Gullele Communication Office
前往频道在 Telegram
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ ይሁኑ። ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ እናደርጋለን።
显示更多📈 Telegram 频道 Gullele Communication Office 的分析概览
频道 Gullele Communication Office (@gullelepress) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 10 248 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 18 387,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 3 258 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 10 248 名订阅者。
根据 23 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 6 114,过去 24 小时变化为 -66,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 3.02%。内容发布后 24 小时内通常能获得 1.19% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 310 次浏览,首日通常累积 122 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 1。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ ይሁኑ።
ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ እናደርጋለን።”
凭借高频更新(最新数据采集于 24 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
10 248
订阅者
-6624 小时
+2 9017 天
+6 11430 天
帖子存档
+6
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ዘመናዊ ስቱዲዮ በይፋ አስመረቀ።
የመንግስትን የመረጃ አቅርቦት ሥርዓት ለማዘመን እና የዲጂታል ኮሙኒኬሽን አገልግሎትን ለማጠናከር የተገነባው ዘመናዊ ስቱዲዮ ተመርቋል።
የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
👉 የአቶ ኃፍታይ ገብረእግዚአብሔር የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ መልዕክት፦ ስቱዲዮው የመንግስትን የልማት ሥራዎች በተደራጀ መንገድ ከመዘገብ ባለፈ ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ትልቅ አቅም ይፈጥራል።
👉የአቶ ወልዴ ወገሴ የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አስተያየት፦ በዲጂታል ዘመን የመረጃ ፍጥነትና ጥራት ወሳኝ መሆናቸውን ጠቅሰው ስቱዲዮው የንቃተ ህዝብ ፕሮግራሞችን በሙያዊ መንገድ ለማቅረብ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው አብራርተዋል።
👉የአቶ ይከበር ስማቸው የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ ገለጻ፦ስቱዲዮው የማህበራዊእና የልማት እንቅስቃሴዎችን በምስልና በቪዲዮ በማቅረብ ተቋማትን ከህዝብ ጋር ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል።
📌 የቴክኖሎጂ አቅም፦ ስቱዲዮው ለቪዲዮ ቀረጻ ለቀጥታ ስርጭት፣ለቃለ መጠይቅ ለድምፅ ቅጂ እና ለዲጂታል ይዘት ዝግጅት የሚያገለግሉ ዘመናዊ መሣሪያዎችን የያዘ ነው።
🔑የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት በቀጣይም የቴክኖሎጂ አቅሙን በማሳደግ የመረጃ ተደራሽነትን እና የህብረተሰብ ተሳትፎን የማጠናከር ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።
+4
#ይምጡ_ይሸምቱ !!
የእሁድ ገበያ የምርት አቅርቦት እና ፍላጎት በማመጣጠን ድርሻው የላቀ ነው ።
(ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣ 13 - 10 - 2018 ዓ.ም )
በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የህብረተሰቡን የኑሮ ውድነት ጫና ለመቀነስ መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በየሳምንቱ ቅዳሜና እሁድ የሰንበት ገበያ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው።
የኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት በአዲሱ ገበያና በቀጨኔ አካባቢ በሚገኙ የእሁድ ገበያዎችን ቅኝት አድርጓል።
በቅኝታችን የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች፣ የምግብ ግብዓቶች፣ አትክልትና ፍራፍሬና ጨምሮ ሌሎች ምርቶች ለሸማቹ ህብረተሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ መሆኑን ተመልክቷል።
የእሁድ ገበያው የነዋሪዎችን የኑሮ ውድነት ጫና በመቀነስና የገበያውን አቅርቦትና ፍላጎት በማመጣጠን ድርሻው የላቀ መሆኑንን ተገንዝቧል ።
+3
የ2018 ዓ.ም ከተማ አቀፍ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በጉለሌ ክፍለ ከተማ መሰጠት ተጀመረ!
የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በ24 የፈተና ጣቢያዎች የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በይፋ አስጀምሯል። ፈተናው ከዛሬ ሰኔ 11 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚሰጥ ይሆናል።
የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ፣የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይከበር ስማቸው፣ የአዲስ አበባ ትምህርት የቢሮ ኃላፊ አማካሪ ወ/ሮ አበበች ነጋሽ እና ክፍለ ከተማው የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባርኬ ዴቲን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች በጣቢያዎች ተገኝተው ተማሪዎችን አበረታተዋል።
ተማሪዎቻችን ዓመቱን ሙሉ ከቀሰሙት ትምህርት በተጨማሪ፣ የራስ መተማመናቸው እንዲጎለብት በርካታ የዝግጅት ሥራዎች ተሠርተዋል።ፈተናው በተረጋጋ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ሁሉን አቀፍ ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል፡፡
ለተፈታኝ ተማሪዎቻችን በሙሉ መልካም ዕድልና ስኬትን እንመኛለን!
