ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 313 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 759,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 546

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 313 名订阅者。

根据 15 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 88,过去 24 小时变化为 2,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.23%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.41% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 352 次浏览,首日通常累积 2 050 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 16 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 313
订阅者
+224 小时
+297
+8830
帖子存档
የደብረ ማርቆስ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በሁሉም የጥገና ዓይነቶች  ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 11 ፣ 2017 (ኢ መ አ):- የደብረ ማርቆስ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በስሩ በሚገኙ አራት የጥገና ሴክሽኖች አማካኝነት በሁሉም የጥገና ዓይነቶች ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ በበጀት ዓመቱ 389 ኪሎ ሜትር ርዝመት  ያለው የመንገድ ሽፋን ለመጠገን የተቻለ ሲሆን የአዲስአበባ-ጎንደር (A3) ዋና መንገድ አካል በሆነው በደጀን - ባሕርዳር የመንገድ ክፍል ውስጥ መጠነ ስፊ የአስፋልት ጥገና ስራዎችን  መስራት ተችሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የድንገተኛ ጥገና ስራዎች በዋናነት በዓባይ ግድብ መዳረሻ እና በጢቅ ፈለገ ብርሃን የመንገድ ክፍሎች የተከናወኑ ሲሆን የድልድይ እና ከልቨርት ጥገና እና ማሻሻል ስራዎች በተለይ በሦስቱ  ሴክሽኖች (በደጀን፣ በቡሬ፣ እና በባህር ዳር) በማከናወን የትራፊክ እንቅስቃሴውን ያለምንም ችግር ማሳለጥ ተችሏል፡፡ ከዚህም ባሻገር ለረዥም ጊዜ ተበላሽቶ የቆየውን በማንኩሳ- ብርሸለቆ የመንገድ ክፍል የሚገኘውን የብርሸለቆ ማሰልጠኛ መዳረሻ ድልድይ እና  የዘማ ወንዝ ድልድይን ከድልድይና እና ስትራክቸር ቡድን ጋር በጋራ በመሆን በአጭር ጊዜ ወደ  ብረት ድልድይ (Bailey Bridge) የመቀየር ስራ ተሰርቷል፡፡ ከትራፊክ ደህንነት ጋር በተየያዘም በሁሉም ሴክሽኖች ሥራዎች የተሰሩ ሲሆን በተለይም በደጀን ሴክሽን ከዚህ በፊት ከነበረው በበለጠ መልኩ  ሰፊ ስራዎችን ማከናወን ተችሏል፡፡ በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የሀይቅ - ቢስቲማ - ጭፍራ መንገድ ግንባታ ለማፋጠን እየተሠራ ነው  አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 09፣ 2017 (ኢ መ አ):- የአፋር እና የአማራ ክልሎችን የሚያገናኘው የሀይቅ - ቢስቲማ - ጭፍራ መንገድ ግንባታ ለማፋጠን እየተሠራ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ 74 ነጥብ 3 ኪሎሜትር የሚሸፍን ኾኖ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል። አሁን ላይ የግንባታው አጠቃላይ አፈጻጸም 40 ነጥብ 95 በመቶ ደርሷል። የአፈጻጸም ሂደቱን ይበልጥ አጠናክሮ ለማስቀጠል በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። በእስካሁኑ የግንባታ ሥራዎች መካከል የጠረጋ፣ የአፈር ቁፋሮ፣ የአፈር ሙሌት፣ የማፋሰሻ ቱቦ፣ የተላያዩ የተፋሰስ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። የ2 ድልድይ እንዲሁም የአነስተኛ እና ከፍተኛ ከልቨርቶች ሥራም የግንባታው አካል ነው። በተጨማሪም የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ለማስጀመር የሚረዱ አስፈላጊ ጥረቶች በመደረግ ላይ ናቸው። አሁንም ድረስ ያልተፈቱ የወሰን ማስከበር ሥራዎች፣ አልፎ አልፎ የሚከሰቱ የጸጥታ ችግሮች እና የግብአት እጥረቶች የፕሮጀክቱ ፈተና ናቸው። ያጋጠሙ ችግሮች በሚፈቱበት ሁኔታ ላይ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ይገኛል። የመንገድ ግንባታውን ሀገር በቀሎቹ ፓወርኮን ኮንስትራክሽን ከአሰር ኮንስትራክሽን ጋር በመተባበር ያከናውኑታል። የፕሮጀክቱን ጥራት እና ቁጥጥር ኮር ኮንሰልቲንግ ያከናውናል። ለፕሮጀክቱ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር የተመደበ ሲኾን፥ ወጪው በፌደራል መንግስት በጀት ይሸፈናል። ነባሩ መንገድ ከ4 - 7 ሜትር ያልበለጠ የጎን ስፋት የነበረው እና በአገልግሎት ብዛት የተጎዳ በመኾኑ ለተጠቃሚው ምቹ አልነበረም። አሁን ላይ ግንባታው ደረጃውን ጠብቆ እየተከናወነ ሲኾን፣ ሲጠናቀቅ ከሀይቅ ተነስቶ ጭፍራ ከተማ ለመጓዝ ቀድሞ ይፈጅ የነበረውን 3 ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ያሳጥረዋል። በፕሮጀክቱ ክልል የሚገኙ በርካታ ከተሞችን በማስተሳሰር ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ዕድገትን ያጠናክራል። በአካባቢው የሚበቅሉትን የማሽላ፣ ጫት እና የተለያዩ የፍራፍሬ ምርት ውጤቶች በቀላሉ በማጓጓዝ የንግድ እንቅስቃሴውን ያቀላጥፋል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኤረር ጉዳ ወንዝ የብረት ድልድይ ግንባታ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው ሐረር፣ ሐምሌ 07፣ 2017 (ኢ መ አ):- የአዲስ አበባ - ድሬዳዋ - ሐረር - ጅግጅጋ መንገድ የኤረር ጉዳ ወንዝ ጊዚያዊ የብረት ድልድይ ግንባታ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ አጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት ለማድረግ እየተሠራ ነው። ከሐረር ከተማ በ12 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው እና 45 ሜትር የሚረዝመው ነባሩ የኮንክሪት ድልድይ ባጋጠመው ከፍተኛ ጎርፍ የመካከለኛው ቋሚ (pier) ምሰሶዎች ተሸርሽረው ድልድዩ ሙሉ በሙሉ መፍረሱ ይታወቃል። በወቅቱ ሙሉ በሙሉ ከፈረሰው ድልድይ ትዩዩ የሚገኘው እና ለአገልግሎት ዝግ ተደርጎ የቆየው ሌላኛውን የኮንክሪት ድልድይ በድሬደዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በኩል አፋጣኝ ጥገና ተደርጎለት የትራፊክ እንቅስቃሴው እንዳይስተጓጎል ማድረግ ተችሏል። ነገር ግን በእርጅና ምክንያት ዝግ ተደርጎ የቆየው ይኸው ድልድይም ቢሆን የሚፈለገውን ጊዜ ያህል አገልግሎት መስጠት እንደማይችል ስለሚታወቅ ለአጭር ጊዜ ዕቅድ በሁለቱ ነባር ድልድዩች መካከል የብረት ድልድይ (Bailey bridge) መገንባት በማስፈለጉ ግንባታው እየተከናወነ ይገኛል። ይህ የብረት ድልድይ ጠቅላላ ርዝመቱ አርባ ሁለት (42) ሜትር እና አራት (4) ሜትር የጎን ስፋት ያለው ሲኾን፣ በአንድ ጊዜ በአንድ አቅጣጫ አንድ ተሽከርካሪ ማስተናገድ የሚያስችል ነው። ግንባታውን በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት እንዲሁም የድልድይና ስትራክቸር ዳይሬክቶሬት በጋራ እያከናወኑ ይገኛሉ። ከድልድዩ ዝርጋታ ጎን ለጎን በሁለቱም አቅጣጫ (በሐረር እና ባቢሌ) በኩል የመዳረሻ መንገዶች አፈር ሙሌት፣ የድጋፍ ግንብ ግንባታ እና ከአስፓልቱ ጋር የማመሳሰል ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። የሐረሪ፣ የኦሮሚያ እና የሶማሌ ክልሎችን የሚያስተሳስረው ይኸው ድልድይ በቋሚነት በኮንክሪት ለመገንባት የዲዛይን ሥራው ተጠናቅቆ የሥራ ተቋራጭ የተመረጠ ሲኾን፥ ሥራው በቀጣይ ዓመት ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የስራ ማስታወቂያ
+2
የስራ ማስታወቂያ

