ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 369 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 754,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 531 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 369 名订阅者。
根据 19 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 119,过去 24 小时变化为 19,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.59%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.42% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 423 次浏览,首日通常累积 2 060 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 21 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 369
订阅者
+1924 小时
+677 天
+11930 天
帖子存档
13 369
የወላይታን እና ዳውሮ ዞኖችን በአስፋልት ኮንክሪት መንገድ የሚያስተሳስረው የሶዶ-ኦሞ ወንዝ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሊጠናቀቅ ነው።
76 ኪ. ሜትር የሚረዝመው የሶዶ -ኦሞ ወንዝ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ከአጠቃላይ ኪ. ሜትር ውስጥ 95 በመቶ የተጠናቀቀ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን በቀጣይ ሁለት ወራት ተጠናቆ ሙሉ በሙሉ ለትራፊክ ክፍት ይሆናል።
አካባቢው ላይ በተደጋጋሚ የሚከሰተውን ከፍተኛ የመሬት መንሸራተት እና ናዳ ለመከላከል በሚያስችል መልኩ ሰፋፊ የአቃፊ ግንብ እና የጋብዮን ስራዎች ተከናውነዋል።
የሶዶ -ኦሞ ወንዝ ከዚህ ቀደም በጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ አድጎ የተገነባ ነው።
የመንገድ ፕሮጀክቱ ከሶዶ ከተማ 7 ኪ. ሜትር ላይ ተነስቶ ኦሞ ወንዝ ላይ የሚያበቃ ሲሆን የግንባታው መጠናቀቅ ወደ ግልገል ጊቤ 3 የኤሌትሪክ ማመንጫ ግድብ በተፈለገው ፍጥነት ለመድረስ ከማስቻሉም በላይ ሀገራዊ ፋይዳው የጎላ ነው ።
በአካባቢው የሚገኘውን የሰብል ምርቶች የሆኑትን ማሽላ ፣ የእንሰት ውጤቶች በተጨማሪም የአሳ ምርቶችን ትራንስፖርትን ተጠቅሞ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በተሻለ ዋጋ በመሸጥ አምራች ሸማቹን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።
ቀደም ሲል ከሶዶ ተነስቶ የኦሞ ወንዝ ለመድረስ መንገዱ ምቹ ባለመሆኑ ከ2 ሰዓት በላይ ይወስድ የነበረ ሲሆን በአሁን ሰዓት በተሽከርካሪ የሚደረገውን የትራንስፖርት ጉዞ በአማካኝ በግማሽ ቀንሷል።
ለአጠቃላይ ግንባታው ከአንድ ቢሊየን ሶስት መቶ አርባ ስምንት ሚሊየን ብር በላይ የጠየቀ ሲሆን ሙሉ ወጪውም በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው ።
ሁናን ሁንዳ ሮድ ኤንድ ብሪጅ ኮርፖሬሽን የተባለው የቻይና ኩባንያ ግንባታውን እያከናወነው ሲሆን የማማከርና የቁጥር ሥራውን ደግሞ የተባበሩት የምህንድስና አማካሪ ኃ/የተ/የግ/ማ እያካሄደው ይገኛል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ የጎን ስፋት በወረዳ 21.5 ሜትር በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 1ዐ ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው የተገነባው።
13 369
