ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 307 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 759,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 546 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 307 名订阅者。
根据 15 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 88,过去 24 小时变化为 2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.23%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.41% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 352 次浏览,首日通常累积 2 050 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 16 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 313
订阅者
+224 小时
+297 天
+8830 天
帖子存档
13 313
የሮቤ - ጋሰራ - ጊኒር የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ዳግም ተጀመረ
አዲስ አበባ ታህሳስ 06 ፣ 2018 (ኢመአ)120.922 ኪሎሜትር የሚረዝመው የሮቤ - ጋሰራ - ጊኒር የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ዳግም ተጀምሯል፡፡
ቀደም ሲል በሁለት ምዕራፍ ተከፋፍሎ ሲሰራ የነበረው የመንገድ ፕሮጀክት የሥራ ተቋራጮች ባሳዩት ደካማ አፈጻጸም ምክንያት ግንባታው እንዲቋረጥ መደረጉ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የፕሮጀክቱን ግንባታ ለማስቀጠል ባደረገው ከፍተኛ ጥረት የመንገዱ ግንባታ ቻይና ፈርስት ሃይዌይ ኢንጂነሪንግ በተባለ የሥራ ተቋራጭ ለማስጀመር ተችሏል፡፡
የፕሮጀክቱን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ ደግሞ ፕሮሚነንት ኢንጅነሪንግ ሶልዩሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር በማከናወን ላይ ነው።
አሁን ላይ የአፈር ሙሌት፣ የቆረጣ፣ የካፒንግ፣ የውኃ ማፋሰሻ ቦዮች ቀበራ፣ የመኪና መሸጋገሪያ፣ የፍሳሽ ቱቦዎች ማምረት እንዲሁም የሰብ ቤዝ ሥራዎች እየተሰሩ ናቸው፡፡
የፕሮጀክቱን ግንባታ በተያዘለት ጊዜ እንዲከናወን ለማስቻል የባሌ ሮቤ የግንባታ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት የባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ጥረት እያደረገ ይገኛል።
ለግንባታው የሚውለው 9,070,900,534.49 ብር (ዘጠኝ ቢሊዮን ሰባ ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሺ አምስት መቶ ሰላሳ አራት) በፌደራል መንግሥት የሚሸፈን ነው።
መንገዱ በወረዳ 21.5 ሜትር፣ በቀበሌ 12 እና 17 ሜትር እንዲሁም በገጠር 10 ሜትር አጠቃላይ የጎን ሥፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ነው።
የሮቤ - ጋሰራ - ጊኒር የመንገድ ግንባታ ሲጠናቀቅ የባሌ ዞን፣ ምስራቅ ባሌ ዞን፣ የሲናና፣ አጋርፋ፣ ጋሰራን እና ጊኒር ወረዳዎች በተጨማሪ አምስት የከተማ አስተዳደርን በማስተሳሰር የመንገዱ ተጠቃሚዎች ቀልጣፋ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል።
ከዚህም ባሻገር በአከባቢው የሚመረቱ እንደ ስንዴ፣ ገብስ፣ ጤፍ የመሳሰሉ ምርቶችን እንዲሁም የተለያዩ ፍራፍሬዎችን ለገበያ ለማቅረብ ብሎም ለቱሪዝም መዳረሻዎች አማራጭ መንገድ በመሆን ከፍተኛ ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ይሰጣል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