+5
በጉለሌ ክፍለ ከተማ የሚሰጡ አገልግሎቶች መሻሻል ማሳየታቸውን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡
(ጉለሌ ኮሙኒኬሽን:10/10/18)
የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት በጉለሌ ክፍለ ከተማ በየሳምንቱ ረቡዕ እና አርብ የባለጉዳይ ቀን በማስመልከት በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ የምልከታና የተገልጋዮች አስተያየት ጠይቋል።
የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ቤት ረቡዕ እና አርብ የሚሰጠውን የባለጉዳይ ቀን ምክንያት በማድረግ በተቋማት ላይ ምልከታ በማድረግ ያነጋገርናቸው ተገልጋዮች በፊት ከነበረው ምልልስና እንግልት ቀንሶ አሁን ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎት በተሻለ አቀባበል እያገኘን ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።
በክፍለ ከተማው አስተዳደር የተገልጋዩን ማህብረሰብ እርካታ ለማረጋገጥና የተሻሻለ አገልግሎት በየጊዜው ለማቅረብ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጿል።
በጉለሌ ክፍለ ከተማ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በተመረጡ ቦታዎች የእሁድ ገበያ ተዘጋጅቷል።
ይምጡና ይሸምቱ!
+5
የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የእሁድ ገበያ ማስፋትና በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን ማቅረብ እንደሚገባ ተገለፀ።
( ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣ 06- 10 -2018 ዓ.ም )
በጉለሌ ክፍለ ከተማ በ10ሩም ወረዳ በቅዳሜ እና እሁድ ገበያ ዛሬም ከበፊቱ በተሻለ ሁኔታ ተጠናክሮ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረቡ እንደቀጠለ ነው።
ህብረተሰቡ በአቅራቢያው በሚገኘው የእሁድ ገበያ የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ግብይት እያደረገ ይገኛል።
በክፍለ ከተማው የኑሮ ውድነት ጫናውን ለማረጋጋት በ10ሩም ወረዳ የእሁድ ገበያ ስፍራዎች ተቋቁመው ህብረተሰቡ ሚዛናዊ በሆነ ዋጋ አስፈላጊ ምርቶችን እንዲገበያይ እየተደረገ ይገኛል ።
የአትክልትና ፍራፍሬ የግብርና የጥራጥሬ አቅርቦት በስፋት በመቅረቡ በመመልከት ወደፊትም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገልጿል።
ዘመናዊ የመንግስት ንብረት አስተዳደር ስርዓትን በመከተል ከብክነት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ።
(ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣ 07 -09 -2018 ዓ.ም )
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ከክፍለ ከተማው ንብረት አስተዳደር ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን "የመንግስት ንብረት በአግባቡ መጠቀም የሁላችን ኃላፊነት ነው ?*" በሚል መሪ ቃል የእንጠያየቅ መድረክ አካሂዷል።
በእንጠያየቅ መድረኩ ላይ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰርካለም ተፈሪ እንደተናገሩት ጽ/ቤቱ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ፣ አስተዳደሩ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው የዛሬው የእንጠያየቅ መድረክ ዋና ዓላማ የመንግስት ንብረትን በአግባቡ በመጠቀም ረገድ የሚታዩ ክፍተቶችን ለማረም ያለመ መሆኑን ገልፀዋል።
በተለያየ ደረጃ ላይ ያሉ የመንግስት የተለያዩ ንብረቶችን በዘመናዊ መልኩ በመመዝገብና ከብክነትና ከብልሹ አሰራር በመጠበቅ ላይ የባለድርሻ አካላት ሚና የጎላ በመሆኑ ይህ መድረክ መዘጋጀቱን ኃላፊዋ ተናግረዋል።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ የመንግስት ንብረት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ትዕግስት በፍቃዱ በበኩላቸው በክፍለ ከተማው የንብረት አስተዳደር ስርዓት ዘመናዊና በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን የተሰራ መሆኑን ገልጸው በተለይም የመንግስት ንብረትን ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በመደረጉ ለውጦች መጥቷል በቀጣይ አስተዳደሩ በትኩረት ይሰራል ብለዋል።
የንብረት አስተዳደር ሶፍትዌር በወረዳዎች ፣ በትምህርት ቤቶችና በጤና ተቋማት የሚገኙ የመንግስት ንብረት አስተዳደር በአዲስ መልክ በማደራጀት የመንግስት ሀብትና ንብረትን በዘመናዊ መልኩ በመምራት፣ በመቆጣጠርና በማስተዳደር የተስተካከለ ቁመና እንዲኖረው የማድረግ ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል፡፡
በተለያየ ደረጃ ላይ ያሉ የመንግስት ህንፃዎች መረጃ የማሰባሰብና የማደራጀት ህንፃዎች ለሰራተኛው ምቹና ውብ ለማድረግ የእድሳትና የጥገና ሥራ መሥራት ስራ ማከናወኑን ገልጸዋል።
የእንጠያየቅ መድረኩ ተሳታፊዎች መድረኩ የመንግስት ንብረት ከብክነት ለመከላከል የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ያሳየ መሆኑን ገልጸው በወረዳዎች የሚገኙ ንብረቶች አስተዳደር ጥገና ያነሰ መሆኑ ፣ የንብረት ርክክብ ዙሪያ ጥያቄዎች ያነሱ ሲሆን በዘርፉ ላይ የተነሱ ጥያቄዎችን ከተቋማት ኃላፊዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
+3
#የአገልግሎት_ቀንን_ለተገልጋዮች !!
(ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣ 05 -10 -2018 ዓ.ም )
የአገልግሎት አሰጣጥ በአግባቡ እና በተቀላጠፈ መልኩ እየተሰጠ ለመሆኑ የአገልግሎት ቀን ምልከታ ተደረገ ።
በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ጨምሮ በሁሉም ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ በተሻለ መልኩ እየተሰጠ ይገኛል።
በክፍለ ከተማ አስተዳደር የባለ ጉዳይ ቀንን ምክንያት በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥ ቀን ምልከታ ተደርጓል።
በክፍለ ከተማው በባለ ጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ እንዲሁም ማህበረሰቡን ለማርካት እና የተልጋዩን እንግልት ለመቀነስ የሚያስችል የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
አመራሩ ፣ባለሙያውና ባለድርሻ አካላት ባለጉዳይን በቢሮ ቁጭ ብሎ ማገልገልና ወቅቱን ጠብቆ ምላሽ መስጠት ስራ በተቀናጀ እና በተጠናከረ መልኩ እየተሰጠ ይገኛል::
ኢትዮጵያ መርጣለች፤ አሸንፋለች!!
የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከአጠቃላይ አመራሮች ጋር በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የተያዙ መንትያ ግቦችን ለማሳካት የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይም ውይይት አካሄደ።
በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ማሾ ኦላና ህብረተሰቡ ከሌሊት እስከ ሌሊት በፅናት ድምፁን በመስጠት የኢትዮጵያን አሸናፊነት በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል።
ምርጫው ዴሞክራሲያዊ ገለልተኛና ሰላማዊ እንዲሆን አመራሩ የፀጥታ አካላት የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሲቪል ማህበራትና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በቅንጅት የላቀ ሚና ተጫውተዋል።
የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በምርጫው የታየውን አንድነት በመድገም የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በትኩረት ለመመለስና ህዝብን በታማኝነት ለማገልገል ቃል ገብተዋል።
የብልፅግና ፓርቲ የጉለሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይከበር ስማቸው በበኩላቸው ፓርቲው የምርጫ ቦርድን ህጎች ተከትሎ ከተፎካካሪዎች ጋር በሰላማዊ መንገድ መወዳደሩን ጠቅሰው በቀጣይም ለሀገራዊ ብልጽግና በጋራ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።
ከነበሩ ጥንካሬዎች በመማር እና ጉድለቶችን በማረም በአገልጋይነት መንፈስ ህዝባችንን ለመካስ ብርቱ ርብርብ ይደረጋል።
የጸና ቃልኪዳን፤ በለውጥ ላይ ያለች ሀገር!
▸ የአፍሪካ ግዙፉ ግድብ፣
የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ፣
▸ የ48+ ቢሊዮን ችግኞች ተከላ፤ ለተፈጥሮና ለሥነ-ምህዳር መታደስ
▸ ከተሞች ፈክተዋል፣ ገጠሮች እየዘመኑ ነው፣ መንገዶች፣ አረንጓዴ ልማትና ዘመናዊ መሠረተ-ልማቶች ተደራሽ እየሆኑ ነው
▸መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፦ ምቹና ከቢሮክራሲ የጸዳ የመንግሥት አገልግሎትን ለዜጎች ማድረስ
#PMOEthiopia #EthiopiaDelivers
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
