SNE Ethiopia - ልዩ ፍላጎት ትምህርት
前往频道在 Telegram
This channel focuses on raising public awareness, increasing education and sharing tips about childrens with and without disabilities. For more info @Snie_bot
显示更多357
订阅者
+124 小时
+17 天
+130 天
数据加载中...
吸引订阅者
十二月 '24
十二月 '24
+16
在0个频道中
十一月 '24
+15
在0个频道中
Get PRO
十月 '24
+14
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+359
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 21 十二月 | +1 | |||
| 20 十二月 | 0 | |||
| 19 十二月 | +1 | |||
| 18 十二月 | +2 | |||
| 17 十二月 | 0 | |||
| 16 十二月 | +1 | |||
| 15 十二月 | 0 | |||
| 14 十二月 | +1 | |||
| 13 十二月 | 0 | |||
| 12 十二月 | 0 | |||
| 11 十二月 | 0 | |||
| 10 十二月 | +3 | |||
| 09 十二月 | 0 | |||
| 08 十二月 | 0 | |||
| 07 十二月 | 0 | |||
| 06 十二月 | 0 | |||
| 05 十二月 | +1 | |||
| 04 十二月 | +3 | |||
| 03 十二月 | +2 | |||
| 02 十二月 | +1 | |||
| 01 十二月 | 0 |
频道帖子
| 2 | 没有文字... | 417 |
| 3 | ድረስ ያሰበበት ከመድረስ የሚከለክል ነገር የለም!" ብሎ ያምናል።
በለጠ ለዚህ ስኬት እንዲበቃ እግዚአብሔር እንደረዳው ይናገራል። የግል ጥረቱና ለፈተናዎች ሁሉ እጅ አለመሰጠቱ የስኬቱ ዋነኛ ምክንያት ነው። ሐዋሳ ዩኒቨርስቲ፣ የሲዳማ ክልል ሴቶችና ህፃናት ቢሮ፥ ለጋሽ ግለሰቦች፣ የተለያዩ ቢሮ የሥራ ኃላፊዎች፣ ቀና ልብ ያላቸው የማህበረሰብ አካላት፣ ወጣቶች ከስኬቱ ጀርባ እንደሚገኙ ይናገራል።
ለወደፊት ምን መሆን እንደሚፈልግ ጠይቄው እግዚአብሔርንና ማህበረሰብን ማገልገል ዋና የሕይወት ግቡ መሆኑን አጫውቶኛል።
ምንጭ ፦ ሳሙኤል በላይነህ ቃ'ሜ | 426 |
| 4 | አዎን ይቻላል‼️አካል ጉዳተኝነቱን ድል የነሳ አንበሳ!!
ይህ ከሰንሰለታማው ጋራምባ ተራራ ግርጌ በመነሳት በአካል ጉዳተኝነትና በሕይወት ፈተና ሳይበገር፣ ተፈትኖ ለሰኬት የበቃው፣ የወጣቱ በለጠ ቡቱና (የአርሶ አደር ልጅ) አጭር የሕይወት መንገድ ታሪክ ነው!
በለጠ ቡቱና (ያምቡሌ) ትውልድና እድገቱ አርቤጎና ወረዳ ሲዳማ ነው። በለጠ 1989ዓ.ም አርቤጎና ጎዋ ቀበሌ ልዩ ሥፍራ ቡላ ተወለደ። በለጠ ከልጅነቱ ጀምሮ በሁለት እግሩ መራመድ አይችልም ነበር። በዚህ ምክንያት እጆቹን እንደ እግርም እንደ እጅም ለመጠቀም ተገደደ። አካል ጉዳተኝነትን እንደ የእግዚአብሔር ቁጣ ተደርጎ በሚታሰብበት በአብዛኛው የኢትዮጵያ ማህበረሰብ በገጠር ተወልዶ፣ አይደለም ተምሮ ለወግ ማዕረግ መብቃት በተሰፋ መኖር መቻል በራሱ ፈታኝ ነው።
በለጠ በህፃንነቱ በወላጅ እናቱና አባቱ መካከል በተፈጠረው አለመግባባት በመለያየታቸው ሌላ የሕይወት ፈተና ለመጋፈጥ ተገዷል። የወላጆቹ መለያየት በአካል ጉዳተኝነቱ ላይ ታክሎበት ሕይወትን በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ ዓይነት አድርገውበታል።
