ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 365 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 754,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 531 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 365 名订阅者。
根据 19 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 119,过去 24 小时变化为 19,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.59%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.42% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 423 次浏览,首日通常累积 2 060 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 20 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 361
订阅者
+1924 小时
+677 天
+11930 天
帖子存档
13 365
የኢትዮ - ጅቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር አካል የሆነው የአዳማ - አዋሽ - መኢሶ መንገድ ከአዳማ - ኪ.ሜትር 60 መንገድ ከባድ ጥገና ተጀመረ።
መንገዱ ካለው ዘርፈ-ብዙ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳ አንፃር የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ከባድ ጥገናውን ማድረግ አስፈላጊ ሆኗል። በመሆኑም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የትራፊክ ፍሰት በበቂ ሁኔታ ለማስተናገድ እና የገቢ እና ወጪ ንግዱን ለማቀላጠፍ እንዲቻል ከፍተኛ ጥገና (አስፋልት ኦቨርሌይ) ስራው ተጀምሯል።
በዚህም መሰረት የመንገድ ፕሮጀክቱ ግንባታ አካል የሆነው የአዳማ-ኪ.ሜ 60 ምዕራፍ-1 መንገድ፣ ለጥገናው የሚያስፈልጉ የጠጠር ማምረት ስራ እና ሌሎች ለግንባታው የሚረዱ የተለያዩ የቅድመ-ግንባታ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
እንዲሁም በፕሮጅክቱ ክልል ውስጥ የአስፋልት ፓቺንግ ሥራ እየተከናወነ ነው። በመሆኑም ጥገናው የትራፊክ ፍሰቱን በማያስተጓጉል መልኩ በፍጥነት ለማከናወን እንዲቻል ተሽከርካሪዎች በተለዋጭ መንገድ እንዲጠቀሙ ይደረጋል።
ከባድ የመንገድ ጥገናውን ዮንአብ ኮንስትራክሽን ድርጅት እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን በለስ አማካሪ ኃ/የተ/የግ/ማ እያከናወነ ይገኛል። ለከባድ ጥገናው የሚውለው 816,465,221(ስምንት መቶ አስራ ስድስት ሚሊዮን አራት መቶ ስልሳ አምስት ሺህ ሁለት መቶ ሃያ አንድ ብር) ሙሉ ለሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል።
የመንገድ ጥገና ፕሮጀክቱ የአዳማ እና ቦሰት ወረዳዎችን እንዲሁም ዳቤ ሶሎቄ እና ወለንጪቲ ቀበሌዎችን የሚያገናኝ ነው።
የዚሁ መንገድ ቀጣይ ክፍል የሆነው ከኪ.ሜ 60 እስከ አዋሽ ያለው መንገድ ከኢትዮጵያ መንግስት በተመደበ 1.3 ቢሊዮን ብር ወጪ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ጥገናው እየተካሄደ ይገኛል፡፡ የቁጥጥር እና የማማከር ሥራውን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ስራዎች ኮርፖሬሽን እየሰራ ይገኛል።
