ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 369 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 753,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 530

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 369 名订阅者。

根据 20 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 129,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.47%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.24% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 143 次浏览,首日通常累积 2 037 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 21 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 373
订阅者
+824 小时
+697
+12930
帖子存档
ከ3ነጥብ6 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚደረግለት የደብረብርሃን -ደነባ -ለሚ መገንጠያ እና ጅሁር-ደነባ የመንገድ ፕሮጀክት ዛሬ ምክትል ጠቅላይ ሚንስትር ደመቀ መኮንን በተገኙበት በይፋ ተጀመረ ። 108 ነጥብ 26 ኪ.ሜትር ርዝመት የሚሸፍነው የደብረብርሃን -ደነባ -ለሚ መገንጠያ እና ጅሁር-ደነባ የመንገድ ፕሮጀክት ሀገራዊ ፋይዳው የላቀ መሆኑን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። የፕሮጀክቱን የግንባታ ወጪ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል ፡፡ ይህንኑ የደብረብርሃን -ደነባ -ለሚ መገንጠያ እና ጅሁር-ደነባ የመንገድ ፕሮጀክን የሚያከናውነው አገር በቀሉ ሰንሻይን የስራ ተቋራጭ ነው። የደብረብርሃን -ደነባ -ለሚ መገንጠያ እና ጅሁር-ደነባ መንገድ ፕሮጀክት የጎን ስፋት በዞን 36.7 ሜትር በቀበሌ 12 ሜትር በወረዳ 19.45 ሲሆን በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 1ዐ ሜትር ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ግንባታ የአራት ድልድዮችን ስራ የተለያዩ ፉካዎችን የሚያካትት ይሆናል። በኮንትራት ውሉ መሰረት ግንባታው በአራት አመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ። በርካታ ትርፍ አምራች አካባቢዎችን እና ወረዳዎችን የሚያስተሳስረው ይህ መንገድ ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት ያልተዘረጋበትና በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ ነው። መንገዱ ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንፃር በአሁኑ ወቅት ደረጃው ወደ አስፋልት ኮንክሪት በማሳደግ የሚገነባ ይሆናል። በመርሃ ግብሩ ላይ የመንገድ ኘሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ እና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ በአካባቢው የሚገኙ የመስተዳድር አካላት፣ የክልሉ ነዋሪዎች ከፍተኛ ትብብር እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ዋና ዳሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኝ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የብልጽግና ፖርቲ ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ብናልፍ አንዱአለምን ጨምሮ በርካታ የመንግስት የስራ ሃላፊዎችም ታድመዋል።