13 313
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ የመልካ ጂሎ-አዋሽ የፍጥነት መንገድ ግንባታን ለማካሄድ የሚያስችል የድጋፍ ስምምነት አካሄዱ
አዲስ አበባ ታህሳስ 03፣ 2018 (ኢመአ) የኢትዮ-ጅቡቲ የመንገድ ኮሪደር አካል የሆነውን የመልካ ጂሎ-አዋሽ 67 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ለመገንባት የሚያስችል የ184 ሚሊዮን ዶላር የድጋፍ ስምምነት በኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ አማካኝነት ተካሂዷል፡፡
የዚህ መንገድ የመጀመሪያ ምዕራፍ የሆነው 61.55 ኪሎ ሜትር የአዳማ-መልካ ጂሎ የፍጥነት መንገድ ግንባታ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ የዚህ መንገድ ቀጣይ ምዕራፍ የሆነውን እና ግንባታውን ለማስጀመር ከአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር የድጋፍ ስምምነት የተካሄደለትን ኮንትራት ሁለት የመልካ ጂሎ-አዋሽ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ለማስጀመር አለምአቀፍ ጨረታ ወጥቶ በሂደት ላይ ይገኛል፡፡
ይህ መስመር ከ90 በመቶ በላይ የሚሆነው የኢትዮጵያ የባህር የወጪ-ገቢ ንግድ የሚካሄድበት እጅግ ወሳኝ የመንገድ ኮሪደር ነው፡፡ በመሆኑም ለአገራችን የሎጂስቲክስ ፍሰት ፣ ለክልላዊ ትስስር እንዲሁም በአፍሪካ ቀንድ ያለውን የኢኮኖሚ ውህደት ለማጠናከር እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡
ከዚህም ባሻገር ኢትዮጵያ ፣ ጅቡቲ እና ደቡብ ሱዳንን የሚያካትት ሁለገብ ፕሮጀክት ሲሆን በአፍሪካ ቀንድ ያለውን የትራንስፖርት ትስስር ለማሻሻል ታሳቢ ተደርጎ የሚገነባ ነው፡፡ በተጨማሪም በኮሪደሩ ላይ ቀልጣፋ እና ውጤታማ የትራንስፖርት ስርዓት እንዲኖር በማድረግ እና በአካባቢው ያሉ አገራትን በንግድ እና በሌሎች ዘርፎች እርስ በእርስ በማስተሳሰር የአገራቱን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ልማት ያሳድጋል ተብሎ ይታመናል፡፡
የዚሁ መንገድ ቀጣይ ክፍል የሆነውን የአዋሽ-መኢሶ መንገድ ግንባታ ለማካሄድ የሚያስችለውን የፋይናንስ ምንጭ የማፈላለግ ስራ እየተከናወነ ሲሆን ፣ የመኢሶ-ድሬደዋ 144 ኪሎ ሜትር የፍጥነት መንገድ ግንባታ ደግሞ በዚሁ በጀት ዓመት በይፋ መጀመሩ ይታወሳል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
13 313
የደብረ ብርሃን - ደነባ - ለሚ መገንጠያ እና ጅሁር - ደነባ የመንገድ ግንባታ በተሻለ አፈፃፀም ላይ ነው
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 1፣ 2018 (ኢ መ አ) :- 108.26 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የደብረ ብርሃን - ደነባ - ለሚ መገንጠያ እና ጅሁር - ደነባ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ሥራ በተሻለ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
የመንገድ ግንባታ ሥራ ሁለት ክፍሎች ያሉት ሲሆን የመጀመሪያው የደብረብርሃን - ደነባ - ለሚ መገንጠያ የመንገድ ክፍል 69.85 ኪሎሜትር እንዲሁም የጅሁር - ደነባ ሁለተኛው የመንገድ ክፍል 38.41 ኪሎ ሜትር ይሸፍናል፡፡
በእስካሁኑ የፕሮጀክቱ የግንባታ እንቅስቃሴ የአፈር ሙሌት ፣የቆረጣ ፣አነስተኛ ድልድይና የቱቦ ቀበራ፣ የካፒንግ፣ የሰቤዝ ንጣፍ፣ የቤዝ ኮርስና የአስፓልት ጠጠር መፍጨት፣ የቤዝኮርስ እንዲሁም ከ16.77 ኪሎ ሜትር በላይ የአስፋልት ኮንክሪት ንጣፍ ለማከናወን ተችሏል፡፡
ግንባታውን የሚያካሂደው የሥራ ተቋራጭ ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ኃ.የተ.ግ.ማህበር ሲሆን የማማከርና የቁጥጥሩን ሥራ ኤቢኤም ኢንጂነርስ እና ፕላስ ኮንሰልት ኃ.የተ.ግ.ማህበር (ንዑስ ኮንሰልታንት) በመሆን እያከናወኑት ይገኛል፡፡
