1 743
订阅者
+224 小时
+37 天
-130 天
帖子存档
በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅን አረንጓዴና ጽዱ የማድረግ ዘመቻ።
።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።
"Clean and Green TVET" በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ዘመቻ ዛሬም ቀጥሎ የኮሌጁን የተለያዩ አካባቢዎችን በማፅዳት የኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ አሰልጣኝ መምህራን እና የአስተዳደር ሠራተኞች እንዲሁም ሰልጣኝ ተማሪዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
በመሆኑም በዘመቻው ኮሌጁን ውብ፣ ፅዱና በአረንጓዴ ልምላሜ የተላበሰ በማድረግ ለትምህርትና ስልጠና ሂደቱ ምቹ አካባቢ የመፍጠር ዓላማውን የማረጋገጥ ጅምር ስራ እየተሰራ መሆኑን እና በቀጣይ በተቀናጀ አግባብ ስራዎችን መስራት እንደሚፈልግ ለመመልከት ተችሏል።
ኢትዮ ጣሊያን ኮምኒኬሽን
የካቲት 25/2014 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ትምህርትና ስልጠና ክፍል"
====================================
🟢 በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የኤሌክትሪካልና ኤሌክትሮኒክስ ትምህርትና ስልጠና ክፍል አሰልጣኝ መምህራን እና ሰልጣኝ ተማሪዎች በራስ ተነሳሽነት ከመደበኛ የስራ ቀን ውጪ በእረፍት ቀናቸው የኮሌጁን ቅጥር ጊቢ በማጽዳት አሳለፉ፤
🟡 በነገራችን ላይ የ2013 ዓ.ም ከትምህርትና ስልጠና ክፍሎች የላቀ የስራ ፈጻሚ በመሆን እውቅና ማግኘቱ የሚዘነጋ አይደለም ይህንም ለሌሎች ትምህርትና ስልጠና ክፍሎችና የኮሌጁ አጠቃላይ ማህበረሰብ አርአያ የሚሆን ተግባር በኤሌክትሪካልና ኤሌክትሮኒክስ ትምህርትና ስልጠና ክፍል ሲያከናውን የመጀመሪያው አለመሆኑና በተለይም በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ በግንባር ቀደምነት በመሰለፍ የተለያዩ ኮሌጁን የሚያስጠሩ ስራዎችን ከዚህ በፊት ያከናወነና አሁንም በማከናወን ላይ ይገኛል፤
🔴 በተያያዘም ትምህርትና ስልጠና ክፍሉ ከዚህ በላቀ ተነሳሽነትና አቅም ኮሌጁ በሚፈለገው በየትኛውም አቅጣጫ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማበርከት ዝግጁ መሆኑን የትምህርትና ስልጠና ክፍል ተጠሪው አሰልጣኝ መምህር ወርቅነህ ዋና የገለጹ ሲሆን በመጨረሻም የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ትምህርትና ስልጠና ክፍሉ ላከናወነው አርአያነት የተላበሰ ተግባር አመስግነው ሌሎችም በተመሳሳይ እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።
ድሬዳዋ
የካቲት 12/2014 ዓ.ም
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምንኬሽን
"የአቅም ግንባታ ስልጠና ለአሰልጣኝ መምህራን"
*********
🟢 በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከቀድሞው የፌደራል የአነስተኛና መካከለኛ በአዲሱ አደረጃጀት ከኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ጋር በመተባበር በፋውንደሪ እና ዲዛይን ላይ በኮሌጁ ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ስልጠና ተሰጠ፤
🟡 ይህም ስልጠና ከዚህ በፊት ከኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት በመጡ ባለሙያዎች የተሰራውን የፍላጎት ዳሰሳ መነሻ በማድረግ ስለ ፋውንደሪ ምንነትና አተገባበር ተግባራዊ ስልጠና በኮሌጁ የፋውደሪ ወርክሾፕ ከፌደራል ኢንተርፕራዝ ልማት በመጡ አሰልጣኞች የተሰጠ ሲሆን፤
