብቶኝ ይሄ ሁሉ በዝቶልኝ ላሳዝንህ አልፈልግም ይከብደኛል ሌላው ቢቀር ዘመኖቼ /ዕድሜዬ ይመሰክሩልኛል አዝ:- ማሳዘን አልፈልግም አንተን (፪x) ... ብዙ ውለታ አለብኝ ያደረከው ለሕይወቴ ለቤቴ ለኑሮዬ (፪x) ማሳዘን አልፈልግም አንተን (፪x) ማስቀየም አልፈልግም አንተን (፪x) ብዙ ውለታ አለብኝ ያደረከው ለሕይወቴ ለቤቴ ለኑሮዬ (፪x) ለሃዘን ቀን ለደስታ ቀን ለፍርድ ቀን ለምጽዓት ቀን የታተምኩበት የአንተ ማኅተም የእርስቴ መያዣ ምጽናናበት ኀጢአትን ባደርግ የምወቀስበት ስለሰማዩ ሚስጥር የምረዳበት መንፈስ ቅዱስ እርሱ ነው ምጽናናበት የቀረ ይቀራል እንጂ (፫x) አሳዝኜው አልወጣም/አልርቅም ከእርሱ እጅ (፬x) አዝ፦ ማሳዘን አልፈልግም አንተን (፪x) .... ብዙ ውለታ አለብኝ ያደረከው ለሕይወቴ ለቤቴ ለኑሮዬ (፪x) ማሳዘን አልፈልግም አንተን (፪x) ማስቀየም አልፈልግም አንተን (፪x) ብዙ ውለታ አለብኝ ያደረከው ለሕይወቴ ለቤቴ ለኑሮዬ (፪x) @btlfld

አዝ፦ አቤቱ እንደቸርነትህ ብዛት እንደ ምህረትህ ብዛት መተላለፌን ደምስሳት (፬x) እኔ መተላለፌን አውቃለሁ ከቶ አልክድም ፊትህ በደሌም ሁልጊዜ በፊትህ ነው አንሳኝ በምህረትህ እንድትመራኝ ብዬ መጣሁ እጠበኝ ከበረዶ ይልቅ ነጭ እሆናለሁ (፪x) አዝ፦ አቤቱ እንደቸርነትህ ብዛት እንደ ምህረትህ ብዛት መተላለፌን ደምስሳት (፬x) ለበደሌ ክርክር አላቀርብም እኔ አልሟገትም መናዘዝ እንጂ እያልኩኝ ኀጢአተኛ ነኝ ሌላ ምን ምርጫ አለኝ ስለዚህ በሂሶብ??? እርጨኝና እጠበኝ ከበረዶ ይልቅ ነጭ እሆናለሁ (፪x) አዝ፦ አቤቱ እንደቸርነትህ ብዛት እንደ ምህረትህ ብዛት መተላለፌን ደምስሳት (፪x) "ጌታ ሆይ ቅዱስ መንፈስህ ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ" ቅዱስ መንፈስህን (፪x) ከእኔ ላይ (፪x) ኧረ አትውሰድብኝ (፪x) ቅዱስ መንፈስህን (፪x) ከእኔ ላይ (፪x) ኧረ አትውሰድብኝ (፪x) ታድያ እኔ ማነኝ ይህን ታላቅ ስም ልጠራ ታዲያ እኔ ማነኝ ፊትህ ለማቅረብ ምሥጋና ግን ፊትህ ለመቆም ሞገስ/ምህረት ከአገኘሁ ምሥጋናን ምሥጋና ምሥጋናን እሰዋለሁ ምሥጋናን ምሥጋና ምሥጋናን እሰዋለሁ (፪x) ምሥጋና ምሥጋና ለኢየሱስ ምሥጋና ይገባሃል አምላክ ለአንተ ለሆንከው ገናና (፪x) "እግዚአብሔር መሃሪና ይቅር ባይ ነው ከቁጣ የራቀ ምህረቱም የበዛ ሁልጊዜ አይቀስፍም ለዘለዓለምም አይቆጣ እንደኀጢአታችን አላደረገብንም እንደበደላችንም አልከፈለንም ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል እንዲሁ እግዚአብሔር ምህረቱን በሚፈሩት ላይ አጠነከረ ቸር እንደሆነ ምህረቱ ለዘለዓለም እንደሆነች እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሁሉ አሁን ይናገሩ" ምህረቱ ለዘለዓለም ነው (፬x) ፣ ምህረቱ ለዘለዓለም ነው (፬x)

አዝ፦ አቤቱ እንደቸርነትህ ብዛት እንደ ምህረትህ ብዛት መተላለፌን ደምስሳት (፬x) እኔ መተላለፌን አውቃለሁ ከቶ አልክድም ፊትህ በደሌም ሁልጊዜ በፊትህ ነው አንሳኝ በምህረትህ እንድትመራኝ ብዬ መጣሁ እጠበኝ ከበረዶ ይልቅ ነጭ እሆናለሁ (፪x) አዝ፦ አቤቱ እንደቸርነትህ ብዛት እንደ ምህረትህ ብዛት መተላለፌን ደምስሳት (፬x) ለበደሌ ክርክር አላቀርብም እኔ አልሟገትም መናዘዝ እንጂ እያልኩኝ ኀጢአተኛ ነኝ ሌላ ምን ምርጫ አለኝ ስለዚህ በሂሶብ??? እርጨኝና እጠበኝ ከበረዶ ይልቅ ነጭ እሆናለሁ (፪x) አዝ፦ አቤቱ እንደቸርነትህ ብዛት እንደ ምህረትህ ብዛት መተላለፌን ደምስሳት (፪x) "ጌታ ሆይ ቅዱስ መንፈስህ ከእኔ ላይ አትውሰድብኝ" ቅዱስ መንፈስህን (፪x) ከእኔ ላይ (፪x) ኧረ አትውሰድብኝ (፪x) ቅዱስ መንፈስህን (፪x) ከእኔ ላይ (፪x) ኧረ አትውሰድብኝ (፪x) ታድያ እኔ ማነኝ ይህን ታላቅ ስም ልጠራ ታዲያ እኔ ማነኝ ፊትህ ለማቅረብ ምሥጋና ግን ፊትህ ለመቆም ሞገስ/ምህረት ከአገኘሁ ምሥጋናን ምሥጋና ምሥጋናን እሰዋለሁ ምሥጋናን ምሥጋና ምሥጋናን እሰዋለሁ (፪x) ምሥጋና ምሥጋና ለኢየሱስ ምሥጋና ይገባሃል አምላክ ለአንተ ለሆንከው ገናና (፪x) "እግዚአብሔር መሃሪና ይቅር ባይ ነው ከቁጣ የራቀ ምህረቱም የበዛ ሁልጊዜ አይቀስፍም ለዘለዓለምም አይቆጣ እንደኀጢአታችን አላደረገብንም እንደበደላችንም አልከፈለንም ሰማይ ከምድር ከፍ እንደሚል እንዲሁ እግዚአብሔር ምህረቱን በሚፈሩት ላይ አጠነከረ ቸር እንደሆነ ምህረቱ ለዘለዓለም እንደሆነች እግዚአብሔርን የሚፈሩ ሁሉ አሁን ይናገሩ" ምህረቱ ለዘለዓለም ነው (፬x) ፣ ምህረቱ ለዘለዓለም ነው (፬x)