ለመንገዱ ግንባታ የሚውለው 3,613,766,908.69 ሶስት ቢሊዮን ስድስት መቶ አስራ ሶስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ስልሳ ስድስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ስምንት ብር በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡
መንገዱ በዞን 25.5 - 35.5 ሜትር ፣በወረዳ 21.5 ሜትር ፣በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር ከ 10- 11 ሜትር አጠቃላይ የጎን ስፋት አለው፡፡
የመንገድ ሥራው ሲጠናቀቅ የአካባቢው ማህበረሰብ የትምህርት፣ ጤና እና መሰል ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ግልጋሎቶችን በአፋጣኝ እንዲያገኙ የሚያስችል ነው፡፡
ከዚሁም ባሻገር በሃገሪቱ ትልቁ የለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ፣ የደብረብርሃን ኢንዱስትሪያል ፓርክ እና ሌሎች በደብረብርሃን ሪጂዮ-ፖሊታን ከተማ አካባቢ የሚገኙ የማኑፋክቸሪንግ ፋብሪካዎች እና ኢንዱስትሪዎች ጥሬ ዕቃዎቻቸውንና የተለያዩ ምርቶቻቸውን ለማጓጓዝ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡
በተጨማሪም ከሙከጡሪ - አዲስ አበባ - ደብረብርሃን እንዲሁም ወደ አዋሽ አርባ - ጂቡቲ ለሚጓዙ የመንገድ ተጠቃሚዎ ች አማራጭ መስመር በመሆን ያገለግላል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
13 313
የመላው አመራር ውጤታማነት የሚረጋገጠው በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርሙ ስኬታማነት ነው - ሚንስትር ጫልቱ ሳኒ
አዲስ አበባ፣ ኅዳር 24፣ 2018 (ኢ መ አ) :- በየደረጃው የሚገኝ መላው አመራር ውጤታማነት የሚረጋገጠው በመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርሙ ስኬታማነት ነው ሲሉ የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚንስትር ጫልቱ ሳኒ ተናግረዋል።
የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚንስቴር እና ተጠሪ ተቋማት የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም ባለፉት 4 ወራት ውስጥ የተከናወኑ ሥራዎችን በዓለምገና ኢንጅነሪንግ ማሠልጠኛ ገምግሟል።
በዚሁ ወቅት ሚንስትሯ የሪፎርሙ ግብ ነጻ ፣ ገለልተኛ እና ተጠያቂነት የሰፈነበት የአገልግሎት አሰጣጥ መዘርጋት እንደኾነ አስረድተዋል።
ተቋማት ብቁ ፣ ብዝኅነትን የተላበሱ ፣ የዜጎችን ክብር የሚመጥኑ እንዲሁም ትውልድን የሚሻገሩ እንዲኾኑ ማስቻል ነው ብለዋል። ሪፎርሙ ከዚህ ቀደም ከነበሩት የተለየ፣ ግልጽ እና የጠራ ዓላማ የተቀመጠለት መኾኑንም ገልጸዋል።
ባለፉት ጊዜያት በዝግጅት ምዕራፉ ውጤታማ ሥራዎች መከናወናቸውን ያነሱት ሚንስትሯ፤ ለሪፎርሙ መሳካት መላው አመራር በትኩረት ሊሠራ ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
በወቅቱ የሚንስቴር መ/ቤቱ ተጠሪ ተቋማት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ፣ የኮንስትራክሽን ባለሥልጣን እንዲሁም የኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት የ4 ወራት ሪፖትርታቸውን አቅርበዋል።
ባለፉት 4 ወራት ውስጥ በዋናነት በተለያየ ደረጃ ሥራውን የሚያከናውኑ ኮሚቴዎች የማዋቀር ፣ የተለያዩ የአቅም ግንባታ እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎች እንዲሁም በርካታ የዝግጅት ሥራዎች መከናዎናቸው ተመላክቷል።