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን ከ25 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተለያዩ የሃገሪቱን አካባቢዎች የሚያስተሳስሩ አስራ አምስት መንገዶችን በአስፋልት ደረጃ ለመገንባት የሚያስችል የውል ስምምነት ፊርማ ዛሬ አካሄደ። ስምምነቱን በኢመባ መሰብሰቢያ አዳራሽ የተቋሙ የስራ ሃላፊዎች፣የሕዝብ ተወካይ ም/ቤት አባላት እንዲሁም መንገዱ ከሚገነባባቸው አካባቢዎች የተወከሉ የአገር ሽማግሌዎችና የአስተዳደር አካላት በታደሙበት ነው የተከናወነው። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ በመረሀ ግብሩ ላይ እንደተናገሩት ከፍተኛ ህዝባዊ ጥያቄ ይነሳባቸው ከነበሩትን መንገዶች መካከል ወደ ግንባታ ለመሸጋገር በመብቃታቸው ለአገራችን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚያበረክቱ ት አስተዋፅዖ ከፍ ያለ በመሆናቸው እንኳን ደስ አለን!የሚል መልዕክትን አስተላልፈዋል። ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በቀጣይም መንግስት የያዘውን የለውጥ ጎዳና ወደ ስኬት እንዲያመራ ከፍተኛ በጀትን በመጠየቅ የህዝብ ጥያቄዎችን መመለሱን ይቀጥላል ብለዋል። ቀደም ብለው ከተፈረሙ መንገዶች መካካል በውላቸው መሰረት የቅርብ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ 20ፕሮጀክቶች ወደ ግንባታ እንዲሸጋገሩ መደረጋቸውን አብራርተዋል። እንዲሁም 21የመንገድ ፕሮጀክቶች ሙሉ ለሙሉ ግንባታቸው ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆኑ የተደረገ ሲሆን በተለያዩ የሃገራችን አካባቢዎች የሚገኙ 15ፕሮጀክቶች ወደ ፍጻሜቸው እየተቃረቡ መሆናቸውን ዋና ዳሬክተሩ ገልጸዋል። ዛሬ ውላቸው የታሰሩት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ አስራ አምስት (15) የመንገድ ፕሮጀክቶች ርዝማኔ በአጠቃላይ 1,022.02 ኪ.ሜ (አንድ ሺህ ሃያ ሁለት ኪ.ሜር) ሲሆን አንድ ከባድ የመንገድ ጥገና እና አንድ የጠጠር መንገድን ያካትታል። ለእነዚህ አስራ አምስት(15) የመንገድ ኘሮጀክቶች የሚውለው አጠቃላይ የግንባታ ወጪ ከ25 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በላይ ሲሆን የግንባታዉ ሙሉ ወጪም የሚሸፈነዉ በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ መንገዶቹ ከዚህ ቀደም በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበሩ ሲሆን ፣ ካላቸው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንፃር ታይቶ በአሁኑ ወቅት በአስፋልት ደረጃ እንዲገነቡ ታቅዶ የውል ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ በጥቅሉ የመንገድ ፕሮጀክቶቹ የጎን ስፋት በገጠር 10 ሜትር ሲሆኑ በዞን ፣ በቀበሌ ፣በወረዳ ፣እና በዞን እንደአስፈላጊነቱ ተጨማሪ ስፋት ይኖራቸዋል። የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶቹ በታቀደላቸው ጊዜና የጥራት ደረጃ ተገንብቶ እንዲጠናቀቅ ተቋሙ አስፈላጊውን ድጋፍና ቁጥጥር እንደሚያደርግም ኢንጂነር ሃብታሙ አረጋግጠዋል ። የየፕሮጀክቱ አሽናፊ ተቋራጮች በበኩላቸው በተሰጠው የግንባታ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በጥራት አጠናቆ ለማስረከብ ቃል በመግባት ህብረተሰቡ ሁለንተናዊ ድጋፍ እንዲያደርግ ጠይቀዋል ።