በለጠ ዕድሜው ለትምህርት ሲደርስ በአካባቢ ወደ ትምህርት ቤት የሚሄዱ ልጆችን እያየ "እኔም ከእነዚህ ልጆች ጋር ትምህርት ቤት በሄድኩ!" እያለ ይብሰለሰል ጀመር። ግና አካል ጉዳተኛነቱ፣ ትምህርት ቤት በአቅራቢያው አለመገኘቱ፣ የመንገድ መሠረተ ልማት ችግር፣ የመጓጓዣ እጦት፣ ማህበረሰቡ በአካል ጉዳተኞች ላይ ያለው አሉታዊ አመለካከት፣ ወላጅ እናት ቤት ውስጥ በማጣት እህል ውሃ የሚሰጥ ሰው መጥፋቱ ይህ ሁሉ ፈተና ከፊት ለፊት ተሰልፎ የሚጠብቀው ነበር። በለጠ ልቡ ኮስታራ ነበረና ፈተናዎቹን ሁሉ ለመጋፈጥ ቆርጦ ተነሳ። "አልችልም!" በይነትን ገና በጠዋቱ ቀበረ። "አዎን ይቻላል!" አለ። አባቱ ከGowa (ጎዋ) ጋራምባ ተራራ አከባቢ Fiide Fooliishsho (ፊዴ ፎሊሾ) ቀበሌ ወዳለው እርሻ ተዘዋውሮ መጥቶ እያለ ከእነሱ መንደር በ5 ኪ.ሜትር ርቀት ላይ ወደሚገኝ Shurro (ሹሮ) አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለመግባት ወሰነ።
"የት ልትደርስ ትማራለህ? በዚህ ጭቃ በእጅህ እየ ደኽህ መከራ ከምታይ አርፈህ አትተኛም!" የአብዛኛው ማህበረሰብ ቅስም ሰባሪ አሰተያየት ነበር። በሌ ለአሉታዊ አሰተያየቶች ጆሮ አልሰጠም። የአንደኛ ክፍል ትምህርቱን አንድ ቢሎ ሹሮ ት/ቤት ጀመረ።
ጋራምባ ተራራና አከባቢው በሲዳማ ክልል የደጋማ ሥፍራዎች ቁንጮ መሆኑ ይታወቃል። በዚህ ተራራ አቅራቢያ የሚገኘው ሹሮ ት/ቤ ከአርቤጎና ወረዳ የሩቅ ት/ቤት ተብለው ከሚታወቁት አንዱ ት/ቤት ነው። የአከባቢው የአየር ንብረት በጣም ዝናባማ፣ መልካ ምድሩ ተራራማ፣ የመረት አቀማመጥ አይደለም ለአካል ጉዳተኛ ለጤነኛ ሰውም ፈታኝ ነው። በለጠ ለተፈጥሮ ፈተና እጅ ሳይሰጥ ከፊዴ ፎሊሾ ቀበሌ ከመኖሪያ በቤታቸው ለሊት 11:00 ወጥቶ 5 ኪ.ሜ ከ3-4 ሰዓት በእጁ እየተራመደ ትምህርት ቤት 2:00 ይደርስ ነበር። በዚህ መልኩ ወደ ት/ቤት ሲሄድ ብዙ ፈተና ገጥሞታል። በአንድ ወቅት ወንዝ ዘሎ ለመሻገር ሲሞክር ይዞት ሄዶ እግዚአብሔር እንዳሰጣለው አጫውቶኛል። በለጠ ከአብሮ አደጎቹ እጅግ ቀድሞ ጉዞ ሰለሚጀምር ዝናብና ብርድ ከማንም በላይ ተፈራርቆበታል። እሾህ፣ ጠጠርና ጭቃ እንደ እግር የሚጠቀማቸውን እጆቹን ጎድተውታል። ከማህበረሰቡ መገለል፣ መድሎ፣ ተሰፋ እስቆራጭ ንግግሮች ተፈታትነውታል። በለጠን ግን ከአካል ጉዳተኝነቱ ጋር ይህ ሁሉ መከራ ታክሎበት ቢሆን የልጅነቱ ህልሙ ምን ከመኖር አላገደውም።
በለጠ የአንደኛ ክፍል ትምህርቱን በብዙ ፈተና ሹሮ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አጠናቆ የተሻለ ሕይወትና ትምህርት በመሻት ወደ አርቤጎና ወረዳ አሰተዳደር መቀመጫ ወደ ሆነቺው Yayye (ያዬ) አቀና። ያዬ ከፊዴ ፎሊሾ (ከነበለጠ ገጠር) 14 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች። በለጠ ከ2-8 ክፍል ቁኒቻ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት፣ ከ9-12 አርቤጎና ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተምሯል። ያዬ ከተማም ከአዲስ አበባ ከተማ እኩል የቆረቆረች ዕድሜ ጠገብ የደጋ ሀገር ከተማ ብትሆንም ለአካል ጉዳተኛ የሚመች መሠረተ ልማት የላትም። የተፈጥሮ በረከቷ እንደተጠበቀ ሆኖ ቅዝቃዜ፣ ዝናብ፣ ጭቃ የተለመደ ነው። በመሆኑም በለጠን ሕይወቱን በከተማ ቢያደርግም ፈተናዎቹ እልፍ ነበሩ።
በሌ ያዬ ከተማ ገብቶ ሦስተኛ ክፍል እስክደርስ በባዶ እጆቹ ነበር የሚራመደው። ልብ በሉ በባዶ እግሩ ሳይሆን በባዶ እጆቹ። ለእጁ የመጀመሪያ ነጠላ ጫማ ሦስተኛ ክፍል ደርሶ ነበር ማድረግ የቻው። የያዬ ከተማ ጭቃና ፒስታ መንገድ አይደለም ነጠላ ጫማ ጫማም አይችለውም። በለጠ በእጆቹ ከመራመድ ነጠላ ጫማ ማድረጉ ከጠጠርና እሾህ ሰቃይ ትንሽ ያሽለው ቢሆን እንጂ ዘላቂ መፍትሄ አልሆነለትም።