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የሞጆ - ሃዋሳ የክፍያ ፍጥነት መንገድ አካል የሆነውን የሞጆ - መቂ - ባቱ ምዕራፍ አንድ /92 ኪሜ /የመንገድ ፕሮጀክትን በይፋ መረቁ።
በመርሃ- ግብሩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድን ጨምሮ፣ የህዝብ ተወካዮች ምክት ቤት አፈጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ ፣ የኦሮሚያ ክልል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ፣ የደቡብ ብ/ብ/ህ/ክ/ ርእሰ መስተዳድር አቶ ዕርስቱ ይርዳው ፣ የትራንስፖርት ሚንስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ፣የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ፣ ከፍተኛ የፌዴራል እና የክልል ባለስልጣናት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ዕንግዶች ታድመዋል፡፡
የፍጥነት መንገዱ የአዲስ አበባ-ሞያሌ-ናይሮቢ-ሞምባሳ የመንገድ ኮሪደር አካል ሲሆን የኢትዮጵያን የወጪ ገቢ ንግድ እንቅስቃሴን በተሻለ ሁኔታ ለመጠቀም የሚያስች ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ።
ኢትዮጵያ ከጎረቤት አገራት ጋር የሚያስተሳስሩ የመንገድ መሰርተ ልማት ግንባታ በስፋት እየተከናወነች እንደሆነና ከአዳማ አዋሽ የሚዘልቀው መንገድ በቅርቡ በፍጥነት መንገድ ደረጃ የግንባታ ስራው እንደሚጀመርም አብስረዋል።
የትራንስፖርት ሚንስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ የምዕራፍ አንድ የሞጆ መቂ ባቱ መንገድ በቀጣይ በመስመሩ ላይ የሚገኙትን ወረዳዎች ፣ ከተሞች አማራጭ መንገድ ተጠቃሚ በማድረግና በግብርና በንግድ ስራ ላይ ለተሰማሩ የትራፊክ እንቅስቃሴውን ምቹ ስለሚያደርግ ሁለንተናዊ ፋይዳው የጎላ ነው ብለዋል።
ዘመናዊና ፈጣን መንገድ ለሀገራችን ሁለንተናዊ እድገት ከሚኖረው ፋይዳ አንፃር ከተለያዩ ሀገሮች የቀሰምነውን ልምድና ተሞክሮ መነሻ በማድረግ መንግስት በቀጣይ ከፍተኛ በጀት ለዘርፉ በመመደብ የፍጥነት መንገድ የማስፋፋቱ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በበኩላቸው የፍጥነት መንገዱ የግብርና ምርታማነትን በመስመሩ የሚገኙትን ሰው ሰራሽ እና የተፈጥሮ የቱሪስት መዳረሻዎችን ለጎብኚዎች ተደራሽ በማድረግ እረገድ ዘርፈ ብዙ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።
በመንገዱ ክልል ውስጥ ያሉ ተገንብተው አገልግሎት በመስጠት ላይ ላሉ እና በቀጣይ ለመገንባት በታቀዱ ግዙፍ የኢንዱስትሪ እና የአግሮፕሮሰሲንግ ፓርኮች ደረጃቸውን የጠበቀ መንገዶችን በማቅረብ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ በሚደረገው ጥረት የፍጥነት መንገዱ ጉልህ ሚናን እንደሚጫወት ገልጸዋል፡፡
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሀብታሙ ተገኘ በበኩላቸው የመንገዱ የግንባታ ስራ 6 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪን እንደጠየቀ ተናግረዋል።
አውስተው የሞጆ መቂ ባቱ የክፍያ የፍጥነት መንገድ ከነባሩ መንገድ ትይዩ በአዲስ መልክ ከእንስሳት እና ከሰዎች እንቅስቃሴ ነጻ በሆነ መልኩ የተገነባ እንደሆነም እና ከአዲስ አዳማ የፍጥነት መንገድ በመቀጠል ለአገራችን ሁለተኛው ፍጥነት መንገድ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የፍጥነት መንገዱ አራት መኪኖችን በአንድ ጊዜ በግራና በቀኝ በኩል የሚያስተናግ ሲሆን ግንባታው የክፍያ ጣቢያን ጨምሮ የተሸከርካሪ ሚዛን ቁጥጥር ጣቢያዎች እና በተለያዩ ቦታዎች የሬስቶራንት አገልግሎት መስጫ ፣ የተሽከርካሪ ጥገና ማከናወኛ (ጋራዥ) እና ለመንገዱ ተጠቃሚዎች የሚረዱ የተለያዩ አገልግሎት መስጫ መዕከላት የሚያካትት ነው ብለዋል።