ከዚሁ ጎን ለጎን የሥራ እና ክህሎት ሚንስቴር የመንግስት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ሞዴል በከተማና መሠረተ ልማት ሚንስትር ደኤታ የትምጌታ አሥራት (ዶ/ር) ቀርቦ ልምድ እና ተሞክሮ ተወስዶበታል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
13 313
የነቀምት - ቡሬ ሎት 3 አጋምሳ - ቡሬ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 63 ነጥብ 49 በመቶ ደረሰ።
አዲስ አበባ፤ ህዳር 24፤ 2018 (ኢመአ)፦ የአማራ እና የኦሮሚያ ክልሎችን የሚያገናኘው የነቀምት - ቡሬ ሎት 3 አጋምሳ - ቡሬ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት 63 ነጥብ 49 በመቶ ደርሷል፡፡
84.55 ኪ.ሜ ርዝመት ባለው በዚህ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ላይ እስካሁን የአፈር ሙሌት ፣ የቆረጣ ፣ የአነስተኛ ድልድይና የቱቦ ቀበራ፣ የቤዝ ኮርስና የአስፓልት ጠጠር መፍጨት፣ የድጋፍ ግንብ ፣የሰቤዝ ፣ የቤዝኮርስ እና 43.13 ኪ.ሜ የሚሆን አስፋልት ንጣፍ ሥራ በመከናወን ላይ ናቸው።
የፕሮጀክቱ ሥራ በቻይናው ቾንግቺንግ ኢንተርናሽናል ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን እየተከናወነ ነው። የማማከርና ቁጥጥር ሥራው ደግሞ በኩንሃ ኢንጅንሪንግና ኮንሰልቲንግ፣ ኮሪያ ኤክስፕረስዌይ ኮርፖሬሽን እና ኢትዮ ኢንፍራ አንጅነሪንግ በትብብር እየተካሄደ ይገኛል።
መንገዱን ለመገንባት 2,291,551,346.32 ሁለት ቢሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሃምሳ አንድ ሺህ ሦስት መቶ አርባ ስድስት ብር ወጪ የሚሸፈነው ከዓለም ባንክ በተገኘ ብድር ነው።
የመንገዱ አጠቃላይ የጎን ስፋት በወረዳ 21.5 ሜትር፣ በቀበሌ 14 ሜትር፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር ተደርጎ በመገንባት ላይ ነው።
የፕሮጀክቱ ግንባታ ሲጠናቀቅ በአማራ ክልል የምዕራብ ጎጃም ዞን የቡሬ ወረዳ እና በኦሮሚያ ክልል ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አምሩ ወረዳ መካከል የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቶችን በይበልጥ ያጠናክራል። እንዲሁም የጎዳ ማሩ፣ ሚግር፣ ጆጊ፣ ጣቦ፣ ሶንቶም፣ ቁጭ፣ ዛልማ፣ ባሲ እና አለፋ ቀበሌዎችን ያገናኛል።
በተጨማሪም በአካባቢው የሚመረቱ እንደ ቡና፣ ሰሊጥ፣ ቦሎቄ፣ በርበሬ፣ ፍራፍሬዎች፣ የግራናይትና ማርብል ማዕድናት እና ሌሎች የግብርና ምርቶች ያለምንም መስተጓጎል ለገበያ እንዲቀርቡ በማድረግ ለክልሎቹ ኢኮኖሚ ትልቅ አስተዋፅዖ ይኖረዋል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
13 313
የደብረማርቆስ - ደብረኤሊያስ - ተምጫ እና ጭምት መገንጠያ - ጭምት ከተማ መንገድ ግንባታ ዳግም ተጀመረ
አዲስ አበባ፣ ኅዳር 20፣ 2018 (ኢ መ አ) :- በአማራ ክልል ምሥራቅ ጎጃም ዞን ከሁለት ዓመታት በፊት ግንባታው ቆሞ የነበረው የደብረማርቆስ - ደብረኤሊያስ - ተምጫ እና ጭምት መገንጠያ - ጭምት ከተማ መንገድ ግንባታ ዳግም ተጀምሯል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ በ2012 ተጀመሮ ሲከናወን የቆየ ቢኾንም ከ2 ዓመታት በፊት የግንባታው አጠቃላይ አፈጻጸም 52 ነጥብ 8 በመቶ ከደረሰ በኋላ በጸጥታ ምክንያት ሙሉ በሙሉ ቆሞ እንደነበር ይታወቃል።
ተቋማችን ችግሩን ለመቅረፍ እና ግንባታውን ለማስቀጠል ከየአካባቢው የጸጥታ መዋቅር እና የመስተዳድር አካላት እንዲሁም ግንባታውን ከሚያከናውነው ፋል ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ እና አማካሪ መሀንዲሱ ጋር የተቀናጀ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። ጥረቱ በመሳካቱም ግንባታውን ዳግም ማስጀመር ተችሏል።