በተመሳሳይም ከአዋሽ መኢሶ የሚዘልቀው ምዕራፍ-3 መንገድ ከባድ ጥገና ከመንግስት በተመደበ 478,385,156 (አራት መቶ ሰባ ስምንት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሰማኒያ አምስት ሺህ አንድ መቶ ሃምሳ ስድስት ብር) ወጪ ዮንአብ ኮንስትራክሽን እያከናወነ ይገኛል፡፡ የማማከር ሥራውን ሃይዌይ ኢንጂነርስ እና ኮንሰልታንት ኃ/የተ/የግ/ማ እየሰራ ይገኛል፡፡
ፕሮጀክቱ 70.5 ኪ.ሜ የሚረዝም ሲሆን፣ የአስፋልት ማንጠፍ ሥራ (አስፋልት ኦቨርሌይ) ሥራ እና የቤዝ ኮርስ እና የሰብበቤዝ ሥራዎች በፕሮጀክቱ ተካተዋል፡፡
በአጠቃላይ መንገዱ ከፍተኛ የገቢ እና ወጪ ንግዱን ከማቀላጠፉም በላይ በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን የተለያዩ የግብርና ምርቶች በጥራትና ፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ የጎላ ሚና ይኖረዋል። የቱሪዝም መዳረሻ የሆነውን የአዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ለጎብኝዎች ምቹ በማድረግ ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡
ይህ መስመር የሀገሪቱ ዋነኛው የገቢ እና ወጪ ንግድ የሚተላለፍበት እንደመሆኑ ያለውን የትራፊክ ፍሰት ይበልጥ ደረጃውን በጠበቀ መልኩ ሊያስተናግድ የሚያስችል የፍጥነት መንገድ ምዕራፍ አንድ አዳማ-አዋሽ (60 ኪ.ሜ) ግንባታ መጀመሩ ይታወቃል፡፡
13 365
የሀገረመቆር- ቁንዲ ክፍል ሁለት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ።
የመንገድ ፕሮጀከቱ 102 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው ሲሆን ለትራፊክ ክፍት ሆኖ ተገቢውን አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
የሁለት ድልድዮች (እያንዳንዳቸው 20 እና 140 ሜትር ርዝመት ያላቸው) ግንባታም ሙሉ ለሙሉ ተጠናቅቋል፡፡
ይህም በመሆኑ በመስመሩ ከዚህ ቀደም ይስተዋል የነበረውን ከፍተኛ የትራንስፖርት እንግልት በማስቀረት ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ፋይዳው የጎላ እንዲሆን አስችሏል።
በአካባቢዉ የሚገኙትን ከፍተኛ የቁም እንስሳት እና የእንስሳት ተዋፅዖ ምርቶችን በፍጥነት ወደገበያ ለማድረስ አስችሏል ፡፡
በዋናነትም ጨረቲ ወረዳን ከጎሮበቀቅሳ እና ከጎሮዳሞሌ ወረዳ ጋር አሰተሳስሯል ፡፡
ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ መንግስት በተመደበ አንድ ቢሊየን አምስት መቶ ሃምሳ ስምት ሚሊየን አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር የተገነባ ነው።
ግንባታውን ያከናወነው ደግሞ ዓለም-አቀፉ የስራ ተቋራጭ ቻይና ኮሚኒኬሽን ኮንስትራክሽን ተቋራጭ ነው፡፡
የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ያከናወናወኑት ደግሞ ስታዲያ ኢንጅነሪንግ ከጂ እና ዋይ ኢንጅነሪንግ ጋር በጥምረት በመሆን ነው፡፡
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በገጠር 8 ሜትር፣ በቀበሌ 14 ሜትር በወረዳ 19 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ነው፡፡
ይህ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት መነሻውን ጨረቲ ከተማ ላይ አድርጎ ቁንዲ ከተማ ላይ የሚያበቃ ሲሆን
፡የጨረቲ -ጎሮበቀቅሳ- ጎሮዳሞሌ - ሀገረመቆር- ቁንዲ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አካል ነው።