የጅግጅጋ - ሎዋንጃ - ሀርሙካሌ መገንጠያ አስፋልት መንገድ ግንባታ ስራ እየተካሄደ ይገኛል። 104 ኪ.ሜ እርዝማኔ ያለው የጅግጅጋ - ሎዋንጃ - ሀርሙካሌ መገንጠያ መንገድ በአስፋልት ኮንክሪት ድረጃ
+2
የጅግጅጋ - ሎዋንጃ - ሀርሙካሌ መገንጠያ አስፋልት መንገድ ግንባታ ስራ እየተካሄደ ይገኛል። 104 ኪ.ሜ እርዝማኔ ያለው የጅግጅጋ - ሎዋንጃ - ሀርሙካሌ መገንጠያ መንገድ በአስፋልት ኮንክሪት ድረጃ ነው እየተገነባ የሚገኘው። መንገዱን ከ1ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየገነባ የሚገኘው አለም አቀፍ ተቋራጭ የሆነው ቻይና ሲቪል ኢንጅነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ድርጅት ነው። በእስካሁኑም የዲዛይንና ቅየሳ ፣ የአፈር ስራና ቆረጣ ፣ የግንባታ ግብአቶች እንዲሁም የዉሀ መፋሰሻ ቱቦዎች ምርት ስራ እየተከናወ ነዉ። የጅግጅጋ - ሎዋንጃ - ሀርሙካሌ መገንጠያ መንገድ ጅግጅጋንና ከዛም አልፎ ያሉ ትልልቅ ከተሞችን ከአገሪቷ ዋነኛ የገቢ ወጪ ንግድ ከሚስተናገድበት ከጅቡቲ ውደብ ከሚያዘልቀው ከድሬደዋ - ደውሌ የክፍያ መንገድ ጋር በአቋራጭ የሚያገናኝ ነው። የዚህ መንገድ ግንባታ ሲጠናቀቅ ከጅግጅጋ ወደ ደወሌ ለመጓዝ የእስከዛሬውን ከጅግጅጋ - ሀረር - ድሬደዋ መስመርን በቀጥታ በመጠቀም በማስቀረት 98 ኪ.ሜ ለመቀነስ የሚያስችል ይሆናል ። የንግድ ማዕከል የሆነችዉን ጅግጅጋ ከተማን በቀጥታ ከጅቡቲ ጋር ቀልጣፋ በሆነ የትራንስፖርት አገልግሎት በማስተሳሰር የጎላ ሚናንም ይጫወታል ። ከዚህም በተጨማሪ በመስመሩ ያሉ አምስት የወረዳ እና የቀበሌ ከተሞችን የዘመናዊ ትራንስፖርት ተጠቃሚ በማድረግ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ እንቅስቃሴያቸውንም ያሳድጋል። ለመንገዱ ግንባታ የሚወጣውን ወጪ የሚሸፍነው የኢትዮጵያ መንግስት ነው። https://www.facebook.com/www.era.gov.et/?ref=aymt_homepage_panel&eid=ARCkXPXNrutcTji1ezsMLyx-8UZgP6e94yvUstDKyuMebfrA51ZObNnufGAvcloBTVdQFrXI-7xz9Uj4

የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመከላከል የሚያግዝ የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሸከርካሪዎች ተርሚናል ግንባታ ተጀመረ በሶማሌ ክልል በሽንሌ ሲቲ ዞን አይሻ ወረዳ ደወሌ ቀበሌ የሚገኘውን የኮቪድ-19 ስርጭትን
+1
የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመከላከል የሚያግዝ የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሸከርካሪዎች ተርሚናል ግንባታ ተጀመረ በሶማሌ ክልል በሽንሌ ሲቲ ዞን አይሻ ወረዳ ደወሌ ቀበሌ የሚገኘውን የኮቪድ-19 ስርጭትን ለመከላከል የሚያግዝ የድንበር ተሻጋሪ የጭነት ተሸከርካሪዎች ተርሚናል ግንባታን በይፋ ተጀምሯል፡፡ ተርሚናሉ የመኪኖች ማቆያና በሂደትም ሁሉንም አገልግሎቶች ያካተተ ለሹፌሮች የመታጠቢያ፣ የማረፊያ፣ የምግብ፣ የጤና ምርመራና ህክምና አገልግሎቶችን የሚሰጥ ነው፡፡ ድንበር ተሻጋሪ ሹፌሮች ጉዞ ከመጀመራቸው በፊት፣ በአንድ ሀገር ክልል ውስጥ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ እንዲሁም ድንበር በር ላይ በሚደርሱባቸው ወቅቶች የሚወስዷቸው ጥንቃቄዎች ለወረርሽኙ ያላቸውን ተጋላጭነት ለመቀነስ ከፍተኛ ሚና አላቸው፡፡ በመሆኑም ተጋላጭነቱን ለማስወገድ ከደቡብ አፍሪካ ቀጠና የልማት ጥምረት #SADC፣ @UNECA፣ የኢትዮጵያ ዳያስፖራ አማካሪዎች ካዉንስልና @FMoHealth @EPHIEthiopia ያወጡዋቸውን የአሰራር ስርዓቶችና ሰነዶች መሠረት ያደረጉ ስታንዳርዶችን መጠቀም መቻሉን ተገልጻል፡፡ የኢፌዴሪ ትራንሰፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ለደወሌ ተርሚናል ግንባታ ስኬት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ተገቢውን የድጋፍ፣ የክትትልና የቁጥጥር ስርዓት የዘረጋ መሆኑን ጠቅስው የአካባቢው ህብረተሰብና የመስተዳድር አካላት እንደጅምሩ ሁሉ ለግንባታው በስኬት መጠናቀቅ አስፈላጊውን ትብብር እንደሚያደርጉ እምነታቸው መሆኑን ገልጸዋል።

ወደ ጢስ አባይ ፏፏቴ ቱሪስት መዳረሻ የሚዘልቀው የባህርዳር - ጢስ እሳት 22 ነጥብ 3 ኪ.ሜ መንገድ እየተገነባ ነው። የፕሮጀክቱን አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ በመስክ የስራ ቅኝት ተጎብኘቷል ። መንገዱ ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት ያልነበረው በመሆኑ የአካባቢው ነዋሪዎች ለብዙ አመታት ሲቸገሩ ቆይተዋል ። በአሁን ሰአት ደረጃው ከጠጠር ወደ አስፋልት ኮንክሪት እንዲያድግ ተደርጎ ነው እየተገነባ የሚገኘው ። በአሁኑ ወቅትም የዲዛይን ቅየሳ ፣ የአፈር ጠረጋና ድልዳሎ ስራዎች እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ የቱሪስት መዳረሻ ስፍራ የሆነውን ወደ አባይ ፏፏቴ የሚያዘልቅ 1.8 ኪ.ሜ መንገድ ለእግረኞች መጠቀሚያ ብቻ የሚሆን ደረጃውን የጠበቀ መንገድ ግንባታ ስራንም ያካተተ ነው ፡፡ በዚህም ወደ ስፍራዉ የሚጓዙ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የሀገር ዉስጥና የዉጭ ጎብኚዎች ከዚህ ቀደም በመንገድ መሰረተ ልማት መጓደል ይፈጠር የነበረውን እንግልት በማስቀረት ለአካባቢውም ሆነ ለሀገር ተጨማሪ የገቢ ምንጭ እንደሚፈጥር ይጠበቃል፡፡ በተጨማሪም ከዚህ በፊት በአካባቢው የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍ ህብረተሰቡ ተሸከርካራዎችን ተጠቅሞ በተመጣጣኝ ዋጋ ወደፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ የሚባል የወሰን ማስከበር አካባቢን የሚያካትት በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት በትብብር እንዲሰሩም ጥረት እየተደረገ ነው። ፕሮጀክቱ ካለው ሃገራዊ ፋይዳ አኳያ በተለይም ለአካባቢው የመስተዳድር አካላት ያልተፈቱ የወሰን ማስከበር ስራዎችን ይበልጥ በትጋትና በትብብር እንዲፍጠኑ ኢመባ ጠይቋል። መንገዱን እየተገነባ የሚገኘው አገር በቀሉ ተቋራጭ ሚልኮን ኮንስትራክሸን ድርጅት ነው፡፡ የባህርዳር - ጢስ እሳት መንገድ ለመገንባት ከ767 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቧል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ፕሮጀክቱን ለመገንባት የሚውለውን ወጪ ይሸፍነዋል ፡፡

በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከጤና ሚኒስቴር እና ከሌሎች አጋር ድርጅት ጋር በመሆን ያዘጋጀው ሁለት የሞባይል መተግበርያ (አፕሊኬሽኖችን) አገልግሎት ላይ ማዋሉን አስታውቋል። ከሞባይል መትግበርያዎቹ የአንደኛው የጤና ባለሞያዎችን እውቀት ለማሳድግ የሚያስችል ሲሆን ሌላው ኮቪድ-19 ከተያዘ ሰው ጋር ንክኪ ያላቸውን ሰዎች መለየት የሚያስችል ነው።

ይሄን አይታችሁ ዝም እንዳትሉ!! ለምትወዱት ላኩለት!! ============================= ..*** በኮሮና ቫይረስ ከተያዝክ በሕይወትህ ገምተህው ፤ አይተህ ፤ የማታውቀውን አይነት ትኩሳት /ንዳድ/ ይሰማሀል፡፡ ከዚህ የተነሳ እድሜ ሙሉህን ቃዥተህ የማታውቀውን ቅዠት ያስቃዥሀል ያልብሀል፤ ጉንፋን ይመስልሀል ግን አይደልም ሁሌ የሚሰማህ አይነት ጉንፋን ወይም ራስ ምታትም አይምሰልህ፡፡ .*** እስፖንጅ አፍንጫህ ላይ የተቀረቀረ ይመስል ለመተንፈስ ትቃትታለህ፡፡ ሳንባህን በአየር ለመሙላት በሀይለኛው ትንፋሽህን ስትስብ አየር ያጥርሀል! ያኔ ይጨንቅሀል ፤ ትፈራለህ! በሀይል ከማሳልህ የተነሳ በድካም አእምሮህን ልትስት ትደርሳለህ! ባሳልክ ቁጥር ደረትህ፣ እጆችህ፣ ጀርባህ፣ የእጅና እግር ጣቶችህ .... ነፍስህ እዚያ ጋር ያለ ይመስል በጣም ያሙሃል መገጣጠሚያህ ሁሉ የተነቃቀለ ይመስልሀል፡፡ .*** በአፍንጫህ አየር ለማስገባት ስለማትችል ኦክስጂን ይሰጡሀል፡፡ ወዳጄ ያ ደግሞ የአፍንጫህ ቱቦዎች እሳት የተለቀቀባቸው ያክል ስቃይ ይለቅብሀል! አሁንም መተንፈስ ካልቻልክ ሌላ ሀኪም ይመጣና ግማሽ ኢንች የሚሆኑ ሁለት ቱቦዎች በጉሮሮህ በኩል ወደሳንባዎችህ ይሰዳል! ይህን artificial respirator ብለው የሚጠሩት ህክምና ለመተንፈስ የሚረዳህ ነው፡፡ .*** ይህ ሁኔታ በጣም ከማስጠላቱና ከመክበዱ በላይ እጅግ አስከፊው ነገር ደግሞ መብላትና መጠጣት አትችልም ይህ አለመሆኑ ደግሞ የባሰ አቅም ያሳጣሀል፡፡ይህ ብቻ አይምሰልህ ከባዱ ነገር ደግሞ በዚህ ሁኔታ ውስጥ ብቻህን መሆን ስላለብህ አጠገብህ ማንም ሊረዳህ የሚችል ዘመድ አዝማድ ድርሽ አይልልህም ወላ እናትህን፣ አባትህን፣ ልጆችህን፣ ሚስትህን፣ ወንድምና እህትህን ወይም ጓደኛችህን ማየት አይፈቀድልህም፡፡(ይሄ በራሱ ያሳብድሀል) .*** ግራ አይግባህ ለምን ይህ እንደሆነብህ ገብቶሀል ? ምክንያቱም ሊገልህ ባለው በሽታ እንዳትበክላቸው ነው! አንዴ ልድገምልህ? ሊገልህ ያለው ኮሮና በቁምህ ዘመድ አዝማድ ጓደኛህን መንጠቅ ጀምሯል!! በዚህ ስቃይ ውስጥ ብቻህን ከመሆንህ የተነሳ ትፈራለህ፣ ታለቅሳለህ ፣ ሊገልህም እንደሚችል ይገባሀል ! ! ! በነገርህ ላይ ልትሞትም ትችላለህ! የምትወዳቸውን እያሰብክ ካለጠያቂ ነፍስ ለማዳን በሚዋከቡ ሀኪሞች ተከበህ ታለቅሳለህ፤ ከትንፋሽህ ጋር ግብ ግብ እየገጠምክ፡፡ .*** ትንሽ ያገገምክ መስሎህ ውስጥህ ተስፋ እየጫረ ባለበት ጊዜ ደግሞ አይንህ እያየ ከተኛህበት ሆስፒታል ካንተው ክፍል ውስጥ ካንተ ቀድሞ የገባ ወይም ካንተ በኋላ የመጣ በነጭ ጨርቅ ተጠቅልሎ አስከሬኑ ሲወጣ ልታይ ትችላልህ! ይህ ደግሞ ቀጥሎ ተረኛ እንደሆንክ እየተሰማህ የባሰ በፍርሀት ታልቃለህ ማለት ነው !! .*** ልክ ይሄንን ስታይ ይቆጭሀል ፤ ያንገበግብሀል ወዲያው ከቻልክ እቤትህ ተቀመጥ፣ ያለምክንያት ከቤት አትውጣ፣ እጅህን በተደጋጋሚ ታጠብ፣ ሳኒታይዘርና አልኮሆል ተጠቀም፣ ርቀትህን ጠብቅ እና ማስክ አድርግ የተባልከው ትዝ የሚልህ! ይሄኔ ነው አሁን የባሰ በቁጭት አለንጋ ትገረፋለህ!! ይፀፅትሀል! እድለኛ ከሆንክ በዚህ ሁሉ አልፈህ ልትተርፍ ትችላለህ ካልሆነ ግን አይንህ እያየ በቸልተኝነትህ ይቺን ምድር በኮሮና ምክንያት ትሰናበታለህ ማለት ነው!! .*** ወዳጄ አንድ ነገር ልምከርህ እኔ ለወላጆቼ ለልጆቼ ለኋደኞቼ ለሚወዱኝ ለምወዳቸው ለሚያከብሩኝ ለማከብራቸው ስል እጠነቀቃለሁ ብለህ ካሁኑ ንቃ! ጥቂት ቀናት ታሪክህን ሊቀይሩ ይችላል!