ከ18 ማዞሪያ - አሸዋ ሜዳ - ኬላ መንገድ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ነው አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2017 (ኢ መ አ):- ከ18 ማዞሪያ - አሸዋ ሜዳ - ኬላ ድረስ በመገንባት ላይ የሚገኘው የመንገድ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ነው። 14 ነጥብ 72 ኪሎሜትር የሚሸፍነው የመንገድ ግንባታው፥ የአዲስ አበባ - አምቦ - ነቀምት መስመር አካል ሲሆን፥ መነሻውን በኮልፌ 18 ማዞሪያ አድርጎ ሸገር ከተማ አሸዋ ሜዳ በኩል ኬላ ድረስ ይዘልቃል። መንገዱ በከተማ መውጫ የሚፈጠሩ የትራፊክ መጨናነቆችን ለመቅረፍ ታልሞ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው። ነባሩ መንገድ ከ8 ሜትር ያልበለጠ እና ለአደጋ የተጋለጠ የነበረ ሲኾን፣ አሁን ላይ የመንገድ ፕሮጀክቱ የእግረኛና የብስክሌተኞች መንገድ እንዲሁም የመሮጫ መም (ትራክ)ን እና የመንገድ አካፋይን ጨምሮ አጠቃላይ 66 ሜትር የጎን ስፋት ይኖረዋል። ይህም የትራንስፖርት ፍሰቱን በማሳለጥ ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ትስስሩን የሚያጠናክር ነው። ከዚህም ባለፈ የከተሞችን ሁለንተናዊ ዕድገት በእጅጉ የሚያፋጥን ነው። የመንገድ ግንባታው በሁለት ሴክሽኖች ተከፍሎ የመጀመሪያው ክፍል በሀገር በቀሉ ብሪጅ ኮንስትራክሽን ሲሆን ሁሉተኛው ክፍል በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የዓለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በራስ ኃይል ግንባታው እየተከናውነ ይገኛል። ኢትዮ - ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬት የቁጥጥር እና የማማከር ሥራውን ያከናውናል። በአሁኑ ሰዓት የዲዛይን፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት እንዲሁም የሰብቤዝ ሥራዎችን ጨምሮ በርካታ የተለያዩ የግንባታ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። አጠቃላይ አፈጻጸሙም አሁን ላይ 20 በመቶ ደርሷል። በዚህ ዓመት መጨረሻ የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ለመጀመር አስቻይ ሁኔታዎች በመከናወን ላይ ናቸው። ይህ ሀገራዊ ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜ እና ጥራት እንዲጠናቀቅ የየአካባቢው ማኅበረሰብ እና የመስተዳድር አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ እና ትብብር እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ይጠይቃል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የወልዲያ ከተማ መንገድ ፕሮጀክት አፈጻጸም 75 ነጥብ 09 በመቶ ደረሰ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 24፣ 2017 (ኢ መ አ):- በ1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ወጪ የሚገነባው የወልዲያ ከተማ መንገድ ፕሮጀክት አፈጻጸም 75 ነጥብ 09 በመቶ ደርሷል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 7 ነጥብ 52 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ የከተማውን መሀል በማቋረጥ እስከ ወልዲያ ስታዲየም ባለው ዋና መሥመር እየተከናወነ ይገኛል። ነባሩ መንገድ ስፋቱ ከ7 ሜትር ያልበለጠ፣ በአገልግሎት የተጎዳ እና ለትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ያልነበረ ሲኾን፣ አሁን ላይ የእግረኛ እና የብስክሌት መንገድ ጨምሮ አጠቃላይ ስፋቱ 30 ሜትር እንዲሁም ወደ ስታዲየም የሚወስደው አቅጣጫ ደግሞ 12 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል። ይህም ምቹ እና ቀልጣፋ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲኖር ከማስቻሉም ባለፈ የከተማውን ሁለንተናዊ ዕድገት እንደሚያፋጥን ይጠበቃል። በመንገድ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ  የማፋሰሻ ቱቦ፣ የከርብ እንዲሁም የእግረኛ መንገድ ግንባታ እየተከናወነ ይገኛል። የነባር እና አዳዲስ ድልድዮች ግንባታም በፕሮጀክቱ ተካትቷል። ፕሮጀክቱ ባጠረ ጊዜ ውስጥ ተጠናቅቆ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት መስጠት እንዲችል፣ ግንባታውን የሚያከናውነው በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት በትኩረት እየሠራ ይገኛል።  