የዚህ መንገድ አካል የሆነው የጨረቲ- ሀገረመቆር ክፍል-1 መንገድ ግንባታው ቀደም ብሎ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ይታወሳል ፡፡
13 365
በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ተከስቶ በነበረው ጦርነት ሳቢያ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበት አገልግሎት መሰጠት አቁሞ የነበረው የጨረቲ ወንዝ ድልድይ በተገጣጣሚ የብረት ድልድይ በመተካት እና ከነተሸካሚው ገንብቶ በማጠናቀቅ መንገዱ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን ተደረገ ፡፡
ይህው 88 ሜትር ርዝመት ያለው ነባሩ የጨረቲ ወንዝ ድልድይ በጦርነቱ ሳቢያ በመጎዳቱ ከሚሌ - ጭፍራ - ወልዲያ መንገድ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ተቋርጦ እንደነበር የሚታወስ ነው።
በመሆኑም በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል መስመሩን ለትራፊክ አገልግሎት ክፍት ለማድረግ እንዲቻል ድልድዩን የመገንባት ስራ ከአንድ ወር በፊት የተጀመረ ሲሆን በዚህም አዲስ 9 ሜትር ቁመት፣ 8 ሜትር ስፋት እንዲሁም 6.2 ሜትር ርዝመት ያለው የማስነሪ አባትመንት ግንብ ሥራ ተከናውኗል ።
በተጨማሪም የዲዛይን እና ቁፋሮን አካቶ በ22 ቀናት ውስጥ በማጠናቀቅ እና ቀሪውን 48 ሜትር ርዝመት ያለው የብረት ድልድይ በአንድ ሳምንት ጊዜ በመገጣጠም አጠቃላይ የድልድዩን ሥራ በአንድ ወር ውስጥ በእቅዱ መሰረት ተጠናቆ በዛሬው ቀን ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ ተችሏል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አሰተዳደር ድልድዩን ለአገልግሎት ለማብቃት ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ አድርጓል።
13 365
የሞጆ - ሀዋሳ ፈጣን የመንገድ ፕሮጀክት አካል የሆኑት ክፍል ሶስትና አራት የመንገድ
ግንባታ ፕሮጀክቶች በመስክ የስራ ቅኝት ተጎበኙ::
በክፍል ሶስት ባቱ - አርሲ ነጌሌ 57 ኪ.ሜ እና ክፍል አራት የአርሲ ነጌሌ - ሀዋሳ 52
ኪ.ሜ የአስፋልት ኮንክሪት የዲዛይንና ግንባታ ፕሮጀክቶች ናቸው በኢትዮጵያ መንገዶች
አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኘ እና በሌሎች የተቋሙ የስራ ሀላፊዎችና
በሚመለከታቸው አካላት የተቃኙት::
በዚህም እየተከናወኑ የሚገኙ ወቅታዊ የግንባታ ስራ እንቅስቃሴዎችና ቀጣይ ስራዎች
በጥልቀት ተገምግመዋል::
የባቱ - አርሲ ነጌሌ ግንባታን እያከናወነ የሚገኘው የእስራኤሉ SBI international holdings A.G /ኤስ ቢ አይ ኢንተርናሽናል ሆልዲንግስ ኤ.ጂ ነው/፡፡
የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ኩንውሀ ኢንጂነሪንግ እና ኮንሰልቲንግ ከኮሪያ
ኤክስፕረስ ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ እያከናወኑት ይገኛሉ፡፡
ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ የሚሆነው ሶስት ቢሊየን ሶሰት መቶ ስምንት ሚሊየን ሁለት መቶ አርባ ሶስት ሺህ ብር እየተሸፈነ የሚገኘው ከአለምባንክ በተገኘ ፋይናንስ ነው፡፡
በዚህ የመንገድ ፕሮጀክት የአፈር ቆረጣ ስራ፣የሰብ ቤዝ ስራዎች፣የስትራክቸር ፣የውሀ
ማፋሰሻ፣የአቃፊ ግንብ፣ትላልቅ የድልድይ ግንባታ፣ማሳለጫዎችና ማቋረጫዎች እንዲሁም