የምዕራፍ አንድ የሞጆ - መቂ - ባቱ የክፍያ የፍጥነት መንገድ በሁለት ኮንትራት የተከፈለ ሲሆን አሱም ሞጆ - መቂ 56 ኪሜ እና መቂ -ባቱ 36 ኪ.ሜ ናቸው ፡
ከዛም ባለፈ 10 ሺ ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ከግብጽ ካይሮ ተነስቶ ደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ድርስ የተዘረጋው የታላቁ የትራንስ አፍሪካን ሃይዌይ የመንገድ ትስስር ክፍልም ነው ፡፡
ከዚህም ውስጥ ለኮንትራት አንድ ሞጆ - መቂ በአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ ፋይናስ የ4,219,913,161.65 ቢሊዮን ብር ብድር እና በኢትዮጵያ መንግስት በተመደበ በጀት የተሸፈነ ነው ፡፡
ቀጣዩ ምዕራፍ አንድ ኮንትራት ሁለት ከመቂ እስከ ባቱ ያለው መንገድ የተገነባው በ2, 132 547,087.55 ቢሊዮን ብር ሲሆን የኮሪያው ኤግዚም ባንክ (በብድር) እና ከኢትዮጵያ መንግስት በተመደበ በጀት ወጪው ተሸፍኗል፡፡
ኮንትራት አንድ የሞጆ- መቂ የክፍያ ፈጣን መንገድ ግንባታ ስራ ያከናወነው የስራ ተቋራጭ ቻይና ሬል ዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ ነው፡፡
የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ሊ ኢንተርናሽናል ሊሚትድ ካናዳ ከ ሊ አሶሲየት ሳውዝ ኤሲያ ፕራይቬት ሊሚትድ በጥምርት ሲሆን ዩናይትድ ኮንሰልት ኢንጅነርስ በንኡስ ተቋራጭነት ተሳትፏል፡፡
ኮንትራት ሁለት መቁ - ባቱ መንገድ የተገነባው በኮርያው ዴዎ ኢንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ነው፡፡
የማማከር ስራውን የተከናወነው ደግሞ ኪዮንግዶንግ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ሊሚትድ ፣ ኩንህዋ ኢንጂነሪንግ እና ኮንሰልቲንግ ኮርፖሬሽን ካንፓኒ ፣ ዶንግ ኢል ኢንጂነሪንግ ኮንሰልታንትስ ሊሚትድ ካምፓኒ ከኢትዮ ኢንፍራ ኢንጂነሪንግ እና ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ፒ ኤል ሲ በጋራ በመሆን ነው፡፡
ከሞጆ እስከ ባቱ በተዘረጋው 92 ኪሜ ውስጥ 6 ያህል ከነባሩ መንገድ ጋር የሚያገናኙ ማሳለጨዎች ተገንብቶለታል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ለእግረኛ ከመንገድ በታች እና በላይ መተላለፊያ 45 መተላለፊያ አሉት ፡፡
በተመሳሳይ መልኩ ተሸከርካሪዎች የሚጠቀሙበት 14 የተመረጡ ቦታዎች የመተላለፊያ የግንባታ ስራ ተካሂዶለታል፡፡
በአጠቃላይ ሞጆ መቂ ባቱን ጨምሮ ሃዋሳ ድረስ የሚዘልቀው 202 ኪ .ሜ የፍጥነት መንገድ የጎን ስፋቱ 32 ሜትር ነው፡፡
የመንገድ አካፋዩ በዚህ ደረጃ እንዲሰፋ የተደረገው በተቃራኒ አቅጣጫ ያለን ተሸከርካሪን በመለየት አደጋን ለማስወገድ አልያም ለመቀንስ ነው፡፡
የመንገዱ አጠቃላይ ወሰን 90 ሜትር ስፋት ያለው ነው፡፡
ይህም በቀጣይ ለሚኖረው የማስፋፋት ስራ በቂ ቦታ እንዲኖር የሚያስችል ይሆናል፡፡
በተጨማሪም የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂን መሰረት ባደረገ መልኩ ችግኞች ይተከሉለታል፡፡ በፍጥነት መንገዱ ለመጠቀም የተቀመጠለት የፍጥነት ገደብ በሰአት ከ80 እስከ 120 ኪሜ ነው፡፡
ከዛም ባለፈ በነባሩ መንገድ ተደጋጋሚ ብልሽት ሳቢያ ለአላስፈላጊ የተሸከርካሪ መለዋወጫ ይወጣ የነበረው ወጪ ከመቀነሱም ባለፈ በትራፊክ መጨናነቅ ምክንያት ያለአግባብ ይወጣ የነበረውን የነዳጅ ፍጆታን የሚያስቀር ነው፡፡
ከዛም ባለፈ 10 ሺ ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው ከግብጽ ካይሮ ተነስቶ ደቡብ አፍሪካ ኬፕታውን ድርስ የተዘረጋው የታላቁ የትራንስ አፍሪካን ሃይዌይ የመንገድ ትስስር አካል ነው ፡፡