አሁን ላይም የመንገድ ዳር የዲች ሥራ በመከናዎን ላይ ሲኾን፥ ግንባታውን በሙሉ አቅም ለማስቀጠል የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመጠናቀቅ ላይ ናቸው።
የመንገድ ፕሮጀክቱ 80 ነጥብ 9 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ ለግንባታው 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግስት በጀት ተይዞለታል። የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን ኢንጅነር ዘውዴ እስክንድር እና ኩባንያው በማከናወን ላይ ይገኛል።
የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ በነባሩ ጠባብ የጠጠር መንገድ ይወስድ የነበረውን 6 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ተኩል ያሳጥረዋል። ምርታማ የኾኑትን የጎዛመን እና የደ/ኤሊያስ ወረዳዎችን ምርት በቀላሉ ወደ ገበያ ለማቅረብ ያስችላል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
13 313
የጅማ - ጭዳ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ለማፋጠን በትኩረት እየተሰራ ነው
አዲስ አበባ፣ ህዳር 17፣ 2018 (ኢመአ) የኦሮሚያና የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያን ክልሎችን የሚያስተሳስረው የጅማ - ጭዳ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ለማፋጠን በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
80 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍነው ይኸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ አፈፃፀሙ 46.16 በመቶ ደርሷል፡፡
በእስካሁኑ የግንባታ ሂደትም የአፈር ጠረጋ ፣ ቆረጣና ሙሌት፤ የውሃ ማስወገጃ ፉካዎችና ስትራክቸር፣ የሰብ ቤዝ ፣ ቤዝ ኮርስ ፣ 20.3 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ለማከናወን ተችሏል፡፡
ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ቲሲጁ ሲቪል ኢንጅነሪንግ ግሩፕ የተባለ የሥራ ተቋራጭ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥሩን ሥራ ኪዮንግዶንግ ኢንጅነሪንግ ፣ኦረንትያል ኮንሰልቲንግ ግሎባል እንዲሁም ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ በጋራ በመሆን እያከናወኑት ይገኛሉ፡፡
መንገዱን ለመገንባት 2,422,629,267 ብር (ሁለት ቢሊዮን አራት መቶ ሃያ ሁለት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሃያ ዘጠኝ ሺህ ሁለት መቶ ስልሳ ሰባት ብር ) ከአፍሪካ ልማት ባንክ እና ከጃፓኑ ዓለም ዓቀፍ ተራድዖ ድርጅት (JICA) በተገኘ የፋይናንስ ድጋፍ የተሸፈነ ነው፡፡
የመንገዱ የጎን ስፋት በገጠር 10 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር ፣ በከተማ 17 ሜትር እንዲሁም በወረዳ 21.50 ሜትር ነው፡፡
የግንባታ ግብዓት አቅርቦት እጥረት መኖሩ እንዲሁም የወሰን ማስከበርና ተያያዥ ችግሮች በፕሮጀክቱ አፈፃፀም ላይ አሉታዎ ተፅዕኖ አሳድሯል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ እነዚህን ችግሮች በመፍታት የፕሮጀክቱን የአፈፃፀም ሂደት ለማፋጠን በርካታ ሥራዎችን እየሰራ ይገኛል።
መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ እንደ ቡና ፣ ሰሊጥ ፣ በቆሎ ፣ ማሽላ እና ከፍተኛ የፍራፍሬ ምርቶች እንዲሁም የተለያዩ የግብርና ውጤቶችን በአፋጣኝ ወደ ገበያ እንዲደርሱ በማድረግ አምራች ሸማቹን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው።