🔴 ከስልጠናው መጠናቀቅ በኋላም በኢንደስትሪዎች ድጋፍ የሚያደርጉ አሰልጣኝ መምህራን በተሟላ መልኩ ድጋፍ የሚያደርጉበትን አቅም በሚገነባ እና የአሰራር እቅድ በማውጣት የተለያዩ ስራዎችን እየሰሩ ማሳየት እንዲችሉ ታስቦ የተሰጠ መሆኑን ስልጠናውን የሰጡት ባለሙያ ገልጸውልናል፡፡
ድሬዳዋ
የካቲት 12/2014 ዓ.ም
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምንኬሽን
የኮሌጁ ሰራተኞች መድረክ
=================
🎯 በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የ2014 ዓ.ም የመጀመሪያ ስድስት ወር የስራ ዘመን አጠቃላይ የኮሌጁ የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የቀረበበት እና የሁለተኛ ስድስት ወር ቀጣይ የስራ አቅጣጫ የተመላከተበትና በቀረበውም ላይ ከአሰልጠኝ መምህራን እና ከአስተዳደር ሰራተኞች ጋር ውይይት የተደረገበት መድረክ ተካሄደ፤
🎯 በዚህም መድረክ ላይ በመጀመሪያው ስድስት ወር የተከናወኑ እና ሳይጠናቀቁ የቀሩ እንዲሁም ያልተከናወኑ ስራዎች መኖራቸውን መመልከት ተችሏል በዚህም የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን እና አስተዳደር ሰራተኞች የተመለከቷቸውን እና መፈታት አለባቸው ያሏቸውን የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለማንሳት ችለዋል በተነሱትም ሃሳብና አስተያየት እንዲሁም ጥያቄዎች ላይ ከመድረኩ በኮሌጁ አመራሮች ምላሽ ተሰጥቷል በቀጣይም እንደ ግብአት ተወስደው የሚታዩ እና ምላሽ የሚሰጥባቸው መሆኑን ገልጸዋል፤
🎯 በመጨረሻም የተጀመረው የውጤት ተኮር የጥራት ማስተግበሪያ ሰነድ የመጀመሪያው ተርም በተገቢው ሁኔታ በመገምገም ያሉ ችግሮችን በሚፈታ መልኩ የሁለተኛው ተርም በተገቢው መንገድ እንዲተገበር ማድረግ፤ የቀጣይ ተርም ላይ የአሰልጣኝ መምህራን ምደባ በተዘጋጀው የሎድ ጋይድላይን መሰረት ተገቢው ክትትል ተደርጎበት እንዲተገበርና የአሰልጣኝ መምህራ አጠቃቀም ላይ ከቴክኖሎጂ ሽግግር ኢንደስትሪ ኤክስቴሽን የስራ ሂደት ጋር በጋራ መስራት፤ ሁሉም አሰልጣኝ መምህራን ባላቸው አንድ ቀን የኢደስትሪ ኤክስቴሽን ድጋፍ እንዲሰጡ ተገቢው የስራ መመሪያ እንዲሰጣቸው ማድረግ፤ በየዲፓርትመንቱ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች ለኮሌጅ ጥቅም በሚሰጡ ተግባራቶች ላይ እንዲያተኩር ማድረግ፤ የተጀመሩ ቴክኖሎጂዎች በተያዘላቸው ጊዜ ማጠናቀቅ፤ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ተግባራት አንዲጠናቀቁ ማድረግ ፤ የኢንደስትሪ ኤክስቴሽን አገልግሎት ድጋፍ በተመረጡ አሰልጣኝ መምህራን ከሚደረገው በዘለለ ሁሉም አሰልጣኝ መምህራን አንድ ቀን የሚሰሩበት ሁኔታ ማመቻቸት፤ ከትምህርት ቤቶች ጋር የተጀመረውን ስራ በማስፋት የተሻለ የፈጠራ ሀሳብ ያላቸውን በመለየት የጋራ ፕሮጀክቶችን ማከናወን፤ የሳይንስ ላብ መገልገያ የሚሆኑ ቁሳቁሶችን በጋራ የማምረት ስራ ለመስራት የሚያስችሉ ተግባራት መፈፀም፤ የኮሌጅ የካይዘን ትግበራን ከኢንደስትሪ ኤክስቴሽን ስራ ጋር የማናበብ ስራ ማከናወን፤ በኮሌጅ የጋራ አገልግሎት ስራዎች ላይ ተገቢው ትኩረት አድረጎ መስራት፤ የኮሌጅ ሰራተኞች የአቴንዳንስ ቁጥጥር ማድረግ ላይ በኃላፊነት ተወስዶ አስፈላጊው ቁጥጥር ማድረግ፤ በኮሌጁ የሚገኙ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተለያየ መንገድ በማሰባሰብ ሰነድ አዘጋጅቶ በየጊዜው እንዲፈቱ ማድረግ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበት በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በቀጣይ የስራ አቅጣጫ አመላክተዋል፡፡