13 369
በምስራቁ የሀገራችን ክፍል በተለይም በሶማሌ ክልል በቅድመ ግንባታ፣ ግንባታ እና ጥገና ያሉ ፕሮጀክቶችን አፈጻጸም እና በቀጣይ የአገሪቱ የመንገድ ልማት ውስጥ የክልል መንገድ ባለስልጣን መስሪያ ቤቶች የሚኖራቸውን ሚና እና ከዚሁ ጋር ተያይዞ ሊፈጠር የሚገባውን አቅም እና አደረጃጀት በተመለከተ የውይይት መድረክ በጅግጅጋ ከተማ ተካሄደ።
በውይይት መድረኩ ላይ የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ ፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ ክቡር አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣ የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ፣ የኢመባ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና የክልል የስራ አመራሮች ታድመዋል።
በመድረኩ ላይ በፌደራል ደረጃ ያለውን የሥራ ጫና መነሻ በማድረግ የተዘጋጀው የክልል መንገድ ባለስልጣን መስሪያ ቤቶች መነሻ አደረጃጀትና መዋቅር ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል።
ሰነዱም በመንገድ ግንባታ ሂደት ክልሎችን በአደረጃጀት፣ በመዋቅር፣ በአቅም ግንባታ በሚፈለገው ደርጃ ማሳደግ የመሰረተ ልማት አውታሩን ለማሳለጥ ሚናው የጎላ እንደሆነ ተገልጿል።
ከመሰረተ ልማት ዝርጋታ አኳያ በተለይም በአስፋልት መንገዶች ግንባታ በፌደራል(በኢመባ) ተወስኖ የነበረውን የስራ ጫና በማስቀረት እና ክልሎች እንዲሳተፉበት በማድረግ ረገድ የአደረጃጅት ሰነዱ እና ተያያዥ ፖሊሲዎች እና ስትራቴጂዎች ወሳኝ መሆናቸውን የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢ/ር ሃብታሙ ተገኘ አብራርተዋል።
በትግበራ ወቅት ሊታዩ እና ሊካተቱ ይገባቸዋል ያሏቸውን አንኳር ነጥቦችንም የክልሉ የስራ ሃላፊዎች አንሰተዋል።
የክልሉ መንግስት የመንገድ ፕሮጀክቶች በተለያዩ ተግዳሮቶች እንዳይስተጓጎሉ እያደረገ ያለው ድጋፍ እና ትብብር የሚያስመሰግን መሆኑን የገለፁት የትራንስፖርት ሚኒስቴር ዴኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ መንግስት በመሰረተ ልማት ዝርጋታ የክልሎችን አቅም ለመገንባት የሚያስችል መጠነ ሰፊ ስራዎችን እንደሚያከናውንም አረጋግጠዋል።
በተለይም የክልሎችን ሚና እና ሃላፊነት በግልጽ አስቀምጦ ይበልጥ የሚያጠናክር ሰነድ መዘጋጅቱ የነበሩ ውስንነቶችን በመቅረፍ ለሀገራዊ የመንገድ የመሰረተ ልማት ግንባታ ፋይዳው ዘርፈ ብዙ እንደሆነም አስታውቀዋል።
የሱማሌ ክልል ርእሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ የመንገድ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ ተጀምረው እንዲሁም ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ እንዲጠናቀቁ አስፈላጊው ክትትል እንዲደረግ አሳስበው በክልሉ በኩል የመንገድ ወሰን ማስከበር እና ተዛማጅ ጉዳዮች ተግዳሮት እንዳይሆኑ አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል።
በግንባታ ላይ የሚገኙ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጻም እና እያጋጠማቸው ያሉ ተግዳሮቶች ላይ ዝርዝር ምክክር ተካሂዷል።
በውይይቱ ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ ያጋጠሙ ችግሮችን ይበልጥ ተናቦ ለመፍታት የጋራ አቅጣጫን አስቀምጠዋል።
