1 739
订阅者
-124 小时
+17 天
-730 天
帖子存档
የኢትዮ-ጣልያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2016 ዓ.ም የስልጠና ዘመን አዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማሰልጠን ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገለፀ::
ኮሌጁ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም የዘንድሮ አዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማሰልጠን ኮሌጁ መጠነ ሰፊ ዝግጅት ማድረጉን ገልፀው ወጣቶች እንደ ሀገር የትኩረት ዘርፍ የሆነውና ለወጣቱ ብዙ እድሎችና አማራጮችን ወደያዘው የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ በመቀላቀል ራሳቸውንም ሆነ ሀገርንም መጥቀም ሚችሉበት መልካም አጋጣሚ የተፈጠረ በመሆኑ በተለይ የ2015 ዓ.ም የ12 ክፍል መልቀቂያ ፈተና የወሰዱ ወጣቶች ይህን መልካም እድል በአግባቡ እንዲጠቀሙም መልዕክት አስተላልፈዋል::
የኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤልያስ መሀመድ በበኩላቸው ኮሌጅ በ2016 ዓ.ም የስልጠና ዘመን በዘጠኝ የሙያ ዘርፎች(ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ፣ አውቶሞቲቭ፣ ማኑፉክቸሪንግ፣ ውድ ዎርክ፣ አይ.ሲ.ቲ፣ኮንስትራክሽን፣ ሆቴልና ቱሪዝም፣ ድራፍቲንግና ሰርቬይንግ፣ አካውንቲግ) ስልጠን ለመስጠት እንደተዘጋጁ ጠቅሰው በተጨማሪም ኮሌጁ ዘንድሮ እስከ 2000 አዲስ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ተቀብሎ የማሰልጠን አቅም እንዳለውና ለዚህም ወጣቶችን በሰፊው እየተጠባበቁ እንደሚገኙ ገልፀዋል::
ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ጥቅምት 15/2016 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