የክሬሸር (ጠጠር የመፍጨት) ስራ በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡
እንዲሁም 21 ኪሎሜትር የDBM/ ለመጨረሻ የአስፋልን ንጣፍ ስራ ዝግጁ የማድረግ ስራ ተጠናቋል/ ።
ቀጣዩን አርሲ ነጌሌ - ሀዋሳ የሚዘልቀውን የመንገድ ክፍል የሚገነባው የስራ ተቋራጭ
አለም አቀፉ የስራ ተቋራጭ (cccc) ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ ነው፡፡
የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ቤጂንግ ኤክስፕረስ ዌይ ሱፐር ቪዥን ካምፓኒ ሊሚትድ
ከውሀን ጄአይኦኬ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልታንሲ ሊሚትድ ጋር በጋራ በመሆን እየሰሩት ነው ፡፡
መንገዱን ለመገንባት የሚውለውን ወጪ አምስት ቢሊየን አንድ መቶ አርባ ዘጠኝ ሺህ ብር በቻይናው ኤግዚም ባንክ 85 በመቶ እና 15 በመቶ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡
በተመሳሳይም በአርሲ ነጌሌ - ሀዋሳ የመንገድ ፕሮጀክት የአፈር ቆረጣ እና ድልዳሎ
ስራ፣የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣የስትራክቸር ስራዎች፣የሰብ ቤዝ ስራ፣የውሀ ማፋሰሻ
ቱቦዎች ቀበራ፣የድልድይ ግንባታ፣የጠጠር ንጣፍ ስራዎች እየተሰሩ ናቸው፡፡
በተመሳሳይ የ3 ነጥብ 4 ኪሎሜትር ለመጨረሻ የአስፋልን ንጣፍ ስራ ዝግጁ የማድረግ ስራ የDBM ተጀምሯል
በአጠቃላይ መንገዶቹ እያንዳንዳቸው 31.6 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖራቸው ተደርገው
የሚገነቡ ይሆናል፡፡
ፕሮጀክቶቹ በተቀመጠላቸው ጊዜ ግንባታቸው እንዲጠናቀቅ ለማስቻል ከስራ ተቋራጮቹና
ከአማካሪ ድርጅቶች ጋር ምክክር ተደርጓል፡፡
በቀጣይም የሚከናወኑ ስራዎችን በተመለከተም የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር
ሀብታሙ ተገኘ የስራ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል።
በሁለቱም የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክቶች ስራ ላይ የሚያጋጥሙ ውስንነቶችን በመፍታት
ግንባታው ይበልጥ በፍጥነትና በሚገባ መልኩ እንዲከናወን ለማስቻልም የሚደረገውን
ጥረት እንደሚቀጥልም አመላክተዋል፡፡
የመንገዶቹ መገንባት የንግድን ትስስርን በማፋጠን የትራንስፖርት ወጪን በመቀነስ
ሀገራዊና አህጉራዊ ፍይዳው የጎላ በመሆኑ በልዩ ትኩረት ለማጠናቀቅ ይበልጥ የክትትልና
የድጋፍ ማዕቀፉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል::
የሞጆ - ሀዋሳ ፈጣን መንገድ አካል የሆኑት ክፍል አንድ ሞጆ - መቂ እንዲሁም ክፍል
ሁለት መቂ - ባቱ ከዚህ ቀደም ግንባታቸው ተጠናቅቆ ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት
መደረጉ የሚታወስ ነው፡፡
13 365
ቋሚ ኮሚቴው የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደርን ጎበኘ
የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ፣ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር(እመአ) ዋና መሥሪያ ቤትን በዛሬው ዕለት ጎበኙ፡፡
የቋሚ ኮሚቴው አባላት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚገነቡና የሚጠገኑ መንገዶችን ጉብኝት ካደረገ በኋላ ነበር ቢሮውን የጎበኙት፡፡
በቢሮ ጉብኝታቸውም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያከናወናቸውን የለውጥ ሥራዎች ማለትም የሥራ ቦታን ምቹ ከማድረግ ጀምሮ የተቋሙን ሥራዎች በተክኖሎጂ እስከማጀመን ድረስ ያሉ ተግባራትን ተዘዋውረው አይተዋል፡፡
ኮሚቴው የቢሮ ግብኝቱን ካጠናቀቀ በኋላ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎች ጋር የመንገድ ዘርፉ አጠቃላይ ወቅታዊ ሁኔታ፣ የ2014 ዓመት የመንገድ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም፣ የመንገድ ዘርፍ የሚያጋጥሙ ችግሮችንና ከመንግስት የሚፈለግ ድጋፍ በሚመለከት ውይይት አድርገዋል፡፡
የእመአ ፕሮጀክቶች አፈጻጸምን የሚመለከት የውይይት መነሻ ሀሳብ በእመአ ምክትል ዋና ዳይሬክተር በሆኑት አቶ የትምጌታ አሥራት ቀርቦ የቋሚ ኮሚቴው አባላትም ጉብኝታቸው መነሻ ያደረጉ አስተየቶችንና ጥያቄዎችን አንስተዋል፡፡
በተነሱ ጥያቄዎች በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጅኒየር ሐብታሙ ተገኝ ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ በማብራሪያቸውም መንገዶች በተያዘላቸው ጊዜ ገደብ ተጀምረው እንዲጠናቀቁ ብሎም ጥራታቸው እንዲጠበቅ ከማድረግ ረገድ መሥሪያ ቤቱ ተገቢውን ክትትል እያደረገ መሆኑ የተጠበቀ ሆኖ ለመንገዶች መዘግየት ምክንያት በሚሆኑት ጉዳዮች ዙሪያ ከቋሚ ኮሚቴው ድጋፍ የሚያስፈልግ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ፣ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑት የተከበሩ ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ በሰጡት ማጠቃለያ የመንገዶች አስተዳደር የመንገድ መረጃዎችን አደራጅቶ ከመያዝ፣ በርካታ ፕሮጀክቶችን በውጤታማነት ከመምራትና በሰባ ዓመታት የተሰሩ ሥራዎችን ይበልጥ እያዳበረና እያሻሻለ፣ አዳዲስ ፈጠራዎችንና አሰራሮችን እየዘረጋ ዘርፉን ውጤታማ ማድረግ የሚያስችሉ በርካታ ተግባራትን በማከናወን ውጤታማ መሆኑ የሚደነቅ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
ሰብሳቢዋ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እንዲጠናቀቁ ከማድረግ አኳያ ጠንከር ያለ ክትትል እንደሚያስፈልግና ከክልሎች ጋር የተጠናከረ ቅንጅት መፍጠር ትኩረት የሚሰጥበት መሆኑንም በአጽንኦት አንስተዋል፡፡
13 365
የኦሮሚያ ክልልን ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚያስተሳስረው የአጋሮ-ጌራ-ሜዳቦ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት በመስክ የሥራ ቅኝት ተጎብኝቷል።
100 ኪ.ሜ የሚረዝመው ፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈፃፀሙ በጥሩ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ በመስክ የስራ ቅኝቱ ተገምግሟል።
ግንባታው የዕለት ተዕለት መደበኛ የትራንስፖርት ፍሰቱን በማያስተጓጉል መልኩ እየተካሄደ ይገኛል።
በእስካሁኑ የሥራ እንቅስቃሴም ፤ የዲዛይን ሥራ፣ የካምፕ ግንባታ፣ የአፈር ቁፋሮ ሥራዎች፣ የጠጠር ማምረት፣ ኮንክሪት ፓይፕ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
የአምስት ድልድዮች የግንባታ ስራ በፕሮጀክቱ የተካተተ ሲሆን ከዲዛይን ጋር የተያያዙ ሥራዎችን አጠናቅቆ በቅርቡ ወደ ሙሉ ግንባታ ለመሸጋገር በትኩረት እየተሰራ ነው።