በቀጣይ ለሚተገበሩ እቅዶችና ማሻሻያዎች እንዲሁም አሁን በግንባታ ላይ ለሚገኙ ፕሮጀክቶች መጠናቀቅ ክልሉ እያደረገ የሚገኘውን ክትትልና ድጋፍ የበለጠ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ርዕሰ መስተዳድሩ አረጋግጠዋል።
13 369
104.3 ኪ.ሜ. የሚረዝመዉ የጅግጅጋ-ቱሉ -ሉዋንጃ-ዱሉአድ-ሳምክብ- ሀርሙካሌ መገንጠያ የመንገድ ግንበታ ፕሮጀክት በመልካም አፈጻጸም ላይ ይገኛል።
ዛሬ አጠቃላይ የመንገድ ግንባታውን የተመለከተ የመስክ ቅኝት በክፍተኛ የሰራ ሀላፊዎች ተካሄዶል።
በዚሁ የመስክ የስራ ቅኝት መርሃ-ግብር ላይ የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተግኝ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡሰማን ፋራህ እንዲሁም የኢመባ የስራ ሀላፊዎችና የሚመለከታቸው አካላት ታድመዋል።
የግንባታው አሁናዊ አጠቃላይ አፈፃፀሙ ከዕቅዱ አኳያ መልካም መሆኑም ተገምግሟል።
ከዲዛይን ማሻሻል እና ከወስን ማስከበር ጋር ተያይዘው የነበሩ ተገዳሮቶች አሁን በመፈታታቸው በቀጣይ የተሻላ አፈጻጻም እንደሚመዘግብም አረጋገጠዋል።
በመንገድ ፕሮጀክቱ የአፈር ቆረጣ ስራዎች፤ የአፈር ጠረጋ እና ድልዳሎ እንዲሁም የድልድይ እና የውሀ መፋሰሻ ቦዮችን የመገንባት ስራ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
የዚህን የመንገድ ፕሮጀክት በቀጣይ የመንገዱን ክፍሎች አስፋልት የማልበስ ስራዎችን ለማካሄድ ይረዳ ዘንድ ከወዲሁ የጠጠር መፍጨት ስራዎች እና አስፈላጊዉ ቅድመ ዝግጅት እየተሰራ መሆኑን ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎቹ ተመልከተዋል፡፡
ፕሮጀከቱ ከጅግጅጋ ወደ ደወሌ ለመጓዝ ይውስድ የነበረውን ጊዜ እና ወጪን በመቀነስ እስትራቲጂካዊ ጠቀሜታ ያለው መሆኑን ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎቹ ተናግረዋል ።
የኢመባ ዋና ዳይሬከትር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ የንግድ ማዕከል የሆነችዉን ጅግጅጋ ከተማን በቀጥታ ከጅቡቲ ጋር ቀልጣፋ በሆነ የትራንስፖርት አገልግሎት በማስተሳሰር የጎላ አሰተዋጾ ያለው በመሆኑ ፕሮጀከቱ እንዲፋጠን ኢመባ ድጋፍ ቁጥጥሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ በበኩላቸው የመስክ ቅኝቱ ዋና ዓላማ ይህ ሀገራዊ እና ቀጠናዊ ፋይዳው የጎላ ፕሮጀክት በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቆ ጥቅም ላይ እንዲውል ለማስቻል በመሆኑ ልዩ ትክረት እንዲሰጠው ነው ብለዋል ።
በግንባታ ሂደት ለሚያጋጥሙ ተገዳሮቶች የቅርብ ክትትል ድጋፍና ቁጥጥሩ ተጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስበዋል።
በአካባቢዉ የጤና የትምህርትና ማህበራዊ እንቅስቃሴዎችን በተሳለጠ የመንገድ መሰረተ ልማት ተደራሽ በማድረግ የመንገዱ መገንባት የሚኖረዉ አስተዋጽዎ የጎላ በመሆኑ የክልሉ አመራርም ድጋፉን ይበልጥ እንዲያሳድግም ጠይቀዋል፤
ግንባታውን የሚያካሂደው ቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የተባለ ዓለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን የመንገዱን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር እየሰራ ያለው ስታዲያ የምህንድስና ስራዎች አማካሪ ኃ/የተ/የግል ማህበር ነው፡፡
የመንገድ ኘሮጀክቱ እየተገነባ የሚገኘው ከመንግስት በተመደበ ከአንድ ቢሊየን
አምስት መቶ ሀምሳ አንድ ሚሊየን ብር በላይ ነው
የመንገድ ግንባታዉ በገጠር 10 ሜትር ስፋት ሲኖረዉ በወረዳና ዞን ተጨማሪ ስፋት እንዲኖረዉ ተደርጎ የሚገነባ ይሆናል፤ በተጨማሪም ፕሮጀክቱ የስድስት ድልድዮች ግንባታንም ያካተተ ነው፡፡