በተጨማሪም መንገዱ ለኢንዱስትሪ ግብዓት ወሳኝ የሆነ የከሰል ድንጋይ በሚወጣበት አካባቢ የሚገኝ ከመሆኑም ባሻገር ፣ ወደ ኮይሻ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የግንባታ ግብዓት የሚያመላልሱ ከባድ ተሽከርካሪዎች የሚጠቀሙት እንዲሁም የጨበራ ጩርጩራ ዝሆን ዳና ሎጅ እና ሃላላ ኬላን ለመሳሰሉ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች አማራጭ መዳረሻ በመሆን የሚያገለግል መሆኑ ኢኮኖሚያዊ ፋይዳውን ከፍተኛ ያደርገዋል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
13 313
በጋምቤላ ክልል በግንባታ ሂደት ላይ ያሉ የመንገድ ፕሮጀክቶችን የሥራ አፈጻጸም ለማሻሻል የሚያስችል ምክክር ተካሄደ።
አዲስ አበባ፣ ህዳር 15፣ 2018 (ኢመአ) በጋምቤላ ክልል ውስጥ በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ የመንገድ ፕሮጀክቶችን የሥራ አፈጻጸም ለማፋጠን፣ ለማሻሻል እንዲሁም የተጓተቱ ፕሮጀክቶችን ማስቀጠል ላይ ትኩረት ያደረገ ምክክር ተካሂዷል።
በምክክሩ ላይ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ፣ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማንን ጨምሮ ሌሎች የፌዴራልና የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ተገኝተዋል።
ውይይቱ በክልሉ በተለያዩ ምክንያቶች የግንባታ ሂደታቸው የተጓተቱ ፕሮጀክቶችን በተለይም በአፈፃፀም ችግር ምክንያት የተቋረጡትን በማስጀመር እንዲሁም እየተከናወኑ ያሉትን በማጠናከር በህብረተሰቡ ዘንድ የሚነሱ የመንገድ መሠረተ ልማት ጥያቄዎችን ምላሽ መስጠት ላይ ያተኮረ ነው።
በዚህም መሰረት በጋምቤላ ክልል በግንባታ ላይ ያሉ ፕሮጀክቶች አጠቃላይ አፈፃፀም ግምገማ ተደርጓል። ግምገማውን ተከትሎ የአቦቦ -ሜጢ - ኩቢጦ መገንጠያ የመንገድ ፕሮጀክትን ጨምሮ የሌሎች ፕሮጀክቶችን ግንባታ ለማፋጠን እና የቆሙትን ለማስቀጠል የሚያስችል የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል።
የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን በአፈፃፀም ችግር የተቋረጡትን ፕሮጀክቶች ማስቀጠል ቅድሚያ የሚሰጠው ጉዳይ እንደሆነ ገልጸው ለመንገድ ልማት ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት በትኩረት እየሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል። አያይዘውም ለፕሮጀክቶቹ ስኬት የክልሉ መንግስት ድጋፍ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።
ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ አለሚቱ ኡሞድ በበኩላቸው የፌዴራል መንግስትን በክልሉ የሚያደርገውን መንገድን የማስፋፋት ጥረት አድንቀዋል፡፡ በተወሰኑ ፕሮጀክቶች ላይ የሚስተዋሉትን የአፈጻጸም ችግሮችን ለመፍታት ብሎም በግንባታ ሂደት ላይ ያሉ መንገዶችን ግንባታ ለማፋጠን እና የተቋረጡትን ለማስቀጠል የክልሉ መንግስት ድጋፍ ከምንጊዜውም በላይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ዉይይቱ በጋምቤላ ክልል ከመንገድ መሠረተ ልማት አኳያ የሚታዪ ክፍተቶችን በቀጣይ ለመቅረፍ እንደሚያስችል ይታመናል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
13 313
የጋሸና - ላሊበላ - ብልባላ - ሰቆጣ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመልካም አፈጻጸም ላይ ነው