ድሬዳዋ
የካቲት 11/2014 ዓ.ም
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምንኬሽን
"የሀገሩን ሰርዶ በሀገሩ በሬ"
==================
🟢 በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከድሬዳዋ አስተዳደር የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ጋር በመተባበር የኮሌጁን የICT ትምህርት ክፍል አሰልጣኝ መምህራንን በመጠቀም በኮሌጁ ለሚገኙ አስተዳደር ሰራተኞችና አሰልጣኝ መምህራን ለ10ቀናት የሚቆይ ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል፤
🟡 በዚህም የተግባር ስልጠና ሰልጣኝ የኮሌጁ ሰራተኞች በመሰረታዊ እና በከፍተኛ የኮምፒውተር ክህሎት ብቁ ሊያደርጉ የሚያስችሉ በዋናነት ኮሌጁ ከዲጂታላይዜሽን ጋር ተያይዞ በቀጣይ ሰራተኛው በኢንተርኔት አማካኝነት ቀልጣፋ እና የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲችልና ከዚህ ጋር ተያይዞ ዘመናዊ የሆነ የመረጃ አያያዝ፣ አደረጃጀትና አጠቃቀም እንዲያዳብር አላማውን ያደረገ ስልጠና በመስጠት ግንዛቤ እንዲጨብጡ ያደርጋል፤
🔴 በቀጣይም "የሀገሩን ሰርዶ በሀገሩ በሬ" እንደሚለው ብሂል በኮሌጁ የሚገኙ ሌሎች ትምህርትና ስልጠና ክፍሎችን በመጠቀም መሰል የኮሌጁን አገልግሎት አሰጣጥ የሚያሻሽሉና እሴት በሚጨምሩ የተለያዩ ስራዎችን በመስራት እንደሚገኝ የሚታወቅ ሲሆን በቀጣይም መሰል እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አስታውቀዋል፡፡
ድሬዳዋ
ጥር 30/2014 ዓ.ም
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምንኬሽን
“ተግባራዊ ጥናትና ምርምር (ACTION RESEARCH)”
🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢
✍️ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከEASTRIP PROJECT ጋር በመተባበር ተግባራዊ ጥናትና ምርምር እያደረጉ ለሚገኙና የኤ ደረጃ አሰልጣኝ መምህራን በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ላይ ያተኮረ ስልጠና በማዘጋጀት አቅም የሚገነቡበትን እድል ፈጥሯል፤ ይህም ስልጠና መሰረታዊ ጥናትና ምርምር ከተግባራዊ ጥናትና ምርምር ያለው ልዩነት፤ የአጠናን ስነ-ዘዴን በማወቅ የተቋማዊ ችግሮች ልየታ፤ ምልከታ በማድረግ ለተግባራዊ ጥናትና ምርምር ፕሮፖዛል ማዘጋጀት በሚያስችሉ ጽንሰ ሃሳባዊና ተግባራዊ ዝግጅት ማድረግ በሚያስችል መልኩ ከኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ በመጡ አሰልጣኞች የተሰጠ ሲሆን የስልጠናውም ዋና ዓላማ በኮሌጁ ውስጥ ያሉ ችግሮችን ተግባራዊ ልየታ በማድረግ በጥናትና ምርምር ላይ ተመስርቶ እንዲፈቱ በሚያስችል የአሰልጣኝ መምህራኑን አቅም ለመገንባት ታሳቢ ያደረገ ነው፤
🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡
✍️ በዚህም ስልጠና ላይ በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እንዲሁም በኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ካምፓስ የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን በቀጣይም ልየታ የተደረገባቸውን ችግሮች ለመፍታት እንዲያስችል በተዘጋጁት ፕሮፖዛሎች መሰረት የተግባራዊ ጥናትና ምርምሩን ተጨባጭ ውጤት የሚያስገኙ ስራዎች የሚሰሩበት ሁኔታ እንደሚመቻች የኮሌጁ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ምክትል ዲን የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ ገልጸዋል፡፡