የሙከጡሪ-ኮከብ መስክ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የግንባታ እንቅስቃሴ በትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታው አቶ ካሳሁን ጎፌ እና በኢመባ የስራ ሃላፊዎች ዛሬ በመስክ የስራ ቅኘት ተጎብኝቷል። 58 ነጥብ 8ኪ.ሜትር ርዝመት የሚሸፍነውን ይህንኑ ፕሮጀክት ነው ዛሬ የተቃኘው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ቀደም ብሎ በወሰን ማስከበር እና ተያያዥ ችግሮች ሳቢያ በእቅዱ መሰረት ለመስራት ሲቸገር ቆይቶ በአሁኑ ወቀት ያሉት ዋና ዋና ችግሮች በመቀረፍቸው ፕሮጀክቱ በጥሩ ሁኔታ በመከናወን ላይ መሆኑን ለሚኒስትር ድኤታው ገለጻ ተደርጎላቸዋል። በዚህም በአሁኑ ወቅት የአስፖልት ማንጠፍ ስራ የተጀመረ ሲሆን በያዝነው አመት መጨረሻ ድረስም ከ20ኪሎሜትር በላይ ለማከናወን አቅዶ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተመልክቷል። አጠቃላይ ፕሮጀክቱን በቀጣይ አመት ሙሉ ለሙሉ አጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ይሆናል ። ይህ እንዲሆን አሁንም ከወሰን ማሰከበር ጋር ተያይዞ ያልተፈቱ ችግሮችን ለማቃለል ሁሉም ባለድርሻ አካላት ይበልጥ ተቀራርቦ እንዲሰራም ሚኒስትር ድኤታው አቶ ካሳሁን ጎፌ አሳስበዋል። የዛሬው የመስክ ቅኘት አላማም የፖሮጀክቱን ሂደት በአካል ከመመልከት ባለፈ የሚስተዋሉ ተግዳሮቶችን ለመፍታትም የበኩሉን ሚና ያበረክታል። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣንም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በትኩረት እየሰራ ነው። የሙከጡሪ -ኮከብ መስክ መንገድ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እንዲገነባ ሆኗል። በብር 768,622, 711.45(ሰባት መቶ ስልሳ ስምንት ሚሊየን ስድስት መቶ ሃያ ሁለት ሺህ በላይ በሆነ ወጪ ጨረታውን አሸንፎ ግንባታውን በማከናወን ላይ የሚገኘው ቻይና ሪልዌይ ቁጥር ሦስት ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ፒልሲ ነው። የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ዩናይትድ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ፒልሲ (UNICONE) የተባለ አማካሪ ድርጅት ነው። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ለመስመሩ ከፍተኛ የሆነ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፍይዳዎችን የሚያጎናጽፍ ነው። አካባቢው ለምና የቱሪስት መስህብ ቦታዎች ስላሉት ለጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። በመንገዱ የሚዋሰኑ የኦሮሚያና የአማራ ክልል አርሶ አደሮች ምርታቸውን በቀላሉና በተቀላጠፈ ሁኔታ ወደ ተላያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ለማመላለስ ያስችላል።

አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ የግንባታ ፕሮጀክት ስራ እየተፋጠነ ነው፡፡ በ1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በሆነ ወጪ በቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ በባህርዳር ከተማ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘው አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ፕሮጀክትን በመስክ የስራ ቅኘት ተጎብኘቷል። ባህርዳር ከተማ ውስጥ ከሚገኘው ከነባሩ አባይ ወንዝ ድልድይ 2 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ነው አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ ግንባታ እየተካሄደ የሚገኘው፡፡ የግንባታ ስራው ከተጀመረ ዘጠኝ ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን የግንባታ አፈጻጸሙ በእቅዱ መሰረት በጥሩ ደረጃ ላይ ይገኛል ። የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ከዲዛይን ስራዎች እና የካምፕ ግንባታዎች መጠናቀቅ በተጨማሪ በዋነኝነት ከመሬት በታች የድልድዩ የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶች ቁፋሮ እና አርማታ ሙሌት ስራ ነው እየተከናወነ የሚገኘው፡፡ ከመሬት በታች የሚቀበሩት እነዚህ የክብ ቅርፅ ያላቸው የድልድዩ የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶች በዲዛይኑ መሰረት ከዝቅተኛው 14 ሜትር እስከ ከፍተኛው 23 ሜትር ድረስ ወደታች የሚቀበሩ ናቸው፡፡ የአንዱ የቋሚ ተሸካሚ መሰረት የመሀል መለኪያ ስፋት በድልድዩ የዳር እና ዳር ተሸካማዎች 1.5 ሜትር ሲሆን የመካከል ተሸካሚዎች ደግሞ 1.8 ሜትር ነው፡፡ 380 ሜትር የሚረዝመው አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ የግንባታ ስራ ፕሮጀክት በእስካሁኑ አፈፃፀም በአጠቃላይ ድልድዩን ለመሸከም ከሚያስፈልጉ 88 የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶች ውስጥ 48 የሚሆኑት የቁፋሮ እና የአርማታ ሙሌት ስራ ማከናወን ተችሏል፡፡ ቀሪዎቹን የቋሚ ተሸካሚ መሰረቶችም በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ እቅድ ተይዞ እየተሰራ ይገኛል፡፡ ዓለም አቀፍ ደረጃውን በጠበቀ ሁኔታ እየተገነባ የሚገኘው አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ለማከናወን የሚወጣውን 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት ነው የሚሸፈነው፡፡ 43 ሜትር የጎን ስፋት ያለው የአባይ ወንዝ ድልድይ በግራና በቀኝ በአንድ ጊዜ 6 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ እንዲችል ተደርጎ ነው እየተገነባ የሚገኘው ። ከዚህም በተጨማሪም ግንባታው የብስክሌት ተጠቃሚዎች መስመር እንዲሁም 5 ሜትር የእግረኛ መሄጃንም አካቷል፡፡ የድልድዩን ግንባታ በተቆጣጣሪነት እና በአማካሪነት እያገለገሉ የሚገኙት የቱርኩ ቦቴክ እና የአገር ውስጥ አማካሪው እስታዲያ በጋራ በመሆን ነው። በአይነቱ እና በዲዛይን ጥበቡ በሀገራችን ዘመናዊ የአባይ ወንዝ ድልድይ የግንባታ አይነት በተሻሻለ መንገድ በገመድ የተወጠረ (Extradosed cable steyed Bridge) የድልድይ ዲዛይን ነው፡፡ ድልድዩን በአዲስ መልክ ለመገንባት ያስፈለገበት ዋነኛ ምክንያት ነባሩ የአባይ ወንዝ ድልድይ ከተገነባ 60 አመታትን በማስቆጠሩና በአገልግሎት ብዛት ለተደጋጋሚ ጉዳት በመዳረጉ ነው ፤ በተጨማሪም የድልድዩ የጎን ስፋት 10 ሜትር ከመሆኑ አንጻር