አዲስ አበባ፣ ህዳር 14፣ 2018 (ኢመአ)፣ በአማራ ክልል ውስጥ የሚገኘው የጋሸና - ላሊበላ እና የ15 ኪ.ሜ የላሊበላ ተለዋጭ መንገድ እንዲሁም የብልባላ - ሰቆጣ የመንገድ ፕሮጀክት ቀሪ ስራዎችን ማጠናቀቂያ በመልካም አፈፃፀም ላይ ይገኛል ።
በእስካሁኑም የሥራ አፈፃፀም የተለያዩ የቅየሳ ስራዎች፣ የአፈር ጠረጋ፣ የቆረጣ እና የሙሌት፣ የሰቤዝ መንገድ ንጣፍ፣ የመንገድ አካፋይ እና የድጋፍ ግንብ ግንባታ፣ የውሃ ማፋሰሻ ቱቦ ቀበራ፣ የአስፋልት ማቅለጫ ማሽን እና የድንጋይ ወፍጮ ማሽን ተከላ ስራዎች ተሰርተዋል።
ከዚህ ቀደም አብዛኛው የመንገዱ ግንባታ በሰሜኑ ጦርነት ከመቋረጡ በፊት የተከናወነ ሲሆን ከቀሪው 23.32 ኪ.ሜ ውስጥ በአሁኑ ወቅት 5 በመቶ ያህሉን የማጠናቀቂያ ሥራ ለማከናወን ተችሏል፡፡
መንገዱ በሚገነባበት አካባቢ በተፈጠረው ተደጋጋሚ የፀጥታ ተግዳሮት ምክንያት የግንባታ ግብዕቶች፣ ማሽነሪዎች እና መሳሪያዎች በበቂ ሁኔታ ለማቅረብ የሥራ ተቋራጩ መቸገሩ እንዲሁም ክፍያ የተፈጸመባቸው ንብረቶች በወቅቱ አለመነሳትም ተደራራቢ ችግር አስከትሏል።
ችግሩን ለመቅረፍ እና ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ እንዲጠናቀቅ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የቅርብ ድጋፍና ክትትል እያደረገ ነው።ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ ከአካባቢው አስተዳደር፣ ከማህበረሰቡ እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በትብብር እየሠራ ነው።
ይህ መንገድ በከተማ ከ19 እስከ 30 ሜትር የጎን ስፋትና 2.5 ሜትር የእግረኛ መንገድ ያለው ሲሆን በገጠር ደግሞ 7 ሜትር የጎን ስፋትና 3 ሜትር የመንገድ ትከሻን አካትቷል፡፡
ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 5,119,831,284.27 (አምስት ቢሊየን አንድ መቶ አስራ ዘጠኝ ሚሊዮን ስምንት መቶ ሰላሳ አንድ ሺህ ሁለት መቶ ሰማንያ አራት ብር) በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው።
ግንባታውን የሚያካሂደው የሥራ ተቋራጭ ህብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ከዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ በመሆን ነው።
የጋሸና - ላሊበላ የመንገድ ክፍል የማማከርና የቁጥጥር ሥራን ኢንጂነር ዘውዴ እስክንድር እና ኃ/የተ/የግ/ማህበር ከዋይ ኤል ኤስ ኢንጂነሪግ ጋር በመተባበር እየሠሩት ሲሆን የብልባላ - ሰቆጣ የመንገድ ክፍል ደግሞ ቤዛ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ከቤዛ ኢንጂነሪንግ ኬኒያ ሊሚትድ ጋር በአጋርነት እያከናወኑት ነው።
የመንገዱ ግንባታ የክልሉን የመንገድ ሽፋን ከማስፋት ባለፈ የሰቆጣ -ላሊበላ እንዲሁም ከጋሸና - ወልድያ- ደሴ ያለውን የትራንስፖርት እንቅስቃሴ በከፍተኛ ሁኔታ ያቀላጥፋል።
በተጨማሪም ለላሊበላ ከተማ፣ ለላስታ፣ መቄትና ዋድላ ወረዳዎች እንዲሁም በዋግ ኽምራ ዞን ለሚገኙ ነዋሪዎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎቶችን በቀላሉ እንዲጠቀሙ ከማድረጉም በላይ የሰሜን ወሎንና የዋግ ኽምራ ዞኖችን በብቸኝነት ያስተሳስራል።
ከዚህም ባሻገር በዓለም የቅርስ መዝገብ (UNESCO) የተመዘገቡትንና ከፍተኛ የቱሪስት ፍሰት ያለባቸውን የላሊበላ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያናት በቀጥታ ተደራሽ የሚያደርግ በመሆኑ የመንገዱን አስፈላጊነት በእጅጉ ይጨምረዋል።
በሌላ በኩል በአካባቢው የሚመረቱ እንደ ዘንጋዳ፣ ገብስ፣ ባቄላ፣ ጤፍ፣ ማር እና ሌሎች የእንስሳት ተዋፅኦዎችን ያለምንም መስተጓጎል ለገበያ እንዲቀርቡ በማድረግ ለክልሉ ኢኮኖሚ ታላቅ አስተዋፅዖ ይኖረዋል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