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
ድሬዳዋ
ጥር 28/2014 ዓ.ም
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምንኬሽን
“ተግባራዊ ጥናትና ምርምር (ACTION RESEARCH)”
🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢
✍️ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከEASTRIP PROJECT ጋር በመተባበር ተግባራዊ ጥናትና ምርምር እያደረጉ ለሚገኙና የኤ ደረጃ አሰልጣኝ መምህራን በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ላይ ያተኮረ ስልጠና በማዘጋጀት አቅም የሚገነቡበትን እድል ፈጥሯል፤ ይህም ስልጠና መሰረታዊ ጥናትና ምርምር ከተግባራዊ ጥናትና ምርምር ያለው ልዩነት፤ የአጠናን ስነ-ዘዴን በማወቅ የተቋማዊ ችግሮች ልየታ፤ ምልከታ በማድረግ ለተግባራዊ ጥናትና ምርምር ፕሮፖዛል ማዘጋጀት በሚያስችሉ ጽንሰ ሃሳባዊና ተግባራዊ ዝግጅት ማድረግ በሚያስችል መልኩ ከኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ በመጡ አሰልጣኞች የተሰጠ ሲሆን የስልጠናውም ዋና ዓላማ በኮሌጁ ውስጥ ያሉ ችግሮችን ተግባራዊ ልየታ በማድረግ በጥናትና ምርምር ላይ ተመስርቶ እንዲፈቱ በሚያስችል የአሰልጣኝ መምህራኑን አቅም ለመገንባት ታሳቢ ያደረገ ነው፤
🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡
✍️ በዚህም ስልጠና ላይ በኢትዮ ጣሊያን እና በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እንዲሁም በኢትዮጵያ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ካምፓስ የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን በቀጣይም ልየታ የተደረገባቸውን ችግሮች ለመፍታት እንዲያስችል በተዘጋጁት ፕሮፖዛሎች መሰረት የተግባራዊ ጥናትና ምርምሩን ተጨባጭ ውጤት የሚያስገኙ ስራዎች የሚሰሩበት ሁኔታ እንደሚመቻች የኮሌጁ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ምክትል ዲን የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ ገልጸዋል፡፡
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
ድሬዳዋ
ጥር 28/2014 ዓ.ም
የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምንኬሽን
“ተግባራዊ ጥናትና ምርምር (ACTION RESEARCH)”
🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢🟢
✍️ በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ EASTRIP PROJECT ጋር በመተባበር በጥናትና ምርምር ለሚገኙ እና የኤ ደረጃ አሰልጣኝ መምህራን በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ላይ ያተኮረ ስልጠና በማዘጋጀት አቅም የሚገነቡበትን እድል ፈጥሯል፤ ይህም ስልጠና መሰረታዊ ጥናትና ምርምር ከተግባራዊ ጥናትና ምርምር ያለው ልዩነት፤ የተቋማዊ ችግሮች ልየታ፤ ምልከታ በማድረግ ለተግባራዊ ጥናትና ምርምር ፕሮፖዛል ማዘጋጀት በሚያስችሉ ጽንሰ ሃሳባዊና ተግባራዊ ዝግጅት ማድረግ በሚያስችል ምልኩ ከኢትዮ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ በመጡ አሰልጣኞች የተሰጠ ሲሆን የስልጠናውም ዋና ዓላማ በኮሌጁ ውስጥ ያሉ ችግሮችን ተግባራዊ ልየታ በማድረግ በጥናትና ምርምር ላይ ተመስርቶ እንዲፈቱ በሚያስችል የአሰልጣኝ መምህራኑን አቅም ለመገንባት ታሳቢ ያደረገ ነው፤
🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡🟡
✍️ በዚህም ስልጠና ላይ በኢትዮ ጣሊያን እና በድሬዳዋ ፖሌቴክኒክ ኮሌጅ እንዲሁም በኢትዮ ቴክኒካል ዩኒቨርሲቲ የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ካምፓስ የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን በቀጣይም ልየታ የተደረገባቸውን ችግሮች ለመፍታት እንዲያስችል በተዘጋጁት ፕሮፖዛሎች መሰረት የተግባራዊ ጥናትና ምርምሩን ተጨባጭ ውጤት የሚያስገኙ ስራዎች የሚሰሩበት ሁኔታ እንደሚመቻች የኮሌጁ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ምክትል ዲን የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ ገልጸዋል፡፡
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
ድሬዳዋ
ጥር 28/2014
የኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን
“ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ (STEM)”
===================================
🟢 በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ቀደም ሲል ከተለያዩ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጋር በተደረገው ውይይትና በተደረሰው የጋራ መገባባትና በተዘጋጀው ዕቅድ መሰረት የአዲሱ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፤ የአዲስ ከተማ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የቅድስት ማርያም አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና እና በሂሳብ ማለትም(STEM) ግንዛቤ ለማስጨበጥ በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከጥር 26-28/2014 ዓ.ም ጉብኝት አድርገዋል፡፡
🟡 በዚህም ተማሪዎቹ የተግባር ስልጠና የሚሰጥባችውን የትምህርት ክፍል(workshop) በመጎብኘት ስለቴክኒክና ሙያና በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና እና በሂሳብ (STEM) ግንዛቤ ማስጨበጥ ተችሏል፡፡ እንዲሁም ተማሪዎቹ የማኑፋክቸሪግ ትምህርትና ሰልጠና ክፍል፤ የአውቶሞቲቭ ትምህርትና ሰልጠና ክፍል፤ የፈርኒቸር ትምህርትና ሰልጠና ክፍል እና የኤሌክትሪክና ኢሌክትሮኒክስ ትምህርትና ሰልጠና ክፍል አሰልጣኝ መምህራን ለጉብኝት ለመጡት ተማሪዎቹ የተግባር ስልጠና የሚስጥበትን ክፍሎች(workshops) በማስጎብኘት ተማሪዎቹን ግንዛቤ እንዲጨብጡ አድርጓል፡፡
🔴 በተጨማሪም ሌሎችም በድሬዳዋ አስተዳደር ስር የሚገኙ የአንደኛ ደረጃና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተዘጋጀው ዕቅድና በተዘረጋው መርሃግብር መሰረት በኢትዮጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በመገኘት መሰል ጉብኝቶችን የሚያደርጉ ሲሆን በቀጣይም ከጉብኝት ባሻገር ተማሪዎች በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና እና በሂሳብ(STEM) በፈጠራ ስራ ዝንባሌ ያላችውን የተመረጡ ተማሪዎች ክህሎታችውን ለማሳደግ ይረዳ ዘንድ የተግባር ስልጠና በሚሰጥባችው የትምህርት ክፍል(workshop) ላይ በተግባር የሚደገፉበት ሁኔታ መመቻቸቱን የኮሌጁ የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ምክትል ዲን የሆኑት አቶ ተሾመ ሸዋዬ ገልጸዋል፡፡
ድሬዳዋ
ጥር 28/2014
የኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