ፕሮጀከቱ የሚከናወነው ፣ የኢትዮጵያ መንግስት በመደበው 3,170,122, (ሶስት ቢሊዮን አንድ መቶ ሰባ ሚሊዮን አንድ መቶ ሃያ ሁለት ሺህ ብር ነው።
ግንባታውን ደግሞ ራማ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግል/ማ እያከናወነ ይገኛል ።
የቁጥጥር እና የማማከር ሥራውን ኢንጂነር ዘውዴ እስክንድር አማካሪ ድርጅት እያካሄደ ይገኛል፡፡
ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ በዋናነት የኦሮሚያ እና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦችን በቅርበት ያስተሳስራል።
መነሻውን ከአጋሮ ከተማ በማድረግ የጌራ ወረዳ መቀመጫ የሆነችውን ጭራ ከተማ አቋርጦ ከፋ ዞን ገዋታ ወረዳ ሜዳቦ ከተማ ላይ ያበቃል።
መንገዱ ቀድሞ ይፈጅ የነበረውን የጉዞ ጊዜ ከአንድ ሰዓት በላይ በማሳጠር የጎማ፣ ጌራ እና ገዋታ ወረዳዎችን በቅርበትም ያገናኛል ።
አካባቢው የቅይጥ ግብርና እና የእንስሳት እርባታ በሰፊው የሚከናወንባቸው በመሆኑ
እነዚህን የግብርና ውጤቶች ወደ ማዕከላዊ ገበያ በጥራት እና በፍጥነት ለማድረስ ያስችላል።
በተለይም የሀገር ኢኮኖሚ ዋልታ የሆነው የቡና ምርት በስፋት የሚገኝበት በመሆኑ ሚናው የጎላ ነው።
በመሆኑም የሥፍራውን እምቅ የተፈጥሮ ፀጋዎች ለመጠበቅ፣ ግንባታው የአካባቢ እና ማህበራዊ ጥበቃ መርሆችን በተከተለ መልኩ በጥንቃቄ የሚከናውን ይሆናል።
መንገዱ በዲዛይኑ መሠረት ደረጃውን ጠብቆ በከተሞች የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 19 ሜትር በወረዳ ማለትም አጋሮ እና ጌራ ላይ 21 ሜትር በቀበሌ 12 ሜትር ሲሆን በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜትር የጎን ስፋት ይኖረዋል።
13 365
የሰከላ አዴት ኮንትራት ሁለት የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በጥሩ የግንባታ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል።
61 ኪ.ሜ የሚረዝመው ይህው መንገድ በመስክ የስራ ስምሪት ተቃኛቷል ።
በእስከ አሁኑም የአፈር ቆረጣና ሙሌት ሥራዎች ፣ የቤዝኮርስ፣ የድልድይ እንዲሁም የውሃ መተላለፊያ ቱቦዎች ከልቨርቶች እና በርካታ የስትራክቸር ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
ሀመንገዱ ተገንብቶ እስከሚጠናቀቅ ለመንገዱ ተጠቃሚ ህብረተሰብ የትራንስፖርት መስተጓጎል እንዳይፈጠር ለማስቻል የተለዋጭ መንገድ ግንባታ እየተሰራ ይገኛል፡፡
የመንገድ ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው አገር በቀሉ ዲ.ኤም.ሲ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡
የማማከርናየቁጥጥርስራውንየሚያካሂደው የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ዲዛይንና ሱፐርቪዥን ስራዎች ኮርፖሬሽንነው።
ለመንገዱግንባታየሚውለው2,578,671,578.69 ብር ነው።
የግንባታ ወጪውም የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡
መንገዱን ገንብቶ ለማጠናቀቅ ለስራ ተቋራጩ የሶስት ዓመት የጊዜ ገደብ የተሰጠው ሲሆን ፣
ግንባታው በተገቢው የጥራት ደረጃ እና ፍጥነት እንዲጠናቀቅ በአትኩሮት እየተሰራ ነው፡፡
መንገዱ ትከሻን ጨምሮ በከተማ 21 ሜትር ፣ በቀበሌ እና በገጠር ደግሞ 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው፡፡