በኮንትራቱ ዉል መሰረት የመንገድ ግንባታዉ በሶስት ዓመት ዉስጥ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ይሆናል::
13 369
የሀዘን መግለጫ
በቀድሞ አውራ ጎዳና በአሁኑ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በፕላንና ፕሮግራም መምሪያ ሃላፊነት፣ በልዩ ልዩ ሀገራዊና ተቋማዊ የጥናትና ምርምር ስራዎች ላይ በመሳተፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱት እንዲሁም ከ1968-1980 ዓ.ም ደግሞ የትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ሆነዉ ያገለገሉት አቶ ዩሱፍ አህመድ መሀመድ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው በ 76 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
አቶ ዩሱፍ አህመድ ሀገራቸውን እና አፍሪካን በመንገድ ልማት ፥ በትራንስፖርትና ኮሚኒኬሽን ዘርፍ ከ35 ዓመታት በላይ አገልግለዋል።
አቶ ዩሱፍ የሦስት ልጆች አባትም ነበሩ።
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ከፍተኛ የማኔጅመንት አባላትና መላው ሰራተኛ ለመለዉ ቤተሰብና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ይመኛል።
13 369
የሀዘን መግለጫ
በቀድሞ አውራ ጎዳና በአሁኑ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን በፕላንና ፕሮግራም መምሪያ ሃላፊነት፣ በልዩ ልዩ ሀገራዊና ተቋማዊ የጥናትና ምርምር ስራዎች ላይ በመሳተፍ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱት እንዲሁም ከ1968-1980 ዓ.ም ደግሞ የትራንስፖርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ሆነዉ ያገለገሉት አቶ ዩሱፍ አህመድ መሀመድ ባደረባቸው ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው በ 76 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።
አቶ ዩሱፍ አህመድ ሀገራቸውን እና አፍሪካን በመንገድ ልማት ፥ በትራንስፖርትና ኮሚኒኬሽን ዘርፍ ከ35 ዓመታት በላይ አገልግለዋል።
አቶ ዩሱፍ የሦስት ልጆች አባትም ነበሩ።
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ከፍተኛ የማኔጅመንት አባላትና መላው ሰራተኛ ለመለዉ ቤተሰብና ወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ይመኛል።
13 369
የሶዶ ዲንኬ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ወደ አስፋልት ንጣፍ ስራ ተሸጋገረ፡፡
በአካባቢዉ እየተገነቡ የሚገኙ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን የተመለከተ የመስክ ቅኝት ተካሄዷል፡፡
በፕሮጀከቱ አሁናዊ የግንባታ እንቅስቃሴ ከፍተኛ የአፈር ቆረጣ፤ የሰብ ቤዝ ፤ የፍሳሽ ማሶገጃ ቱቦ ቀበራ እና የድልድይ ስራ ከሞላ ጎደል እየተገባደደ ነው።
በእቅዱ መሰረትም እስካሁን 18 ኪ.ሜ የአስፋልት ንጣፍ ስራ የተከናወነ ሲሆን ለአሰፋልት ንጣፍ ዝግጁ በሆኑ የፕሮጀከቱ ክፍሎችም በትኩረት እየተሰራ ነው።
በአጠቃላይ አሁናዊ የግንባታ አፈጻጸሙ 41.34 በመቶ የደረሰ ሲሆን ይህም በተያዘለት የግዜ ገደብ እንደሚጠናቀቅ ያመላክታል፡፡
የሶዶ ዲንኬ የአስፋልት መንገድ ግንባታ 86.22 ኪሜ ርዝማኔ አለዉ፡፡
ግንባታዉን እያከናወነ የሚገኘዉ China Railway Seventh Group LTD ሲሆን የመንገዱን የማማከርና የቁጥጥር ስራዉን የሚያካሄደዉ JV Newtech Consulting Group ከ Net Consulting Engineers Plc ጋራ በጋራ ነዉ፡፡