ሀገር በቀሎቹ ልደት ኮንሰልቲንግ እና ስማርት ኮንሰልቲንግ ግንባታው በቀመጠለት ጊዜ እና የጥራት ስታንዳርድ እንዲከናወን፣ የቁጥጥር እና የማማከር ሥራውን በጥምረት ያከናውናሉ። ለመንገድ ፕሮጀክቱ የተያዘው 1 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ወጪ በፌደራል መንግስት በጀት ይሸፈናል። ** ዜናው ለመጨረሻ ጊዜ የተሠራው ኅዳር 2016 ነው። ያኔ አፈጻጸሙ 58 በመቶ ነበር አሁን ላይ 79 በመቶ ደርሷል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የእንጦጦ ማርያም - ጉለሌ ዕጽዋት ማዕከል እና የእንጦጦ ማርያም - ጠፈር ምርምር ማዕከል - ኮተቤ መገንጠያ ፕሮጀክቶች እየተፋጠኑ ነው አዲስ አበባ፣ ሰኔ 21 2017 (ኢ መ አ):- ከእንጦጦ ማርያም - ጉለሌ ዕጽዋት ማዕከል እንዲሁም ከእንጦጦ ማርያም - ጠፈር ምርምር ማዕከል - ኮተቤ መገንጠያ ድረስ እየተገነቡ የሚገኙት የመንገድ ፕሮጀክቶች እየተፋጠኑ ነው። የመንገድ ግንባታዎቹ አዲስ አበባን ከዋና ዋና የክልል ከተሞች ጋር ከሚያስተሳስሩ እንዲሁም ከፍተኛ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚከናወንባቸው የከተማ መውጫ የሆኑ ፕሮጀክቶች አካል ናቸው። የመንገድ ፕሮጀክቶቹ በዋናነት ከደብረብርሃን መሥመር መጥተው ወደ ጎጃም መስመር የሚጓዙ ተሽከርካሪዎች አዲስ አበባን ሳይነኩ ማለፍ የሚያስችሉ ናቸው። ፕሮጀክቶቹ በሁለት ምዕራፍ ተከፋፍለው በመገንባት ላይ የሚገኙ ሲኾን፥ በመጀመሪያው ምዕራፍ ከእንጦጦ ማርያም - ጠፈር ምርምር ማዕከል - ኮተቤ መገንጠያ ድረስ በመገንባት ላይ የሚገኘው የመንገድ ፕሮጀክት 18 ነጥብ 58 ኪሎሜትር ይሸፍናል። የመንገድ ግንባታውን ሀገር በቀሉ አሰር ኮንስትራክሽን በ5 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ወጪ እያከናወነ ሲኾን፥ ስታዲያ የምሕንድስና ሥራዎች አማካሪ የማማከር እና የቁጥጥሩን ሥራ በመሥራት ላይ ይገኛል። አሁን ላይ የመጀመሪያው 10 ሴንቲሜትር የአስፋልት ንጣፍ (Bitumenous Road Base) ተጠናቅቆ መንገዱ ለተሽከርካሪዎች ክፍት የተደረገ ሲኾን፥ ቀጣይ ደረጃ የአስፋልት ንጣፎች የትራፊክ እንቅስቃሴውን በማያስተጓጉል መልኩ በመከናወን ላይ ይገኛሉ:: ጎን ለጎንም የእግረኛ መንገድ ግንባታ ሥራ በመከናወን ላይ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ አሁን ላይ አጠቃላይ አፈጻጸሙ 67 ነጥብ 55 በመቶ ደርሷል። የተመዘገበውን አበረታች አፈጻጸም አጠናክሮ በማስቀጠል እስከ ኅዳር 2018 ድረስ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። መንገዱ የእግረኛ እና የመንገድ አካፋይን ጨምሮ አጠቃላይ 31 ሜትር የጎን ስፋት አለው። በተመሳሳይ በምዕራፍ ሁለት ከእንጦጦ ማሪያም - ጉለሌ እጽዋት ማዕከል ድረስ የሚዘልቀው የመንገድ ፕሮጀክት አሁን ላይ ከአጠቃላይ የመንገድ ሥራው 55 በመቶው ተጠናቅቋል። የመንገድ ግንባታውን በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የዓለምገና መንገድ ጥገና ዲስትሪክት የሚያከናውን ሲኾን፣ 4 ነጥብ 37 ኪሎሜትር ይሸፍናል። ለፕሮጀክቱ 1 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር በፌደራል መንግስት በጀት ተይዞለታል። ኢትዮጵያ ኢንጂነሪግ ኮርፖሬሽን፣ ትራንስፖርት ዘርፍ የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን በማከናወን ላይ ይገኛል። አሁን ላይ የአስፋልት ንጣፍ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የድጋፍ ግንብ እንዲሁም ፍሳሽ ማስወገጃ እና ቱቦ ቀበራ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። ግንባታውን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ ከተማዋ ላይ የሚስተዋለውን የትራፊክ ጭንቅንቅ በእጅጉ የሚያቀሉ ናቸው። በተጨማሪም የእንጦጦ ፓርክ እንዲሁም የጠፈር ምርምር ማዕከል መዳረሻውን ምቹ በማድረግ በኩል ሚናቸው የጎላ ነው። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