አካባቢው ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ የአስፋልት መንገድ ተጠቃሚ ያልነበረ በመሆኑ ምክንያት የተለያዩ ችግሮችን ሲያስተናግድ ቆይቷል፡፡
ፕሮጀክቱ እውን ሲሆን አካባቢ ከፍተኛ የጤፍ ፣ ስንዴ እና ሌሎች የግብርና ምርቶችን ጨምሮ ማርና የአትክልት ምርታማነቱ ከፍተኛ በመሆኑ ሚናው የላቀ ነው።
መንገዱ ተገንብቶ ለአገልግሎት ክፍት ሲሆን እነዚህን የግብርና ምርቶችን ያለምንም ችግር በአፋጣኝ ወደ ገበያ ለማቅረብ እና የአካባቢው የንግድ እንቅስቃሴ ወደ ተሻለ ደረጀ እንዲያድግም ለማድረግ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡
13 365
79 ኪ.ሜ የሚረዝመው የጅማ-አጋሮ-ዴዴሳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመስክ የሥራ ቅኝት ተጎብኝቷል።
በዚህም አጠቃላይ ፕሮጀክቱ በጥሩ መነቃቃት ላይ እንደሚገኝ ተገምግሟል።
ወደ አስፋልት ስራ የተሸጋገረ ሲሆን በእስከ አሁኑ የሥራ እንቅስቃሴ፣ 7 ኪ.ሜ የአስፋልት ማንጠፍ ሥራ ተከናውኗል።
ቀሪ የፕሮጀክቱን ክፍል ለማፋጠንም እየተሰራ ነው።
የአፈር ቆረጣ እና የሰብ-ቤዝ ንጣፍ እና የቤዝ-ኮርስ ሥራዎችም እየተከናወኑ ነው።
በመንገድ ግንባታው ምክንያት የትራንስፖርት መስተጓጎል እንዳይፈጠር ተለዋጭ መንገድ ተሰርቶ አገልግሎት በመስጠት ላይም ይገኛል፡፡
ግንባታውን አለም አቀፉ የሥራ ተቋራጭ ድርጅት ቻይና ሬይል ዌይ 20 ፈርስት ግሩፕ እያከናወነ ነው።
የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ኦሜጋ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ እና ፕሮሜ ኮንሰልታንት የተሰኙ አማካሪ ድርጅቶች በጣምራ እየሰሩ ነው ፡፡
ግንባታው የሚጠይቀው 1.5 ቢሊዮን ብር ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል።
ፕሮጀክቱ፣ በግንባታው ወቅት የገጠሙትን ተግዳሮቶች በመቅረፍ የፕሮጀክቱን እንቅስቃሴ ለማሻሻል በሥራ ተቋራጩ እና በኢመአ መካከል ተደጋጋሚ ውይይቶች ተደርገዋል።
ይህን ተከትሎ ሥራ ተቋራጩ የነበሩበትን እጥረቶች በመቀረፍ ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ተችሏል።
በተጨማሪም በፕሮጀክቱ የሚስተዋለው ከፍተኛ ቁጥር ያለው የወሰን ማስከበር ሂደትን የድርጊት መርኃ-ግብር በማዘጋጀት ንብረቶች በአፋጣኝ እንዲነሱ በቅንጅት ተሰርቷል።
የጅማ-አጋሮ-ዴዴሳ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ሲጠናቀቅ የአገሪቱን የደበብ እና የደቡብ ምዕራብ ክፍሎች ደረጃውን በጠበቀ የመንገድ መሠረተ-ልማት ያስተሳስራል፡፡
ከአዲስ አበባ ተነስቶ ጅማ የሚደርሰው መንገድ ቀጣይ በመሆን የአጋሮን እና የበደሌን ከተማን አቋርጦ በመቱ ጋምቤላ ለሚደርሰው አውራ-ጎዳና አካል ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በጅማ ውስጥ የሚገኙትን ጥንታዊዎችን የማና፣ የጎማ እና የጉማይ ወረዳዎች በቅርበት በማገናኘት የህዝብ ለህዝብ ትስስሩን ያሳልጣል።
ፕሮጀክቱ፣ መንገዱ ቀድሞ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በ2 ሰዓታት በማሳጠር፣ በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን የአዝርዕትና የቡና ምርቶችን በፍጥነትና በጥራት ለገበያ እንዲቀርቡ በማድረግ፣ የሀገርን የማሕበረሰቡን ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ሁኔታ በማሳደግ እረግድ የጎላ ሚናን ያበረክታል ።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