የዚህ መንገድ የግንባታ ወጪ አንድ ቢሊዮን አምሳ አራት ሚሊዮን ሶስት ሺህ ሲሆን አጠቃላይ የግንባታ ወጪዉም በኢትዮጵያ መንግስትና በአፍሪካ ልማት ባንክ የሚሸፈን ይሆናል፡፡
በኮንትራቱ ዉል መሰረት የመንገድ ግንባታዉ በአራት ዓመት ዉስጥ ተጠናቆ ለመንገዱ ለተጠቃሚዎች ክፍት ይሆናል፡፡
የመንገድ ግንባታዉ በገጠር 10 ሜትር፤ በወረዳ 12 ሜትር እና በዞን 26 ሜትር የጎን ስፋት ይኖረዋል፡፡
በተያያዘ ዜናም የዚሁ መንገድ አካል የሆነዉና 75.9 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የዲንኬ - ሳውላ - ሸፊቴ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ስራም በመስከ ምልከታዉ ተቃኝቷል፡፡
በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅ ታስቦ የተጀመረው ይህዉ የመንገድ ፕሮጀክት አሁን ላይ በጥሩ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል ።
በእስካሁኑ የስራ እቅድ የአፈር ቆረጣና ሙሌት፣ የሰብ ቤዝና ቤዝ ኮርስ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ።
አስፋልት የማንጠፍ ስራም የተጀመረ ሲሆን በቀጣይ አጠናክሮ ለማስቀጠል በርካታ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተሰሩ ነው ።
በፕሮጀከቱ የግንባታ ውል መሰረት አስራ ሁለት ድልድዮችን ያካተት ሲሆን የሁለት ድልድዮች ግንባታም ጎን ለጎን እየተገባደደ ይገኛል፡፡
በአጠቃላይ የሚኖረው የጎን ስፋትም የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በዞን 26፣ በቀበሌ 12፣ በገጠር 10 ሜትር ይኖረዋል፡፡
የዲንኬ - ሳውላ - ሸፊቴ የግንባታ ስራን እያከናወነ የሚገኘው አለም አቀፉ የስራ ተቋራጭ ቤጂንግ አርባን ኮንስትራክሽን ግሩፕ ካምፓኒ ነው፡፡
የግንባታዉን የማማከርና ቁጥጥር ስራውን የሚያካሂዱት አራት አማካሪ ደርጅቶች ሲሆኑ፡- እነዚህም ሶሱንግ ኢንጅነሪንግ ኃላ/የተ/የግ/ማ ፣ኮሪያ ኮንሰልታንትስ ኢንተርናሽናልኃላ/የተ/የግ/ማ ፣ዳሳን ኮንሰልታንትስ ኃላ/የተ/የግ/ማ እና ኔት ኮንሰልትስ ኃላ/የተ/የግ/ማ በጋራ በመሆን ነዉ፡፡
የግንባታ ወጪውም 1,020,177,271.11 የሚፈጅ ሲሆን በአፍሪካ ልማት ባንክ እና በኢትዮጵያ መንግስት በጋራ የሚሸፈን ይሆናል፡፡
አጠቃላይ ፕሮጀከቶቹ ሲጠናቀቁ የወላይታን ዞን ከጋሞ እና ጎፋ ዞን ጋራ በቅርበት ያስተሳስራሉ፡፡
በተጨማሪም በዞኖቹ መካከል ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገትን በመፍጠር የትራንስፖርት እንቅስቃሴን እንዲስፋፋ ያግዛል፡፡
የዚህ መንገድ መገንባት ወደ ኦሞ ኩራዝ የስኳር ፋብሪካ ፕሮጀክት ለሚደረጉ ጉዞዎች አማራጭ መንገድ በመሆን ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡
በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የተለያዩ ምርቶች እንደ ቡና እና የተለያዩ ፍራፍሬዎች እንዲሁም የቀንድ ከብቶችና ፊየሎችን ጨምሮ በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ አምራች ሸማቹን ብሎም አርሶ አደሩን ይበልጥ ተጠቃሚ ያደረጋል
በተጨማሪም የቱሪስት መስህብ መዳረሻ የሆነውን የማዜ ፓርክን ለመጎብኘት ለሚመጡ የሀገር ዉስጥና የውጪ ጎብኚዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ሀገሪቱ ከቱሪዝም ኢንዱስትሪ የምታገኘውን የውጪ ምንዛሬ ገቢን ለማሳደግ ዓይነተኛ የሆነ ሚና ይኖረዋል፡፡
13 369
ከአምስት ወራት በፊት የተጀመረው የጅግጅጋ ገለለሽ -ደገሃምዶ -ሰገግ የአሰፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ኮንትራት ሁለት በመፋጠን ላይ ነው።