በቡሬ - ጎመር መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት የማንጠፍ ሥራ ተጀመረ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 20፣ 2017 (ኢ መ አ):- በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን በቡሬ - ጎመር መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት የማንጠፍ ሥራ ተጀመረ። 43 ነጥብ 60 ኪሎሜትር የሚሸፍነው የመንገድ ፕሮጀክቱ፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ በመገንባት ላይ ይገኛል። አሁን ላይ የአስፋልት ንጣፍ ሥራ እየተከናወነ የሚገኝ ሲኾን፥ ጎን ለጎንም የውኃ መፋሰሻ፣ የአፈር ሥራ፣ የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው። የ3 ድልድዮች፣ የ6 ስላቭ ከልቭርቶች እና የ52 ፓይፕ ከልቨርቶች ግንባታም የፕሮጀክቱ አካል ነው። ግንባታውን ሀገር በቀሉ ሚድሮክ ኮንስትራክሽን ኢትዮጵያ በ1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪ እያከናወነ ይገኛል። ወጪው ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ነው የተሸፈነው። የግንባታውን ጥራት ቁጥጥር እና የማማከር ሥራ አይ ኤም ኤስ ኢንጅነርስ ከፕሮፌሽናል ኢንጅነርስ ኮንሰልቲንግ ጋር በጥምረት ያከናውናሉ። የመንገድ ግንባታው ዕውን ሲኾን ቀድሞ ከቡሬ ከተማ ተነስቶ ጎመር ለመድረስ የሚወስደውን የሁለት ሰዓት የጉዞ ጊዜ ወደ 45 ደቂቃ ዝቅ በማድረግ የማኅበረሰቡን ድካም እና እንግልት ያስቀራል። በምዕራብ ጎጃም እና ወለጋ ዞን መካከል ያለውን ማኅበራዊ እና ምጣኔ ሀብታዊ ትስስር ያጠናክራል። አርሶ አደሩ ምርቱን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማቅረብ የተሻለ ተጠቃሚ እንዲሆን ያስችለዋል። በሥፍራው ለሚገኘው የቡሬ ኢንዱስትሪ ፓርክ ምቹ መዳረሻ በመኾን ከፍተኛ መነቃቃትን ይፈጥራል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የቱሉቦሎ - ኬላ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 14፣ 2017 (ኢ መ አ):- የኦሮሚያ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎችን የሚያገናኘው የቱሉቦሎ - ኬላ አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታው ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 80 ኪሎሜትር የሸፈነ ሲኾን፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው የተገነባው። የመንገድ ግንባታውን የቻይናው ዓለም-አቀፍ የሥራ ተቋራጭ ሁናን ሁንዳ ሮድ ኤንድ ብሪጅ ኮርፖሬሽን አከናውኖታል። ሀገር በቀሉ የተባበሩት የምህንድስና አማካሪዎች የግንባታውን ጥራት በመቆጣጠር እና በማማከር በኩል ተሳትፏል። ለፕሮጀክቱ የዋለው 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት ተሸፍኗል። በመንገድ ፕሮጀክቱ ሦስት ድልድዮችን ጨምሮ አነስተኛ፣ ከፍተኛ ፍሳሽ ማስተላለፊያዎች፣ ቱቦዎች እና ከልቨርቶች ግንባታም ተካትቷል። መንገዱ በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜትር፣ በወረዳ 20 ሜትር እንዲሁም በቀበሌ 15 ሜትር የጎን ስፋት አለው። የመንገዱ መጠናቀቅ የማኅበረሰቡን የዘመናት የመሠረተ ልማት ጥያቄ ምላሽ የሰጠ ከመኾኑም ባለፈ የአዲስ አበባ-ቡታጅራ -ሆሳዕና እና የአዲስ አበባ - ወልቂጤ - ጅማ መስመር  ያሉትን አውራ መንገዶች ያገናኛል፡፡ ይህም ከዚህ ቀደም ይደረግ የነበረውን ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ በማስቀረት የጉዞ ጊዜን ያሳጥራል። የተቀላጠፈ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ እንዲኖር በማስቻል፣ የማኅበራዊ ተቋማት ተደራሽነትን በማስፋት እንዲሁም የገበያ ትስስሩን በማጠናከር የመንገዱ መገንባት ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያበረክታል። የቱሉቦሎ፣ ሀርቡጩሉሌ፣ ኮምበል፣ አጨበር፣ ቀሽት እና ኬላን ጨምሮ ሌሎች በርካታ አካባቢዎችን በቅርበት ያገናኛል። መንገዶች በከፍተኛ የሀገር ሀብት የሚገነቡ በመኾኑ ኅብረተሰቡ በኃላፊነት እንዲገለገል ኢመአ ያሳስባል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የቴፒ-ሚዛን የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በሚቀጥለው በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2017 (ኢ መ አ) ፡- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ግንባታው በመካሄድ ላይ የሚገኘው እና የቤንች ሸኮን እና የሸካ ዞኖችን የሚያገናኝ የቴፒ-ሚዛን 47.87 ኪሎ ሜትር አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትን በቀጣዩ በጀት ዓመት ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡ በእስካሁኑ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የማፋሰሻ ፣ የስትራክቸር ፣ የሰብ ቤዝ እና የቤዝ ኮርስ ንጣፍ እንዲሁም 25 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱን እያከናወነ የሚገኘው ቻይና ግዞባ ግሩፕ ኃ/የተ/የግ/ማህበር (CGGC) የተባለ የቻይና የስራ ተቋራጭ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራው ደግሞ ፕሮሚነንት ኢንጂነሪንግ ሶሉሽንስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር በሚባል አማካሪ ድርጅት አማካኝነት በመካሄድ ላይ ይገኛል። ለግንባታው ማስፈጸሚያ የሚውለውን 1,276,922,787 (አንድ ቢሊዮን ሁለት መቶ ሰባ ስድስት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃያ ሁለት ሺህ ሰባት መቶ ሰማንያ ሰባት) ብር በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው ። አሁን ላይ የስራ ተቋራጩ ከአጠቃላይ ስራው 31.6 ኪሎ ሜትር ወይም 66 በመቶውን ያጠናቀቀ ሲሆን የፕሮጀክቱን ቀሪ ስራዎችም በሚቀጥለው በጀት አመት (2018 ዓ.ም) ለማጠናቀቅ እየሰራ ይገኛል፡፡ እቅዱን ከግብ ለማድረስም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከሚመለከታቸው ባለድረሻ አካላት ጋር በተዋረድ ተቀናጅቶ እየሰራ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ የቤንች ሸኮን እና የሸካ ዞኖችን የሚያገናኝ እንደመሆኑ መጠን በአካባቢው እንደ ቡና ፣ ሙዝ ፣ አቮካዶ ፣ ማር ፣ የተለያዩ ቅመማ ቅመሞች ፣ ቁንዶ በርበሬ እና ኮረሪማ እንዲሁም ፍራፍሬዎች በከፍተኛ ሁኔታ የሚመረቱ በመሆኑ እነዚህ ምርቶች በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ እንዲደረሱ በማስቻል ከፍተኛ ማህበራዊ እና አኮኖሚያዊ አስተዋጽኦን ያበረክታል፡፡ በተጨማሪም መንገዱ ሁለቱን ዞኖችን የሚያገናኝ ከመሆኑም ባሻገር በወረዳና በከተማ አስተዳደር ደረጃም የቴፒ ከተማ አስተዳደርን ፣ የኪ ወረዳን ፣ ሸኮ ከተማ አስተዳደርን ፣ ሸኮ ወረዳ እና ሚዛን አማን ከተማ አስተዳደርን በቅርበት በማገናኘት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መስተጋብራቸውን ይበልጥ ያጠናክራል ተብሎ ይታመናል፡፡ በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads