ar
Feedback
Gullele Communication Office

Gullele Communication Office

الذهاب إلى القناة على Telegram

የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ ይሁኑ። ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ እናደርጋለን።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Gullele Communication Office

تُعد قناة Gullele Communication Office (@gullelepress) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 10 248 مشتركاً، محتلاً المرتبة 18 387 في فئة الأخبار والوسائط والمرتبة 3 258 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 10 248 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 23 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 6 114، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -66، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 3.02‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 1.19‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 310 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 122 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 1.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን የቴሌግራም ቻናል ቤተሰብ ይሁኑ። ትክክለኛና ወቅታዊ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ እናደርጋለን።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 24 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الأخبار والوسائط.

10 248
المشتركون
-6624 ساعات
+2 9017 أيام
+6 11430 أيام
أرشيف المشاركات
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ዘመናዊ ስቱዲዮ በይፋ አስመረቀ። የመንግስትን የመረጃ አቅርቦት ሥርዓት ለማዘመን እና የዲጂታል ኮሙኒኬሽን አገልግሎትን ለማጠናከር የተገነባው ዘመናዊ ስቱዲዮ ተ
+6
የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ዘመናዊ ስቱዲዮ በይፋ አስመረቀ። የመንግስትን የመረጃ አቅርቦት ሥርዓት ለማዘመን እና የዲጂታል ኮሙኒኬሽን አገልግሎትን ለማጠናከር የተገነባው ዘመናዊ ስቱዲዮ ተመርቋል። የተነሱ ዋና ዋና ነጥቦች፦ 👉 የአቶ ኃፍታይ ገብረእግዚአብሔር የአዲስ አበባ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ መልዕክት፦ ስቱዲዮው የመንግስትን የልማት ሥራዎች በተደራጀ መንገድ ከመዘገብ ባለፈ ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ትልቅ አቅም ይፈጥራል። 👉የአቶ ወልዴ ወገሴ የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አስተያየት፦ በዲጂታል ዘመን የመረጃ ፍጥነትና ጥራት ወሳኝ መሆናቸውን ጠቅሰው ስቱዲዮው የንቃተ ህዝብ ፕሮግራሞችን በሙያዊ መንገድ ለማቅረብ ጉልህ ሚና እንደሚኖረው አብራርተዋል። 👉የአቶ ይከበር ስማቸው የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ ገለጻ፦ስቱዲዮው የማህበራዊእና የልማት  እንቅስቃሴዎችን በምስልና በቪዲዮ በማቅረብ ተቋማትን ከህዝብ ጋር ይበልጥ ያቀራርባል ብለዋል። 📌 የቴክኖሎጂ አቅም፦ ስቱዲዮው ለቪዲዮ ቀረጻ ለቀጥታ ስርጭት፣ለቃለ መጠይቅ ለድምፅ ቅጂ እና ለዲጂታል ይዘት ዝግጅት የሚያገለግሉ ዘመናዊ መሣሪያዎችን የያዘ ነው። 🔑የጉለሌ  ክፍለ ከተማ ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት በቀጣይም የቴክኖሎጂ አቅሙን በማሳደግ የመረጃ ተደራሽነትን እና የህብረተሰብ ተሳትፎን የማጠናከር ሥራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቋል።

#ይምጡ_ይሸምቱ !! የእሁድ ገበያ የምርት አቅርቦት እና ፍላጎት በማመጣጠን ድርሻው የላቀ ነው ። (ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣ 13 - 10 - 2018 ዓ.ም ) በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የህብረተሰቡን
+4
#ይምጡ_ይሸምቱ !! የእሁድ ገበያ የምርት አቅርቦት እና ፍላጎት በማመጣጠን ድርሻው የላቀ ነው ። (ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣ 13 - 10 - 2018 ዓ.ም ) በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የህብረተሰቡን የኑሮ ውድነት ጫና ለመቀነስ መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በየሳምንቱ ቅዳሜና እሁድ የሰንበት ገበያ ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው። የኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት በአዲሱ ገበያና በቀጨኔ አካባቢ በሚገኙ የእሁድ ገበያዎችን ቅኝት አድርጓል። በቅኝታችን የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች፣ የምግብ ግብዓቶች፣ አትክልትና ፍራፍሬና ጨምሮ ሌሎች ምርቶች ለሸማቹ ህብረተሰብ በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ መሆኑን ተመልክቷል። የእሁድ ገበያው የነዋሪዎችን የኑሮ ውድነት ጫና በመቀነስና የገበያውን አቅርቦትና ፍላጎት በማመጣጠን ድርሻው የላቀ መሆኑንን ተገንዝቧል ።

የ2018 ዓ.ም ከተማ አቀፍ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በጉለሌ ክፍለ ከተማ መሰጠት ተጀመረ! የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በ24 የፈተና ጣቢያዎች የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በይፋ አስጀምሯል።
+3
የ2018 ዓ.ም ከተማ አቀፍ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በጉለሌ ክፍለ ከተማ  መሰጠት ተጀመረ!   የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በ24 የፈተና ጣቢያዎች የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በይፋ አስጀምሯል። ፈተናው ከዛሬ ሰኔ 11 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ የሚሰጥ ይሆናል።   የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ፣የብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይከበር ስማቸው፣ የአዲስ አበባ ትምህርት የቢሮ ኃላፊ አማካሪ ወ/ሮ አበበች ነጋሽ እና ክፍለ ከተማው የትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ባርኬ ዴቲን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች በጣቢያዎች ተገኝተው ተማሪዎችን አበረታተዋል።   ተማሪዎቻችን ዓመቱን ሙሉ ከቀሰሙት ትምህርት በተጨማሪ፣ የራስ መተማመናቸው እንዲጎለብት በርካታ የዝግጅት ሥራዎች ተሠርተዋል።ፈተናው በተረጋጋ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ሁሉን አቀፍ ቅድመ ዝግጅት ተደርጓል፡፡ ለተፈታኝ ተማሪዎቻችን በሙሉ መልካም ዕድልና ስኬትን እንመኛለን!

በጉለሌ ክፍለ ከተማ የሚሰጡ አገልግሎቶች መሻሻል ማሳየታቸውን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡ (ጉለሌ ኮሙኒኬሽን:10/10/18) የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት በጉለሌ ክፍለ ከተማ በየሳምንቱ ረቡዕ እና አር
+5
በጉለሌ ክፍለ ከተማ የሚሰጡ አገልግሎቶች መሻሻል ማሳየታቸውን ተገልጋዮች ገለጹ፡፡   (ጉለሌ ኮሙኒኬሽን:10/10/18) የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት በጉለሌ ክፍለ ከተማ በየሳምንቱ ረቡዕ እና አርብ  የባለጉዳይ ቀን በማስመልከት በአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ የምልከታና የተገልጋዮች አስተያየት ጠይቋል።   የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ቤት ረቡዕ እና አርብ የሚሰጠውን የባለጉዳይ ቀን ምክንያት በማድረግ በተቋማት ላይ ምልከታ በማድረግ ያነጋገርናቸው ተገልጋዮች በፊት ከነበረው ምልልስና እንግልት ቀንሶ አሁን ቀልጣፋና ጥራት ያለው አገልግሎት በተሻለ አቀባበል እያገኘን ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።   በክፍለ ከተማው አስተዳደር የተገልጋዩን ማህብረሰብ እርካታ ለማረጋገጥና የተሻሻለ አገልግሎት በየጊዜው ለማቅረብ የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጿል።

በጉለሌ ክፍለ ከተማ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በተመረጡ ቦታዎች የእሁድ ገበያ ተዘጋጅቷል። ይምጡና ይሸምቱ!
በጉለሌ ክፍለ ከተማ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ በተመረጡ ቦታዎች የእሁድ ገበያ ተዘጋጅቷል። ይምጡና ይሸምቱ!

የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የእሁድ ገበያ ማስፋትና በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን ማቅረብ እንደሚገባ ተገለፀ። ( ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣ 06- 10 -2018 ዓ.ም ) በጉለሌ ክፍለ ከተማ በ10ሩም ወረዳ በቅዳ
+5
የኑሮ ውድነትን ለማቃለል የእሁድ ገበያ ማስፋትና በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን ማቅረብ እንደሚገባ ተገለፀ። ( ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣ 06- 10 -2018 ዓ.ም ) በጉለሌ ክፍለ ከተማ በ10ሩም ወረዳ በቅዳሜ እና እሁድ ገበያ ዛሬም ከበፊቱ በተሻለ ሁኔታ ተጠናክሮ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረቡ እንደቀጠለ ነው። ህብረተሰቡ በአቅራቢያው በሚገኘው የእሁድ ገበያ የግብርናና ኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ግብይት እያደረገ ይገኛል። በክፍለ ከተማው የኑሮ ውድነት ጫናውን ለማረጋጋት በ10ሩም ወረዳ የእሁድ ገበያ ስፍራዎች ተቋቁመው ህብረተሰቡ ሚዛናዊ በሆነ ዋጋ አስፈላጊ ምርቶችን እንዲገበያይ እየተደረገ ይገኛል ። የአትክልትና ፍራፍሬ የግብርና የጥራጥሬ አቅርቦት በስፋት በመቅረቡ በመመልከት ወደፊትም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገልጿል።

photo content
+7

ዘመናዊ የመንግስት ንብረት አስተዳደር ስርዓትን በመከተል ከብክነት መከላከል እንደሚገባ ተገለጸ። (ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣ 07 -09 -2018 ዓ.ም ) የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ከክፍለ ከተማው ንብረት አስተዳደር ጽ/ቤት ጋር በጋራ በመሆን "የመንግስት ንብረት በአግባቡ መጠቀም የሁላችን ኃላፊነት ነው ?*" በሚል መሪ ቃል የእንጠያየቅ መድረክ አካሂዷል። በእንጠያየቅ መድረኩ ላይ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሰርካለም ተፈሪ እንደተናገሩት ጽ/ቤቱ በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ህብረተሰቡ የሚያነሳቸውን ጥያቄዎች ፣ አስተዳደሩ እያከናወናቸው የሚገኙ ተግባራትን ተደራሽ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው የዛሬው የእንጠያየቅ መድረክ ዋና ዓላማ የመንግስት ንብረትን በአግባቡ በመጠቀም ረገድ የሚታዩ ክፍተቶችን ለማረም ያለመ መሆኑን ገልፀዋል። በተለያየ ደረጃ ላይ ያሉ የመንግስት የተለያዩ ንብረቶችን በዘመናዊ መልኩ በመመዝገብና ከብክነትና ከብልሹ አሰራር በመጠበቅ ላይ የባለድርሻ አካላት ሚና የጎላ በመሆኑ ይህ መድረክ መዘጋጀቱን ኃላፊዋ ተናግረዋል። የጉለሌ ክፍለ ከተማ የመንግስት ንብረት አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ትዕግስት በፍቃዱ በበኩላቸው በክፍለ ከተማው የንብረት አስተዳደር ስርዓት ዘመናዊና በቴክኖሎጂ የተደገፈ እንዲሆን የተሰራ መሆኑን ገልጸው በተለይም የመንግስት ንብረትን ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በመደረጉ ለውጦች መጥቷል በቀጣይ አስተዳደሩ በትኩረት ይሰራል ብለዋል። የንብረት አስተዳደር ሶፍትዌር በወረዳዎች ፣ በትምህርት ቤቶችና በጤና ተቋማት የሚገኙ የመንግስት ንብረት አስተዳደር በአዲስ መልክ በማደራጀት የመንግስት ሀብትና ንብረትን በዘመናዊ መልኩ በመምራት፣ በመቆጣጠርና በማስተዳደር የተስተካከለ ቁመና እንዲኖረው የማድረግ ስራዎች ተከናውነዋል ብለዋል፡፡ በተለያየ ደረጃ ላይ ያሉ የመንግስት ህንፃዎች መረጃ የማሰባሰብና የማደራጀት ህንፃዎች ለሰራተኛው ምቹና ውብ ለማድረግ የእድሳትና የጥገና ሥራ መሥራት ስራ ማከናወኑን ገልጸዋል። የእንጠያየቅ መድረኩ ተሳታፊዎች መድረኩ የመንግስት ንብረት ከብክነት ለመከላከል የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ያሳየ መሆኑን ገልጸው በወረዳዎች የሚገኙ ንብረቶች አስተዳደር ጥገና ያነሰ መሆኑ ፣ የንብረት ርክክብ ዙሪያ ጥያቄዎች ያነሱ ሲሆን በዘርፉ ላይ የተነሱ ጥያቄዎችን ከተቋማት ኃላፊዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።

#የአገልግሎት_ቀንን_ለተገልጋዮች !! (ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣ 05 -10 -2018 ዓ.ም ) የአገልግሎት አሰጣጥ በአግባቡ እና በተቀላጠፈ መልኩ እየተሰጠ ለመሆኑ የአገልግሎት ቀን ምልከታ ተደረገ ። በ
+3
#የአገልግሎት_ቀንን_ለተገልጋዮች !! (ጉለሌ ኮሙኒኬሽን ፣ 05 -10 -2018 ዓ.ም ) የአገልግሎት አሰጣጥ በአግባቡ እና በተቀላጠፈ መልኩ እየተሰጠ ለመሆኑ የአገልግሎት ቀን ምልከታ ተደረገ ። በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ጨምሮ በሁሉም ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጥ በተሻለ መልኩ እየተሰጠ ይገኛል። በክፍለ ከተማ አስተዳደር የባለ ጉዳይ ቀንን ምክንያት በማድረግ የአገልግሎት አሰጣጥ ቀን ምልከታ ተደርጓል። በክፍለ ከተማው በባለ ጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ እንዲሁም ማህበረሰቡን ለማርካት እና የተልጋዩን እንግልት ለመቀነስ የሚያስችል የተቋማት አገልግሎት አሰጣጥ ተጠናክሮ ቀጥሏል። አመራሩ ፣ባለሙያውና ባለድርሻ አካላት ባለጉዳይን በቢሮ ቁጭ ብሎ ማገልገልና ወቅቱን ጠብቆ ምላሽ መስጠት ስራ በተቀናጀ እና በተጠናከረ መልኩ እየተሰጠ ይገኛል::

photo content
+6

photo content
+6

ኢትዮጵያ መርጣለች፤ አሸንፋለች!! የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከአጠቃላይ አመራሮች ጋር በ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ የተያዙ መንትያ ግቦችን ለማሳካት የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም በቀጣይ አቅጣጫዎች ላይም ውይይት አካሄደ። በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የመንግስት ዋና ተጠሪ ዶ/ር ማሾ ኦላና ህብረተሰቡ ከሌሊት እስከ ሌሊት በፅናት ድምፁን በመስጠት የኢትዮጵያን አሸናፊነት በተግባር ማረጋገጡን ገልጸዋል። ምርጫው ዴሞክራሲያዊ ገለልተኛና ሰላማዊ እንዲሆን አመራሩ የፀጥታ አካላት የኮሙኒኬሽን ዘርፍ ሲቪል ማህበራትና ተፎካካሪ ፓርቲዎች በቅንጅት የላቀ ሚና ተጫውተዋል። የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ በምርጫው የታየውን አንድነት በመድገም የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በትኩረት ለመመለስና ህዝብን በታማኝነት ለማገልገል ቃል ገብተዋል። የብልፅግና ፓርቲ የጉለሌ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይከበር ስማቸው በበኩላቸው ፓርቲው የምርጫ ቦርድን ህጎች ተከትሎ ከተፎካካሪዎች ጋር በሰላማዊ መንገድ መወዳደሩን ጠቅሰው በቀጣይም ለሀገራዊ ብልጽግና በጋራ መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል። ከነበሩ ጥንካሬዎች በመማር እና ጉድለቶችን በማረም በአገልጋይነት መንፈስ ህዝባችንን ለመካስ ብርቱ ርብርብ ይደረጋል።

የጸና ቃልኪዳን፤ በለውጥ ላይ ያለች ሀገር! ‎ ‎▸ የአፍሪካ ግዙፉ ግድብ፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃ፣ ‎ ‎▸ የ48+ ቢሊዮን ችግኞች ተከላ፤ ለተፈጥሮና ለሥነ-ምህዳር መታደስ ‎ ‎▸ ከተሞች ፈክተዋል፣ ገጠሮች እየዘመኑ ነው፣ መንገዶች፣ አረንጓዴ ልማትና ዘመናዊ መሠረተ-ልማቶች ተደራሽ እየሆኑ ነው ‎ ‎▸መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት፦ ምቹና ከቢሮክራሲ የጸዳ የመንግሥት አገልግሎትን ለዜጎች ማድረስ ‎ ‎#PMOEthiopia #EthiopiaDelivers