በስፍራው የሚገኙ የመንገድ የግንባታ ፕሮጀከቶችን የስራ እንቅስቃሴ የተመለከተ የመስክ ቅኝት ሰሞኑን ተካሂዳል።
በዚህም የጅጅጋ ገለለሽ ደገሃምዶ ሰገግ በጥሩ ደረጃ እየተገነባ መሆኑ ተመላክቷል ።
የስራ ተቋራጩ የካፕ ግንባታን ጨምሮ ለግንባታ ሂደት የሚዉሉ የተለያዩ ማሽነሪዎች ተከላን አጠናቆ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ገብቷል፡፡
በአሁኑ ወቅት የአፈር ቆረጣ ስራዎች፤የአፈር ጠረጋ እና ሙሌት ፤ የዉሃ መፋሰሻ ቱቦዎች ማምረት ብሎም የአስፋልት ጠጠር መፍጫ ማሽን ተከላ እየተከናወነ ይገኛል፡፡
ግንባታው እስከ 32 ሜትር እርዝመት ያላቸው አምስት ድልድዮች ስራንም ያካተተ ነው።
በአጠቃላይ አሁናዊ የግንባታ እቅድ አፈጻጸሙ 11 በመቶ የደረሰ ሲሆን ይህም ቃል እንደተገባው ፕሮጀከቱን ፈጥኖ ለማጠናቀቅ እንደሚያስችል ታምኖበታል። ።
መንገዱን በአንድ ቢሊየን ስምንት መቶ ሃያ ስምንት ሚሊየን ብር በላይ ጨረታውን አሸንፎ ግንባታውን እያከናወነ ያለው ቤአኤካ ጄኔራል ቢዝነስ የተባለው አገር በቀል የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን ፤
የፕሮጀከቱን የማማከርና ቁጥጥር ሰራዉን የሚያካሄደዉ ደግሞ ሲ ቴክ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማ ነዉ፡፡
የጅግጅጋ-ገለለሽ_ደገሀምዶ ሰገግ መንገድ 109.82 ኪሎ ሜትር ርዝመት አለው።
ለግንባታ የሚያስፈልገውን ሙሉ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል
የመንገድ ፕሮጀክቱ በሶስት ዓመት ከስድስት ወራት ተጠናቆ ለህዝቡ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ይጠበቃል።
በተያያዘ ዜናም በመስክ የስራ ቅኝቱ የዚሁ የመንገድ ከፍል የሆነው እና 52.2 ኪ.ሜ የሚረዝመው ኮንትራት ሶስት የደገሃምዶ -ሰገግ የመንገድ ግንባ በጥሩ የስራ አፈጻጻም ላይ ይገኛል ።
የመንገድ ፕሮጀከቱ የሰብ ቤዝ ስራ፤የአፈር ቆረጣ ፤ የአፈር ጠረጋ እና ሙሌት እንዲሁም የውሀ ማፍሰሻ ቦዮችን የመገንባት ስራ እየተካሄደ ነው፡፡
ግንባታውን የሚያካሂደው ማርካን ትሬዲንግ ኃላ/የተ/የግ/ማ የተባለ አገር በቀል የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን
የመንገዱን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር እየሰራ የሚገኘው ብርሀን ኮንስትራክሽን ዲዛይን ኮንሰልታንት ኃ/የተ/የግል ማህበር ነው፡፡
የአስፋልት ኮንክሪት መንገዱ እየተገነባ የሚገኘው ከመንግስት በተመደበ 768 ሚሊየን 698ብር በጀት ነው።
በኮንትራቱ ዉል መሰረት የመንገድ ግንባታዉ በሶስት ዓመት ዉስጥ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ይሚሆን ይሆናል፡፡
የጅግጅጋ ገለለሽ ደጋሃመዶ -ሰገግ መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ጅግጂጋ ከሚወስደው ዋና መንገድ ጋር ዘመናዊ በሆነ የአስፋልት መንገድ ተደራሽ የሚያደርግ ነው
በክልሉ በርካታ ወረዳዎችንና ቀበሌዎችን የሚያስተሳሰር በመሆኑ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳው የላቀ ያደረጋዋል።
በተለይም በአካባቢው ያሉትን አርብቶ አደር የማህበረሰብ ክፍሎች የእንሰሳት ሀብታቸውን በቀላሉ እና በተሻለ ዋጋ ወደ ማዕከላዊ ገበያ አውጥቶ በመሸጥ ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል ።
የዚሁ የመንገድ አካል የሆነው የጅግጅጋ-ገለለሽ 55.4 ኪ.ሜ ኮንትራት አንድ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ከወራት በፊት ለትራንስፖርት አገልግሎት ክፍት መሆኑ ይታወሳል ።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