በለጠ ሰባተኛ ክፍል ደርሶ ከነጠላ ጫማ ወደ ሸበጥ ጫማ ከፍ ማለት ቻለ። በለጠ ለመማር ያለውን ጥረትና ከሰዎች ጋር በጣም ተግባቢ መሆኑን በዚያን ጊዜ ያዬ ከተማ የግል ክሊኒክ የነበረው አቶ ካሣ ካዬሶ ዊልቼር አምጥቶ እንደ ሰጠው ይናገራል። ያዬ ከተማ በዛ የጠጠር መንገድ፣ በዚያ ጭቃ እንዴት ይንዳው? ማንስ ይግፋው? በለጠ ተማሪዎች እየገፉት ለጥቂት ጊዜ ሕይወትን በዊልቼር ሞከረው። የአየር ፀባዩና የመሠረተ ልማት ችግር ሌላ ፈተና ሆኖበት ዊልቼሩን በመተው ወደ ሸበጥ ጫማው ተመለሰ።
በለጠ በክረምትና አንገብጋቢ ማህበራዊ ጉዳዮች ሲገጥሙት ከያዬ ፊዴ ፎሊሾ አንዳንዴ በፈረሰ፣ ሌላ ጊዜ ሰው ተሸክሞት ተመላልሷል። በአንድ ወቅት ከፊዴ ፎሊሾ እሰከ ያዬ ከቤት ከለሊቱ 11:00 ተነስቶ ከምሽቱ 1:00 ( ከ12 ሰዓታት) በላይ በእጆቹ ተጉዞ እንደደረሰ ያስታውሳል። በለጠ የጥንካሬው ጥግ፣ ለአካል ጉዳተኝነትና እሱን ተከትሎ ለሚገጥሙ ፈተናዎች ሁሉ እጅ ያለመሰጠት ልክ፣ የመንፈሰ ብርታቱ መጠን የሚደንቅ ወጣት ነው። በእውነቱ በዛ ገጠር፣ በዛ ማህበረሰብ ውሰጥ አካል ጉዳተኛ ሆኖ ተወልዶ እንደ በለጠ ለመሆን የሚታሰብ አይደለም። እሱ ግን መሆን የሚፈልገውን በእግዚአብሔር ኃይል ሆኖ አሳየ። ይደንቃል።
በለጠ የአሥራ ሁለተኛ ክፍል ካጠናቀቀ በኋላ በ2012 ሐዋሳ ዩኒቨርስቲ በኤክስቴንሽን የትምህርት መርሃግብር በማኔጅመንት ትምህርት ክፍል የመጀመሪያ ድግሪ ትምህርቱን ጀመረ። ላለፉት 5 ዓመታት ኑሮውን በሐዋሳ ዩኒቨርስቲ በማድረግ፣ የማደሪያና የምግብ ድጋፍ ከዩኒቨርሲቲው በማግኘት ከምንም በላይ በእግዚአብሔር አቅም ጉልበት ሆኖለት ትምህርቱን ማጠናቀቅ ችሎዋል።
በለጠ ምንም እንኳን አካል ጉዳተኛ ቢሆንም ሥነ ልቦናው ጠንካራ ነው። በራሰ መተማመኑ ከፍ ያለ ነው። ባህሪው ከሰዎች ጋር ቶሎ ተግባቢ፣ በግል ሕይቱ ዘናጭና ንፅህናን የሚወድ በጣም አራዳ ነው። በሌ የዋዛ አይምሰላችሁ። መብቱን ለማሰከበር ከማንም ጋር ከመጋፈጥ ወደ ኋላ የማይል ቆራጥ ተሟጋች ነው። የሲዳማን ሀዮ (መላ) ያውቅበታል። ንቃተ ህሊናው የላቀ ነው። ሰው ሁሉ የሚደነቅበት ወጣት ነው። በለጠ የራሱ ብቻ አይደለም። ለማህበረሰቡ መብትና ጥቅም ጥብቅና ለመቆም አንደኛ ነው። በሌ ማህበራዊ ሕይወቱ ጠንካራ ነው። የታመመውን ሆስፒታል፣ የታሠረውን ማረሚያ ሄዶ ይጠይቃል። ለቅሶና ቀብር ቀድሞ ይደርሳል። በለጠ (ያምቡሌ) የስፖርት አፍቃሪ ነው። በአካል ጉዳተኞች ስፖርት በአትሌቲክስ ዘርፍ የቀድሞ ደቡብ ክልል በመወከል በልዩ ልዩ ዘርፎች ሜዳሊያ ተሸላሚም ነበር። በለጠ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ቀንደኛ ደጋፊም ነው። በለጠ "አካል ጉዳተኛ አካሉ ቢጎዳም አሰተሳሰቡና ልቡ ጤናማ እሰከሆነ | 375 |
| 5 | እንኳን አደረሳችሁ፤ አደረሰን! | 410 |
| 6 | የንግግር ህክምና
የንግግር ህክምናን በተመለከተ በህብረተሰቡ ዘንድ የተሳሳተ አረዳድ መኖሩ ይነገራል፡፡ ይህም የንግግር ህክምና የምክር አገልግሎት መስጠት ነው የሚል እሳቤ ነው፡፡
የምክር አገልግሎት ለአእምሮ እክል ወይም ህመም የሚሰጥ ቢሆንም የንግግር ህክምና ነው ማለት አለመሆኑም ይገለጻል፡፡
በንግግር ህክምና የአይምሮ እክል ያጋጠመውን ታካሚ የልጅነት ጊዜ አስተዳደግን የሚመረምር እና ያጋጠመውን ችግር ከስር ከመሰረቱ የሚያጤን ሲሆን፤ ታካሚው የችግሩን መንስኤ እንዲገነዘብ የሚረዳ የህክምና መንገድ ነው፡፡
በዚህ የህክምና ሂደት ላይ ታካሚዎች የሚሰማቸውን የውስጥ ሀዘን፣ ንዴት፣ ሃሳባቸውን እና ያለፉበትን መልካም ሆነ መጥፎ አጋጣሚዎችን በነጻነት የሚናገሩ ሲሆን፤ ባለሞያው ችግሩን በትኩረት በመረዳት የትኛው ጉዳይ በህይወታቸው ላይ ተጽዕኖን ሊያሳድር እንደሚችል እና ህመሙ ሚታከምበትን ሁኔታ የሚመረምር ይሆናል፡፡
የህክምና ሂደቱ በባለሞያው እና በታካሚው መካከል የሚካሄድ በመሆኑ የታካሚው ሚስጥር እንዲጠበቅ ያደርጋል፡፡
የንግግር ህክምና፦ ለጭንቀት፣ ድባቴ እና መሰል አእምሮ እክሎች የንግግር ህክምናን እንደ መጀመሪያ የህክምና ሂደት የሚሰጥ ነው። እንዲሁም ድንገተኛ ሃዘን ሲያጋጥም፣ ከአደጋ በኋላ የሚከሰት የአይምሮ እክልን፣ በትዳር ህይወት የሚያጋጥሙ ግጭቶችን፣ ለሱስ ለተጋለጡ ሰዎች፣ አረዳድ እና ባህሪን ለማረቅ፣ ጠባሳ ሆነው የቀጠሉትን በልጅነት ጊዜ የተከሰቱ መጥፎ የህይወት አጋጣሚዎችን ለማከም የሚሰጥ ነው።
በልጅትነት ጊዜያት ላይ የሚያልፉ ጥሩም ሆኑ መጥፎ የህይወት ክስተቶች ለሰዎች የወደፊት ህይወት እና ስነልቦና ላይ ከፍተኛ ጫና ያሳድራሉ፡፡
በመሆኑም ወላጆች ወይም አሳዳጊዎች ልጆቻቸው የሚናገሩት ንግግር የተገራ፣ የሚተገብሯቸው ድርጊትች የተቆጠቡ ሊሆኑ ይገባል፡፡ ምክንያቱም የብዙዎች የአእምሮ እክሎች በልጅነት ጊዚያት ላይ በሚፈጠሩ መጥፎ ጠባሳዎችን ተከትሎ የሚከሰቱ ናቸው።
የሰዎች አሉታዊ ንግግር በሌሎች ላይ ለበታችነት ስሜት፣ ምንም ማድረግ አልችልም ብሎ ለማሰብ እና አንዳንዴም ከልክ በላይ ለራስ ክብርን መስጠት ሊያጋልጥ በመቻሉ፤ አንደበት ሊታረም እና ለሰዎች አይምሮ መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡
የንግግር ህክምና ውጤታማ ነው። በማህበረሰቡ ዘንድ የተለመደው የተሳሳተ አረዳደድ ሊታረም ይገባል እና ሰዎች የሚያስጨንቃቸውን እና የሚያጋጥማቸውን መጥፎ የህይወት ክስተቶችን ከባለሞያ ጋር በመነጋገር የአእምሮ ጤናቸውን መጠበቅ ይችላሉ፡፡
ህክምናው በዋናነት በልጅነት የእድሜ ክልል ያጋጠሙ ሁኔታዎችን የሚያስታውስ፣ የትኛው የህይወት ገጠመኝ የሰዎችን ስነልቦና እና የዕለት ተዕለት ህይወት ላይ ጫና የሚያሳድሩ መንስዔዎችን የሚመረምር በመሆኑ በወላጅ አልያም በአሳዳጊዎች ዘንድ ከታች የተዘረዘሩት ቢለመዱ ጥሩ ነው።
በተቻለ መጠን ቁጡ አለመሆን፣ የልጆች ባህሪ ላይ መስራት፣ ከቁስ በተጨማሪ ፍቅርን ለልጆች መስጠት እና ልጆች የሚተማመኑበት ወላጅ መሆን አስፈላጊ ነው፡፡
ምንጭ ፦ ዶ/ር እስጢፋኖስ እንዳላማው (የአዕምሮ ህክምና ስፔሻሊስት)
በፌስቡክ ያግኙን
https://www.facebook.com/snieet | 461 |
| 7 | ድንገተኛ የመረበሽ ስሜት እና ህመም - Panic attack and Panic disorder
🔹 መንገድ እየተሻገርን ነው ድንገት በፍጥነት መኪና ቢመጣብን፤ የተሳፈርንበት መኪና ከሌላ መኪና ሊጋጭ ሲል የሚገጥመንን ስሜት አስታዉሱ፡፡ ለእንደዚህ አይነት እዉነተኛ አደጋዎች አእምሮአችን ቅጽበታዊ ምላሽ በመሰነድ አድሪናሊን የተባለ ንጥረ-ቅመም እንዲመነጭ ያደርጋል፡፡ ይህም ሩጠን እንድንሸሽ ብሎም ቅጽበታዊ ምላሽ እንድንሰጥ ያደርጋል፡፡
🔹 አንዳንዴ በተለያየ ምክንያቶች አእምሮአችን ተጨባጭ አደጋዎች በሌሉበት ሁኔታ መደንገጥ ለሌለብን ነገሮች ነገሮች ጭምር የተሳሳተ አተረጉዋጎም በመስጠት አድሪናሊን እንዲመነጭ ያደርጋል፡፡
🔹ይህም ከፍተኛ መረበሽ ስሜትስሜት ውስጥ እንድንገባ ያደርገናል፡፡ ይህ ክስተት panic attack ይባላል፡፡
🔸ፓኒክ አታክ ድንገቴ የሆነ የመረበሽ ስሜት ሲሆን: በይሆናል ለታሰበ ጭንቅ ፈጣሪ ሁነት የሚሰጥ የተጋነነ አእምሯዊ እና አካላዊ ስሜት ነው::
🔸ይህ የመሸበር ስሜት በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ጣራ የሚነካ እና በደቂቃዎች ውስጥ የሚጠፋ ነው፡፡
🔸 በዚህ ድንገቴ የመረበሽ ወቅት ሰውነታችን ሊያሳያቸው የሚችሉ 13 ገደማ ምልክቶች አሉ::
🔸 ከነዚህ ምልክቶች 11ያህሉ አካላዊ ቀሪ ሁለቶቹ ደሞ አእምሯዊ ምልክቶች ናቸው::
ምልክቶቹ:-
1️⃣ልባችን በሃይል መምታት: ልብ በሃይል ስትመታ መታወቅ፣
2️⃣ ማላብ፣
3️⃣ ማንቀጥቀጥ፣
4️⃣ ትንፋሽ ማጠር፣
5️⃣አንገታችን የመታነቅ ስሜት መሰማት፣
6️⃣ ደረት አካበቢ ምችት መንሳት፣
7️⃣ማጥወልወል ወይንም የሆድ ምቾት መንሳት፣
8️⃣የማዞር: የድንግዝግዝ ስሜት: መንገዳገድ: ወይንም ራስን መሳት፣
9️⃣ብርድ ብርድ ወይንም ሙቀት ሙቀት ማለት፣
10. የእጅና እና እግር መደንዘዝ ወይንም መቆጥቆጥ፣
11. ለራስ ወይንም ለከባቢ የእንግድነት ስሜት መሰማት፣
12. ከቁጥጥር ውጭ የሆኑ ያህል ወይንም ወደ እብደት የሄዱ ያህል መሰማት፣
13. ሊሞቱ ወይንም ነብሳቸው ልትወጣ የደረሰች ያህል መሰማት::
🔹አንድ ሰው ፓኒክ አታክ አጋጠመው ለማለት ከ 13 ምልክቶች ቢያንስ አራቱን ማሟላት ይኖርበታል::
🔹 እነዚህ ምልክቶች ካለምንም አባባሽ ሁኔታዎች አልያም በተለያዩ አባባሽ ምክንያቶች ጋር ተያይዘው ሊከሰቱ ይችላሉ::
✅ አባባሽ ምክንያቶች:
*ሰው የተሰባሰበበት ቦታ የሚከሰቱ ( Social Anxiety Disorder with panic attack specifier)
: ከሚፈሩት ነገር ጋር ሲጋፈጡ (በspecific phobia with panic attack specifier)
: ድህረ አደጋ አደጋውን ለሚያስታውሱ ሁነቶች ሲጋለጡ (Post traumatic stress disorder with panic attack specifier)
* የታወቀ ህመም ካለባቸው ህመሙ በራሱ የሚያመጣቸው የፓኒክ አታክ ምልክቶች (አስም: የእንቅርት ህመም: የልብና የመተንፈሻ አካል ህመሞች) መድሃኒቶች: እጾች (ቡና ጫት እና ሌሎች አነቃቂ ንጥረ ነገሮች)
🟫 Panic Disorder-
✔ ከአንድ በላይ ፓኒክ አታኮች ካለምንም ቅድመ አባባሽ ሁነት ሲከሰቱ:
✔ ይህንም ተከትሎ ድጋሚ ፓኒክ አታክ እንዳይከሰት ወይንም ስለ ፓኒክ አታኩ ጦስ አብዝቶ መጨነቅ ወይንም ፓኒክ አታኩን ሊያመጡ ይችላሉ ተብለው ከታሰቡ ነገሮችን ለመራቅ መሞከር ሲኖራቸው:
✔ ፓኒክ አታኮቹ በመድሃኒት: በእጾች ወይንም በህመሞች ምክንያት እንዳልተከሰቱ ሲረጋገጥ:
✔ ከሌሎች የአእምሮ ህመሞች ጋር ተያይዞ እንዳልተከሰተ መረጋገጥ ሲችል ፓኒክ ዲሶርደርን ማሰብ ይቻላል::
🛑 ህክምናው:-
🔹መድሃኒቶች:- ጸረ ጭንቀት መድሃኒቶች
🔹 የስነ ልቡና ህክምናዎች
Cognitive behavioral therapy
• ይህ ህመም ያጋጠማቸው ሰዎች አካላዊ ምልክቶቻቸውን የማጉላትና የመጥፎ ነገር ማሳያዎች እድረገው መሳላቸው የበለጠ ለጭንቀት እንደሚዳርጋቸው ይታመናል::
• ስለዚህም ነገሮችን ባላስፈላጊ ሁኔታ የማጉላትና የማወሳሰብ እና ሌሎች ጠቃሚ ያልሆኑ አስተሳሰቦችን በመለየት የማሻሻል ሂደት አንዱ የህክምናዉ አላማው ነው::
• ሌላው ባህርይን መሰረት ያደረገ (ገና ለገና ነገሮች ፓኒክ አታክ ያመጡብናል ብለው ያሰባቸውን ሁነቶች በተጋነነ ሁኔታ ለመራቅ የሚያደርጉትን ሙከራ እንዲያሻሽሉ: እነዚህ የሚፈሯቸው ነገሮች በርግጥም የታሰበውን ምልክት እንደማያስከስቱ እንዲረዱ ለነገሮች እና ሁኔታዎችን እንዲጋፈጡ በማድረግ : አየር ወደውስጥ እያስገቡና እያስወጡ ሰውነትን ከመረበሽ ስሜት የማስወጣት መንገዶችንና መሰል ራስን የማረጋግያ መንገዶችን እንዲጠቀሙ በማድረግ::
ማጠቃለያ
• ፓኒክ አታክ እና ዲሶርደር መታከም የሚችል ህመም ነውና እነዚህ ምልክቶች ሲሰሙን የስነ-አእምሮ ባለሞያን መማከር ብልህነት ነው፡፡
ዶ/ር እስጢፋኖስ
https://www.facebook.com/snieet | 811 |
| 8 | ጥቁር አዝሙድ ለጤናችን የሚሰጠን አስደናቂ ጥቅሞች!
በጥቁር አዝሙድ ውስጥ ለሰው ልጅ ጠቃሚ የሆኑ ከ100 በላይ የተለያዩ የኬሚካል ንጥረ ነገሮች አሉ። እንደ ካልሲየም፣ ፖታሲየም፣ ብረት፣ ዚንክ፣ ማግኒዥየም፣ ሲኒየም፣ ቫይታሚን ኤ፣ ቫይታሚንቢ፣ ቫይታሚን ቢ2ና ሲ የመሳሰሉት መገኛ ነው።
የአለርጂ በሽተኞች አሉታዊ ምልክቶችን ለመቀነስ የሚረዳ እንደ ፀረ-ሂስታሚን በውስጡ ይዟል።መርዛማ ንጥረ ነገሮችን ከሰውነት ለማፅዳት ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
ለስኳር በሽታ የኢንሱሊን መጠንን ለመቆጣጠር፣ ኮሌስትሮልን፣ የሰውነት ዝውውርን ያሻሽላል እንዲሁም ጤናማ የጉበት ሥራን ያበረታታሉ።
ደረቅ ሳልን ለማስታገስ ከቡና ጋር ቀላቅሎ መጠጣት ከፍተኛ የሆነ ጠቀሜታ አለው፣ የፊት መሸብሸብንና ቴታነስን ለመከላከል ጥ/አዝሙድን ከሞቀ ውሃ ጋር ቀላቅሎ መጠቀም ይመከራል።
እንደ ሣል፣ ትኩሳት፣ አስም፣ የቆዳ ሽፍታ፣ እብጠትና የሆድ ድርቀትን ለማከም አገልግሎት ላይ ይውላል።
የፀጉር መሳሳትና መላጣነትን ይከላከላል፣ የአይን ኢንፌክሽን፣ ህመምና ደካማ እይታን ለመከላከል ዘይቱ ይጠቅማል።
በተበከለ ምግብ አማካኝነት የሚከሰትን ድንገተኛ ትውከትን ለማስቆም ይረዳል፣ የጥርስ ህመምን ለማስታገስ ግማሽ የሻይ ማንኪያ የጥቁር አዝሙድ ዘይት ከሙቅ ውሃ ጋር ቀላቅሎ በተጎዳው ጥርስ ላይ በማፍሰስ ህመምን ማስታገስ ይቻላል።
የደም ግፊትን በጣም ይቀንሳል። ዘይቱ ጸረ-አልባሳት ባህሪዎች የደም ግፊትንና ሌሎች የልብና የደም ቧንቧ በሽታዎችን ለማከም ጥቅም ላይ ይውላል።
በማንኛውም የሰውነት ክፍል ላይ አደገኛ የሆኑ ዕጢዎች መፈጠርን ይከላከላል፣ ለሴቶች የወር አበባ ፍሰትና እንቅስቃሴን ያበረታታል።
ምንጭ፦ ኢትዮ መረጃ | 321 |
| 9 | download.webp | 321 |
| 10 | ከ78 ሚሊየን ብር በሚልቅ ወጪ የብሬል መጽሐፍትን እያሳተምኩ ነው – የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ
የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ከ78 ሚሊየን ብር በሚልቅ ወጪ ለአይነስውራን መማሪያና ማስተማሪያ የሚሆኑ የብሬል መጽሐፍን እያሳተመ መሆኑን አስታወቀ፡፡
መጽሐፍቱ በበጀት ዓመቱ ከ5ኛ እስከ 8ኛ ክፍል ለሚማሩ አይነስውራን መማሪያና ማስተማሪያ የሚውሉ መሆናቸው ተጠቅሷል፡፡
በአዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት የተዘጋጀው የብሬል መጽሐፍ ለአይነ ስውራን ተማሪዎች ውጤታማነት ጉልህ ድርሻ እንዳለው መገለጹን የክልሉ ትምህርት ቢሮ መረጃ አመላክቷል፡፡
ለአብነትም ተማሪዎቹ የብሬል ንባብ ክኅሎታቸውን እንዲያዳብሩ፣ በቀላሉ አንብበው እንዲረዱ፣ የቤት ሥራም ሆነ የክፍል ሥራ ከመጽሐፉ በቀላሉ እንዲሠሩ ከማገዝ ባለፈ ፍትሐዊነትንና የትምህርት ጥራትን እንደሚያረጋግጥ ተመላክቷል፡፡
ምንጭ፦ FBC | 324 |
| 11 | "ልጆች ስክሪን ላይ የሚያሳልፉት እያንዳንዱ ደቂቃ እድገታቸው ላይ ተፅዕኖ አለው።" አዲስ ጥናት
ስማርት ስልክ፣ ቴሌቪዥን እና ሌሎች ስክሪን ነክ ቁሶች የህፃናት ማባበያና ማጫወቻ መሆን ከጀመሩ ሰነባብተዋል።
በአውስትራሊያ ሀገር አዲስ የተሰራ ጥናት እንዳመለከተው እድሜያቸው ከ 18-36 ወራት ያሉ ህፃናት ስክሪን ላይ የሚያሳልፉት ጊዜ ከቤተሰብ ጋር የሚኖራቸውን ጊዜ ይቀንሰዋል፤ይህም የቋንቋ እድገታቸውን ይገድበዋል።
ተመራማሪዎቹ በጥናቱ ውስጥ የተካተቱትን ቤቶች በዘመናዊ የንግግር መለያ ቴክኖሎጂ በመጠቀም በቤት ውስጥ ያለውን የንግግር ጊዜ እና የስክሪን አጠቃቀም ክትትል አድርገዋል።
የህፃናቱ ጾታ፣ የእናት የትምህርት ደረጃ እንዲሁም ያሳዳጊዎች የአዕምሮ ሁኔታ በጥናቱ ከግምት የገቡ ጉዳዮች ናቸው።
በጥናቱ ውጤት መሰረት እያንዳንዱ ተጨማሪ ደቂቃ የስክሪን ላይ ቆይታ በ ሶስት አመታቸው መስማት ከሚገባቸው አዋቂዎች ከሚያወሯቸው ቃላት በደቂቃ ሰባት ያህል ያነሰ ቃላት እንዲሰሙ፣ በአምስት ያህል ያነሱ ድምፀቶችን እንዲሰሙ እንዲሁም በየደቂቃው የሚያደርጓቸው የእርስ በእርስ ንግግሮች በ አንድ ቀንሶ ተገኝቷል።
የህፃናት እድገት ከፍተኛ ጥንቃቄ ይፈልጋል፤ የሚያስፈልጋቸውን ብቻ መስጠት ብልህነት ነው።
ምንጭ፦ ዶ/ር መክብብ ካሳ | 596 |
| 12 | 没有文字... | 387 |
| 13 | ዛሬ የአለም ዳውን ሲንድረም ቀን ነው - ዳውን ሲንድረም ያለባቸውን ሰዎች ሁሉ (በተለምዶ የሚከሰት የክሮሞሶም ሁኔታ) ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያለመ ነው✨
በተለምዶ አንድ ሕፃን ከእያንዳንዱ ወላጅ የተገኘ 46 ክሮሞሶም ማለትም 23 ጥንድ ክሮሞሶም ይኖረዋል። ዳውን ሲንድረም ያለባቸው ሕፃናት ከእነዚህ ክሮሞሶም 21ኛዋ ክሮሞሶም ውስጥ ተጨማሪ ቅጂ/copy ሆና 47 ክሮሞሶም አላቸው። የዓለም ዳውን ሲንድረም ቀን በየዓመቱ በፈረንጆች መጋቢት 21 ቀን ይከበራል። ይህም 21ኛውን ክሮሞሶም ለማሰብ ነው።
በዚህ የአለም ዳውን ሲንድረም ቀን ዳውን ሲንድሮም ያለባቸውን ሰዎች እስከ ልዩ ችሎታዎቻቸው ጋር እናክብር፣ እናካትት። ዳውን ሲንድረም ያለባቸውን ሰዎች ጨምሮ እያንዳንዱ ሰው ክብር፣ ፍቅርና አገልግሎት ይገባዋል☺️
#World_Down_Syndrome_Day
#inclusion
#Respect | 629 |
| 14 | ልዩነትን መቀበል እና ልዩነትን ዛሬ እና በየቀኑ ማክበር። 💙 መልካም የአለም አቀፍ ዳውን ሲንድሮም ቀን! ዳውን ሲንድሮም ላለባቸው ግለሰቦች እንዲካተቱ፣ እንዲታገዙ እና እንዲቀበሉ መሟገታችንን እንቀጥል። #የአለም ዳውን ሲንድሮም ቀን #ማካተት #ልዩነት #ተቀባይነት
Embracing uniqueness and celebrating diversity today and every day. 💙 Happy World Down Syndrome Day! Let’s continue to advocate for inclusion, understanding, and acceptance for individuals with Down syndrome. #WorldDownSyndromeDay #Inclusion #Diversity #Acceptance
Diborah Foundation | 357 |
| 15 | ቅናት እና የአእምሮ ጤናችን በሳይኮሎጂ እይታ!
ቅናት መጠኑ ይለያይ እንጂ በአብዛኛው ሰው ላይ የሚታይ ባህርይ ነው፡፡ እኛ ሰዎች በሁለቱም ማለትም ባለንም በሌለንም ቁሳዊም ሆነ ስነ-ልቡናዊ ጥቅሞች ባላቸው ነገሮች ላይ እንቀናለን፡፡ በሌለን ነገር ላይ የምንቀናው ቅናት ሰዎች የሚፈልግቱንና እኛ የሌለንን ሲያገኙ፣ ሲያሳኩ ወይም የሚያሳኩበትን የተስተካከለ መስመር ሲይዙ የሚሰማን ምቾት የማጣት ስሜት ሲሆን፤ ባለን ነገር ላይ ቅናት ማለት ደግሞ ሌሎች እኛ ያለንን ቁሳዊ አካል ወይም የስሜት ግኙነት የመሰረትንበትን ሰው ሊያሳጧችሁ የሚመስል መጥፎ ስሜት በውስጣችሁ ሲፈጠር ነው፡፡
#ለምሳሌ የፍቅር አጋርህን ሌላ ወንድ ሲያናግራት ብታይ እና ሰላም የማጣት ስሜት ሲሰማህ ቅናት ተስተዋለብህ ማለት ነው፡፡
ቅናት ገደቡን ካለፈ በእኛም ላይ ሆነ በሌሎች ሰዎች ላይ ስነ ልቡናዊ እና አካላዊ ጉዳቶችን ይፈጥራሉ፡፡ ሆኖም ግን ቅናትን በበጎ መልኩ የምንጠቀምበት ከሆነ መልካም የሆነ ግንኙነትና እኛ ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በመሙላት ወደተሻለ ደረጃ ወይም የምንቀናባቸው ሰዎች ወዳሉበት የስኬት ማማ ላይ ለመድረስ መንገዱን ይጠርግልናል፡፡
🔹 ከላይ እንደተገለጸው ቅናት የተለያዩ ስነ-ልቡናዊ እና አካላዊ ጉዳቶችን ያስከትላል ከእነዚህም መሀከል፡-
▸ ቅናት ቤተሰብን ይበትናል
▸ ፍቅረኞችን ያለያያል
▸ የስራ ባልደረቦችን ያጋጫል
▸ ሰላማዊውን የሰው ልጆች መስተጋብር ያፋልሳል
▸ ባስም ሲል ቅናት ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ህይወትን ያስጠፋል
🔹ስለዚህ መፍትሔው ምንድን ነው?
► በጾታዊ ፍቅር ምክንያት ከሆነ ቅናት የሚይዘን በግልጽ መነጋገር፦ ማስተዋል ያለብን ቀንቻለው ማለት የተሸናፊነት ምልክት ሳይሆን ግንኙነቱን ዘላቂና ሰላማዊ ማድረግ እፈልጋለሁ ማለት እደሆነ ነው፡፡
► መተማመን በፍቅር ግንኙነት ውስጥ ዋናው የግንኙነት መሰረቱ መተማመን ነው፦ መተማመን የሌለው ጾታዊ ፍቅርም ለቅናት የተጋለጠ ነው፡፡ እሱ የሌለው እኛ ግን ያለን ሌሎች ነገሮችም እንዳሉ መገንዘብ፡፡
► ሁልጊዜ ራስህን በጥረት ውስጥ ማሳለፍ ይኖርብሃል፦ ምክንያቱም የቻልከውን ያህል ስለታተርክ በቅናት ፋንታ እርካታን ታገኝበታለህ፡፡
► ከምንቀናባቸው ሰዎች ልምድ መቅሰም አለብን፦ ይህም ማለት የቀናህበትን ነጥብ ነቅሰህ አውጣ በዚህም አንተ ማግኘት ያቃተህ ሌሎች ግን ያሳኩት ከሆነ እንዴት እንዳሳኩት በማወቅ ራስህን እንድታሻሽል ይረዳሀል፡፡
► ሌሎች ሰዎች ላይ እና ያላቸው ነገሮች ላይ ያለህን ፅንፍ የያዘ ትኩረትህን ቀንስ፦ ምክንያቱም የአዕምሮህን የትኩረት አቅጣጫ በማስቀየር አቅምህን ያዳክማል፡፡
► ስለሌለህ ሳይሆን ስላለህ ነገር በማሰብ ለእራስህ እውቅና ስጥ በዚህም በጊዜ ሂደት በራስ መተማመንን አዳብረህ ቅናትን ታስወግዳለህ፡፡ | 461 |
| 16 | የስነ ልቦና ታካሚዎች ቁጥር መጨመሩን የአማኑኤል ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አስታውቋል።
የሆስፒታሉ የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አብዩ የኔአለም ለትርታ እንደገለጹት፡ ባለፉት ሶስት ወራት የተመዘገበው የስነ ልቦና ታካሚዎች ቁጥር ሆስፒታሉ ከያዘው እቅድ በላይ ነው።
ሆስፒታሉ ባለፉት በሶስት ወራት 400 ታካሚዎችን ለማስተናገድ አቅዶ፣ 833 ታካሚዎች አገልግሎቱን ማግኘታቸውን ነው ያስታወቁት። በኢትዮጲያ ባለው ነባራዊ የፖለቲካ ውጥረት፣ የኑሮ ውድነት፣ የሰላም እጦት እና በሌሎችም ገፊ ምክንያቶች ሳቢያ ታካሚዎች የስነ ልቦና ህክምና አገልግሎት ለማግኘት ወደ ተቋሙ መምጣታቸውን ገልጸዋል።
የዘንድሮው የህክምና አፈጸጸም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸርም ከፍተኛ የአሀዝ ልዩነት እንዳለው ነው ያስታወሱት። በ2015 በጀት ዓመት በሩብ ዓመቱ ለ875 ታካሚዎች ህክምና ለመስጠት ታቅዶ አገልግሎት ለማግኘት የመጡ ታካሚዎች ብዛት 726 እንደሆነና ይህም 83% በመቶ መሆኑን አመላክተዋል፡፡
በኢትዮጵያ ሰላማዊ የዕለት ተለት ህይወትን መምራት የሚችሉበት ሁኔታ ካልተፈጠረ፣ የስነ ልቦና ጉዳት የሚገጥማቸው ዜጎች ቁጥር መጨመሩ የማይቀር እንደሆነ ነው የአማኑኤል ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አብዩ የኔአለም ለትርታ የተናገሩት።
Via: ትርታ ኤፍ ኤም | 619 |
| 17 | 没有文字... | 863 |
| 18 | ዛሬ እሁድ ህዳር 23/December 3 አለም አቀፍ የአካል ጉዳተኞች ቀን በአለማችን ለ32ኛ ጊዜ በሀገራችን ደግሞ ለ31ኛ ጊዜ እየተከበረ ይገኛል።
መሪ ቃሉም «ለአካል ጉዳተኞች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እና ለዘላቂ የልማት ግቦች ስኬት - ትርጉም ያለው ትብብር» የሚል ነው።
ይህ በየዓመቱ የሚከበረው የአካል ጉዳተኞች ቀን የአካል ጉዳተኞችን መብቶችና ተሳታፊነት መሰረት ያደረገ ሲሆን ከበፊቱ የተሻለ የግንዛቤ ሥራና እንቅስቃሴ ተደርጎ በሁሉም ዘርፎች አካታች እንዲሆኑ ያስችላል። | 1 381 |
| 19 | ጃንሆይ በሰበታ የሚገኘውን የመጀመሪያ የአይነስውራን የብሬል ትምህርት ቤትን በ1957 ዓም ሲመሰርቱ። | 886 |