በመስመሩ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው የትራፊክ ፍሰት መጨናነቅ በመፍጠሩ ነው ፡፡ ድልድዩ አለም አቀፋዊ ደረጃውን በጠበቀ ሁናቴ ዘመናዊ በሆነ መልኩ መገንባቱ የሀገር ቋሚ የቱሪስት መስህብ በመሆን እረገድ ፍይዳው የጎላ ነው ። አፍሪካን በመንገድ መሰረተ ልማት ማገናኘት ያለመው ትራንስ አፍሪካ ሃይ ወይ የተሰኘው ከግብፅ ካይሮ ተነስቶ ደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ድረስ የሚዘልቀው ዋና መንገድ አካል በመሆኑ በዚህ አፍሪካ አቀፍ ባህርይ ባለው መንገድ ላይ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥቅምን ለኢትዮጵያ በማስገኘት ዘመኑን የሚመጥን ድልድይ መገንባት ጠቀሜታው ከሀገር አልፎ አህጉራዊ ፋይዳው የጎላ ነው። የድልድዩ ግንባታ በሶስት አመት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል፡፡

የሙከጡሪ-ኮከብ መስክ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአስፖልት ንጣፍ ስራ ማከናወን ጀመረ። 58 ነጥብ 8ኪ.ሜትር ርዝመት የሚሸፍነውን ይህንኑ ፕሮጀክት የመስክ ቅኝት ተካሂዶል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ቀደም ብሎ በወሰን ማስከበር እና ተያያዥ ችግሮች ሳቢያ በእቅዱ መሰረት ለመስራት ሲቸገር ቆይቷል። በአሁኑ ወቀት ያሉት ዋና ዋና ችግሮች በመቀረፍቸው ፕሮጀክቱ በጥሩ ሁኔታ በመከናወን ላይ መሆኑን በመስክ ቅኘታችን ተመልክተናል። በአሁኑ ወቀት 12ኪሎ ሜትር የአስፖልት ማንጠፍ ስራ የተሰራ ሲሆን በያዝነው አመት መጨረሻ ድረስም ከ20ኪሎሜትር በላይ ለማከናወን አቅዶ በትኩረት እየተሰራ ነው። አጠቃላይ ፕሮጀክቱን በቀጣይ አመት ሙሉ ለሙሉ አጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ይሆናል። ይህ እንዲሆን አሁንም ከወሰን ማሰከበር ጋር ተያይዞ ያልተፈቱ ችግሮችን ለማቃለል የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በትኩረት እየሰራ ነው። የሙከጡሪ -ኮከብ መስክ መንገድ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እንዲገነባ ሆኗል። በብር 768,622, 711.45(ሰባት መቶ ስልሳ ስምንት ሚሊየን ስድስት መቶ ሃያ ሁለት ሺህ በላይ በሆነ ወጪ ጨረታውን አሸንፎ ግንባታውን በማከናወን ላይ የሚገኘው ቻይና ሪልዌይ ቁጥር ሦስት ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ፒልሲ ነው። የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ዩናይትድ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ፒልሲ (UNICONE) የተባለ አማካሪ ድርጅት ነው። ይህ የመንገድ ፕሮጀክት ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ለመስመሩ ከፍተኛ የሆነ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፍይዳዎችን የሚያጎናጽፍ ነው። አካባቢው ለምና የቱሪስት መስህብ ቦታዎች ስላሉት ለጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን ይፈጥራል። በክልሎቹ በተለይም በመንገዱ የሚዋሰኑ የኦሮሚያና የአማራ ክልል አርሶ አደሮች ምርታቸውን በቀላሉና በተቀላጠፈ ሁኔታ ወደ ተላያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ለማመላለስ ያስችላል።