ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 369 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 753,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 530

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 369 名订阅者。

根据 20 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 129,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.47%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.24% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 143 次浏览,首日通常累积 2 037 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 21 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 369
订阅者
+824 小时
+697
+12930
帖子存档
የሃዋሳ -ሞያሌ መንገድ አና የሞያሌ የጋራ መተላለፍያ ጣቢያ ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ እና የኬንያ ፕሬዚዳንት እሁሩ ኬንያታ በተገኙበት በቀን 30/03/2013 በይፋ መመረቁ ይታወቃል ። ይህ መስመር ወደ ግንባታ ለማሸጋገር ከ 8 አመት በፊት ጥናቱ ሲከናወን የቡሌ ሆራ ከተማ ሀገረማርያም ተብሎ ይጠራ የነበረ ከመሆኑ አኳያ ፕሮጀክቱ ተቀርፆ ወደ ተግባር ሲሸጋገር ባሉን የኮንትራት ዉሎችም ሆነ በፋይናንስ በደገፈን የአፍሪካ ልማት ባንክ ሰነዶች ለአገልግሎት ሲዉል ቆይቷል። በምረቃ ስነስርዓቱ በተዘጋጁ ህትመቶች አና ባነሮች ሀገረማርያም ተብሎ የተጠቀሰው በዚሁ ምክንያት እንደሆነ እንዲታወቅ እየጠየቅን በቀጣይ እንደሚስተካከል በእክብሮት እንገልፃለን ።

በደቡብ የሀገራችን ክፍሎች የሚዘረጉ የመንገድ ልማት ቀጣይ እቅድ ፣የክልሎች ሚና እና ተሳትፎ ላይ ያተኮረ የውይይት መድረክ ዛሬ በሀዋሳ ከተማ ተካሄደ። በውይይት መድረኩ ላይ የደቡብ ክልል ርእሰ መስተዳድር ክብር አቶ እርስቱ ይርዳው ፣ የሲዳማ ክልል ርእሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ፣ የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ ፣ የኢመባ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች እና የክልል የስራ አመራሮች ታድመዋል። በመድረኩ ላይ የቀጣይ የአስር አመታት የሀገራችን የመንገድ መሪ እቅድ ዋና ዋና ይዘትን የዳሰሰ ሰነድ ቀርቧ ውይይት ተካሂዶበታል። ከባለፋት አመታት የመንገድ መርሃ -ግብሮች አተገባበር የነበሩ ውስንነቶችን በመለየት፣ ቀጣይ የሀገራችን የመሰረተ ልማት አውታር ሊኖረው የሚችለውን ጸጋዎች አሟጦ ለመጠቀም በሚያስችል መልኩ በጥልቀት መዘጋጀቱ ተገልጾል። ከዚህ አኳያ በመንገድ ግንባታ ሂደት ውስጥ ክልሎችን በአደረጃጀት ፣በመዋቅር ፣በአቅም ግንባታ አሳድጎ የመሰረተ ልማት አውታሩን በከፋተኛ ደረጃ ለማሳለጥ መሪ እቅዱ የጎላ ሚና እንዳለው ተመላክቷል። አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታና በቀጣይ ከሚኖረው ሰፊ የመሰረተ ልማት ግንባታ የክልሎችን አቅም አሳድጎ ፣ቀጥተኛ የመንገድ ግንባታ እና ፕሮጀክቶችን ወደ ማስተዳደር የሚያሸጋግር በመሆኑ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ርእሳነ መስተዳድሮቹ አንሰተዋል። የደቡብ ክልል ርእሰ መስተዳድር ክብር አቶ እርስቱ ይርዳው እና የሲዳማ ክልል ርእሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ደስታ ሌዳሞ በእቅድ ግብአትነት ሊካተቱ ይገባቸዋል ያሏቸውን አንኳር ነጥቦችንም አንስተዋል። እንዲሁም በቀጣይ ሊተኮርባቸው በሚገቡ አጀንዳዎች ላይም ተወያይተዋል። የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ መሪ እቅዱ ክልሎችን በቀጥታ የመንገድ የመሰረተ ልማት ግንባታ ባለቤትና ተቆጣጣሪ በማድረግ ፣ አንድ ተቋም ላይ ተንጠልጥሎ የቆየውን ከፍተኛ የስራ ጫናን ወደ ክልሎች በማጋራት ፣ የመንገድ አውታሩን በከፍተኛ ፍጥነትና ጥራት ለመከወን እንደሚያስችል አብራርተዋል። የትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታው አቶ ካሳሁን ጎፌ በበኩላቸው መሪ እቅዱ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ማህበራዊና ፖለቲካዊ ብልጽግናዎችን ለማጎናጸፍ ሚናው የለቀ እንደሆነ ገልጸዋል። በተለይም የክልሎችን ሚና እና ሃላፊነት በግልጽ አስቀምጦ ይበልጥ የሚያጠናክር በመሆኑ፣ የነበሩ ውስንነቶችን በመቅረፍ ለሀገራዊ የመንገድ የመሰረተ ልማት ግንባታ ፋይዳው ዘርፈ ብዙ እንደሆነም ተናግረዋል። ይህን ተፈጻሚ የሚያደርጉ ዝርዝር የፖሊሲና የህግ ማእቀፍችን እመንግስት እያዘጋጀ እንደሆነም ገልጸዋል። በዛሬው የውይይት መድረክ ላይ በቀጣይ ወደ ግንባታ የሚሸጋገሩ የመንገድ ፕሮጀክቶች በዝርዝር ቀርበዋል። እንዲሁም በግንባታ ላይ የሚገኙ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች አፈጻጻምና እያጋጠማቸው ያሉ ተግዳሮቶች ላይም ምክክር ተካሂዶል። በተለይም ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዞ ያጋጠሙ ችግሮችን ይበልጥ ተናቦ ለመፍታት የጋራ አቅጣጫን አስቀምጠዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድና የኬኒያው ፕሬዚዳት ኡሁሩ ኬኒያታ የኢትዮ-ኬንያን በር የሞያሌ የጋራ መተላለፊያ ጣቢያ/ONE STOP BOARDER POST/ፕሮጀክትን መረቁ። በሁለቱ ጎረቤት ሀገሮች የድንበር ከተማ ሞያሌ ዛሬ በተከናወነው መርሃ ግብር ዋና ዋና ስራው የተጠናቀቀውን የሀዋሳ ሞያሌ 500 ኪ.ሜ ርዝመት ያለውን የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክትንም መሪዎቹ መርቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የጋራ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን የሚያጎናጽፈው ይህ ፕሮጀክት ለአፍሪካዊ ብልጽግና ጉዞ ጉልህ ማሳያ ነው ብለዋል። አጠቃላይ ፕሮጀክቱ በመንገድ ትስስር ተሳልጦ የጋራ የመተላላፊያ መስመርን እውን አድርጎ በዘመናዊ መልኩ መገንባቱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ትስስሩን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሳድገው እንደሆነም ተናግረዋል። የኬኒያው ፕሬዚዳት ኡሁሩ ኬኒያታ በበኩላቸው የታሪካዊ ወዳጅ ሀገራት የኢኮኖሚ ትስስርን ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሳድጉ ፕሮጀክቶች እውን በመሆናቸው የሁለቱን ሀገራት ህዝቦች እንኳን ደስ ያላችሁ ብለዋል ። ኢትዮጵያዊ እና ኬኒያ በጋራ የመበልጸግ ራዕይያቸውን ወደፊት የሚያራምዱ ፕሮጀክቶች በመሆናቸው ከቀጠናው አልፎ አህጉራዊ ሚናቸው የላቀ እንደሆነም አብራርተዋል። ሁለተናዊ ፋይዳ ያላቸውን ይህን መሰሉን ፕሮጀክቶች በቀጣይም አጠናክረው እንደሚገነቡ ሁለቱ መሪዎች አረጋግጠዋል። የሀዋሳ_ሞያሌ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት እና በኢትዮ -ኬንያ ድንበር የሞያሌ የጋራ መተላለፊያ ጣቢያ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት በመደረጉ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ና ማህበራዊ እድገት ታላቅ የምስራች ነው ብለዋል የትራንስፖርት ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ። አጠቃላይ ስለፕሮጀክቶቹ ገለጻ ያደረጉት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ሀብታሙ ተገኘ/ኢንጂነር/ የአዲስ አበበ ሀዋሳ ሞያሌ መንገድ ከካይሮ እስከ ኬፕታውን የሚዘልቀው የትራንስ አፍሪካን ሃይዌይ አካል የሆነው የሞምባሳ-ናይሮቢ-አዲስአበባ ኮሪደር ክፍል ነው ብለዋል። አጠቃላይ ርዝመቱም ወደ780ኪ.ሜ የሚጠጋነው፡፡ በኢትዮጵያ በኩል መንገዱ የሚኖረውን ማህበራዊ፣ኢኮኖሚያዊእና ፖለቲካዊ ፋይዳ ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ተከታታይ የደረጃ ማሳደግ ሥራ ሲሰራ ቆይቷል ብለዋል፡፡ በመጀመሪያው ምዕራፍ 80ኪ.ሜ አካባቢ የሚረዝመው የአዲስ አበባ አዳማ የፍጥነት መንገድ ከ11ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበት ከጥቂት ዓመታት በፊት ለትራፊክ ክፍት መደረጉእና አሁንም አገልግሎት እየሰጠ እንደሆነ አስታውሰዋል። የዚሁ መንገድ ቀጣይ ክፍል የሆነውእና ወደ ሀዋሳ የሚዘልቀው የ202ኪ.ሜ የፍጥነት መንገድ በአራት ኮንትራክተር ተከፍሎ እየተሰራ ይገኛል፡፡ በዚህም መሠረት 56ኪ.ሜ የሚረዝመው ከሞጆ እስከ መቂ ያለው የመጀመሪያው ኮንትራት እና 37 ኪ.ሜ የሚረዝመው ከመቂ እስከ ባቱ ያለው ሁለተኛው ኮንትራት ወደ 5.7ቢሊዮን ብር ወጪ ተደርጎባቸው እየተገነቡ ሲሆን በዚህ በጀት ዓመት ተጠናቀው ለትራፊክ ክፍት እንደሚደረጉ ይጠበቃል። በተመሳሳይ 8ቢሊዮን ብር በሚጠጋ በጀት ከባቱ እስከ አርሲ ነጌሌ ያለው 57ኪ.ሜ እና ከአርሲነጌሌ እስከ ሀዋሳ ያለው የ52 ኪ.ሜ የፍጥነት መንገዶች ግንባታ እየተካሄደነው፡፡ እነዚህም መንገዶች በቀጣይ ሁለት አመታት ሙሉ ለሙሉ ተጠናቀው ለትራፊክ ክፍት እንደሚደረጉ ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ከዚህ በተጨማሪ በመጨረሻው ምዕራፍ የሚገኘው ከሀዋሳ እስከ ሞያሌ የሚዘልቀው 500ኪ.ሜ መንገድእና የሞያሌ የጋራ የመተላለፊያ ጣቢያ በስድስት ኮንትራክተር ተከፍሎ ግንባታው ሲካሄድ የቆየ ሲሆን አሁን ላይ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት ሆኗል። የመጨረሻውን ምዕራፍ ግንባታ ለማካሄድ ወደ 6.3ቢሊዮንብር ወጪ የተደረገ ሲሆን ይህም ከአዲስ አበባ እስከ ሞያሌ ያለውን የመንገድ ኮሪደር ደረጃ ለማሳደግ ወጪ የተደረገውን የገንዘብ መጠን ከብር 31.2 ቢሊዮን በላይ እንዲሆን አድርጎታል፡ ልማት የሚያስፈልገው ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ከኢትዮጵያ መንግስት፣ከአፍሪካ ልማት ባንክ፣ከቻይናኤግዚምባንክ፣ከዓለም ባንክእና ከኮሪያ ኤግዚም ባንክ የተገኘ ነው፡ በተለይም የአፍሪካ ልማት ባንክ ከሀዋሳ እስከ ሞያሌ ያለውን መንገድእና የሞጆ መቂን የፍጥነት መንገድ ፋይናንስ በማድረግ የአንበሳውን ድርሻ ይወስዳል፡፡ የልማት አጋሮቹ ላደረጉት ሁለተናዊ ድጋፋም መሪዎቹ ከፋተኛ ምስጋና አቅርበዋል። ከዚሁ ጋር ተያይዞም የሞያሌ የጋራ የመተላለፊያጣቢያ/OSBP/የሀዋሳ-ሀገረማሪያም- ሞያሌ መንገድ አካል ሆኖ የተሠራ ሲሆን ይህ የጋራ የመተላለፊያ ጣቢያ/OSBP/ሰዎችም ሆነ ተሽከርካሪዎች ድንበር ሲያቋርጡ በሁለት ሀገራት ጉምሩክ፣ኢሚግሬሽን፣የጤና የመተላለፊያ፣ደረጃ መዳቢ አልፈው ሄደው በመዳረሻ ሃገር በተገነባው የየመተላለፊያ ጣቢያብቻ በመቆም አስፈላጊውን የመግቢያና የመውጭ አገልግሎቶች በጣቢያው ከሚገኙ የሁለቱ ሀገራት ባለሞያዎች ዘንድ ማግኘት እንዲችሉ የሚያደርግ ነው፡፡ በዚህም መሠረት በሁለቱም ሀገራት ድንበር ውስጥ የጋራ የየመተላለፊያ ጣቢያ መሠረተ ልማት የተገነባ ስለሆነ በአንዱ ሃገር ውስጥ በሚገኘው ጣቢያ ውስጥ የሁለቱም ሀገራት ሠራተኞችይገኛሉ፡፡ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ያስገነባው የጋራ የመተላለፊያ ጣቢያው መገንባትእና ሥራ መጀመር በድንበር ላይ የሚደረገውን የተንዛዛእና ረጅም የየመተላለፊያና የይለፍ ፈቃድ አሰጣጥ ስርዓት የተሳለጠና ፈጣን እንዲሆን በማድረግ በሁለቱ አገራት መካከል ያለውን የንግድሥራና ፍሰት ቀልጣፋ፣ አዋጭእና ውጤታማ ያደርገዋል፡፡ የዚህ ወሳኝ መሠረተ ልማት በይፋ ተመርቆ ሥራ መጀመር የኬንያንእና የኢትዮጵያን ጠንካራእና የረጅምጊዜ ግንኙነት የበለጠ የሚያጠናክር ሲሆን መንግስታችንም ለሁለቱ አገራትና ህዝቦች ሁለንተናዊ ልማትና ተጠቃሚነት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ያረጋገጠ ነው ብለዋል ዋና ዳይሬክተሩ ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ ። በመርሃ ግብሩ ላይ ከፍተኛ የፌዴራል ተቋማት የስራ ሃላፊዎች የኬኒያ ባለስልጣናት የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሽመልስ አብዲሳ የሶማሌ ክልል የስራ ሃላፊዎች አባገዳዎች የአጎራባች የከተማዋ ነዋሪች አባገዳዎችና ጥሪ የተደረገላች እንግዶች ታድመዋል።

የመልካሳ-ሶደሬ-ኑራሔራ-መተሐራ የመንገድ ፕሮጀክት ያጋጠመውን የወሰን ማስከበር ችግር ለመፍታት ያለመ የምክክር መድረክ ዛሬ በአዳማ ከተማ ተካሄደ። በውይይት መርሃ ግብሩ ላይ የትራንስፖርት ሚኒሰትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ፤ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የፕሮጀክት ማኔጅመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢነጂ. መሀመድ አብዱራህማን እና ሌሎች የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎችን ጨምሮ የአካባቢው የዞንና የወረዳ አመራሮች ተገኘተዋል፡፡ የመድረኩ ዋነኛ ትኩረት ፕሮጀክቱ ባለበት ከፍተኛ የሆነ የወሰን ማስከበር ችግር ምክንያት የተጓተተ በመሆኑ እነዚህ የወሰን ማስከበር ችግሮች በአስቸኳይ ተቃለው ፕሮጀክቱን ለማፋጠን ያለመ ነው፡፡ በመድረኩም ላይ የመንገድ ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቁ የሚጠበቅበትን አገልግሎት መስጠት ይችል ዘንድ በመንገድ ግንባታ ክልል ውስጥ ያሉ ቤቶችና ንብረቶች የአካባቢው መስተዳድር በፍጥነት ማስነሳት እንደሚገባው እንዲሁም የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሆነ አማካሪው አፈፃፀማቸውን ይበልጥ ሊያሻሽሉ እንደሚገባ ሚኒስትር ዲኤታው አሳስበዋል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የየአካባቢዎቹ የመስተዳድር አካላት በበኩላቸው የተነሱት ችግሮች ተጨባጭ መሆናቸውን በመገንዘብ ለፕሮጀክቱ መፋጠን ይበልጥ ለመስራት እንተጋለን ብለዋል፡፡ በዛሬው ውይይት የተቀመጠው የጋራ የመፍትሄ አቅጣጫ እንዲተገበር መላ የአካባቢውን ህዝብ በማሰተባበር ችግሩ እንዲፈታ እንደሚሰሩም ቃል ገብተዋል። በኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣንም በበኩሉ በኮንትራክተሩ እንዲሁም በአማካሪ ድርጀቱ በኩል የሚታዩ ውስንንቶች ካሉ እንዲታረሙ ይበልጥ እንደሚሰራ ተገልፃል። ይኸው የመልካሳ-ሶደሬ-ኑራሔራ-መተሐራ 94 ኪ.ሜ መንገድ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ በመስራቅ ሸዋ ዞን እና በ አርሲ ዞን ውስጥ የሚገኙ አምስት ወረዳዎችን የሚያገናኘ ነው፡፡ በምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ከተማን፤ ቦሰትና ፈንታሌ ወረዳዎችን የሚያሰተሳሰር ሲሆን በአርሲ ዞን ደግሞ በጀጁና መርቲ ወረዳዎችን ያቆራኛል፡፡ ግንባታውን በአንድ ነጥብ ሁለት ቢሊየን ብር ወጪ እየገነባ የሚገኝው የንኮማድ ኮንስትራክሽን የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲሆን የግንበታ ወጪው በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው። የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ECDSWCX የተባለ ድርጀት እያከናወነ ይገኛል።

57 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የቱርሚ-ኦሞ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመፋጠን ላይ ነው። ከአጠቃላይ የግንባታ ስራው አሁን ላይ 48 ኬሎሜትሩ ሙሉ ለሙሉ የአሰፓልት ግንባታ ስራው ተጠናቋል ። ቀሪ የግንባታ ክፍሉን በጥራት ገንብቶ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሰራ ነው። ስራውን ለማካሄድ የተመደበው ስምንት መቶ ዘጠና ሰባት ሚሊዮን ብር በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡ የመንገዱን ግንባታ በማካሄድ ላይ የሚገኘው ራማ ኮንስትራክሽን የተባለ ሀገር በቀል የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ ፕሮጀክቱን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ስታዲያ ኢንጂነሪንግ ወርክስ ኮንሰልታንት የተባለ ሀገር በቀል አማካሪ ድርጅት በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የቱርሚ-ኦሞ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ በደቡብ ክልል ውስጥ የምትገኘውን ቱርሚ ከተማን ከካንጋቴን ከተማ ጋር በማስተሳሰር የነበረውን የትራንስፖርት የመሰረተ ልማት ቁልፍ ችግር የሚፈታ ነው። ይህ መስመር ከዚህ ቀደም ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት ያልተዘረጋበትና የተወሰነው የመንገድ ክፍል ብቻ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ ሲሆን ፣ ከመንገዱ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንፃር ታይቶ በአሁኑ ወቅት ደረጃው ወደ አስፋልት ኮንክሪት አድጎ እየተሰራ ነው፡፡ መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በከተማ 14 ሜትር ፣ በገጠር ደግሞ 10 ሜትር ስፋት ይኖረዋል፡፡ እንደአጠቃላይ ፕሮጅክቱ በጥሩ አፈፃፀም ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ በተቀመጠው የጥራት ደረጃ እና የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው፡፡ የመንገዱ መገንባት ለተሸከርካሪዎች ደህንነት ከሚኖረው ፋይዳ ባሻገር ለምርት ትስስር መሳለጥ ፋይዳው የጎላ ነው። ከዚህ ቀደም ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በማሳጠር በቂ የሆነ የመንገድ መሰረተ ልማት ተጠቃሚ ያልሆነውን የአካባቢው ህብረተሰብ ደረጃውን የጠበቀ የመንገድ መሰረተ ልማት ተጠቃሚ በማድረግ የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በእጅጉ ያቃልለታል፡፡ በአካባቢው ለሚገኙ ትንንሽ ከተሞች ዕድገት የሚኖረው ፋይዳ ከፍተኛ ሲሆን ፣ እንደ ትምህርት እና ጤና ያሉ የመሰረተ ልማት ተቋማትን በአካባቢው በማስፋፋቱ ረገድም ጉልህ አስተዋፅኦ ይኖረዋል፡፡ የዚሁ የመንገድ አካል ትስስር የሆነው የወይጦ ቱሪሚ መስመርን በአሰፖልት ደረጃ ግንባታውን ለማካሄድ የጨረታ ሂደቱ በመጠናቀቅ ላይ ሲሆን በያዝነው አመትም ወደ ግንበታ ስራ ይሸጋገራል።

የምስራቅ እና የሰሜን ሸዋን የሀገራችን ክፍሎችን በአቋራጭ የሚያስተሳስረው የቢሾፍቱ - ጨፌ ዶንሳ - ሰንዳፋ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ስራ ዛሬ በትራንስፖርት ሚኒስትር ድኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ በኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ እንዲሁም በተቋማቱ ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች በመስክ የስራ ቅኘት ተጎበኘ። 55ኪ.ሜትር የሚረዝመው የቢሾፍቱ - ጨፌ ዶንሳ - ሰንዳፋ የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ግንባታው እየተከናወነ ነው፡፡ ዲዛይን እና ግንባታን በጋራ አካቶ የያዘው ፕሮጀክቱ በእስካሁኑ አፈጻጻም የተሰሩ ስራዎች ያጋጠሙ ችግሮችና ቀጣይ የስራ እቅዶችን በተመለከተ ለተቋማቱ የስራ ሃላፊዎች ገለጻ ተደርጎላቸዋል። በእስካሁኑ ክንውንም የካምፕ ግንባታ የመሬት ጠረጋ የአፈር ሙሌት ድልዳሎ ስራዎች እየተከናወኑ ነው። የአፈር ቆረጣ እና የውሃ መፋሰሻ ቱቦ የማምረት ስራዎችም እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱን በ974 ሚሊዮን ብር በሆነ ወጪ በመገንባት ላይ የሚገኘው በሀገር በቀሉ ራማ ኮንስትራክሽን ነው። የግንባታ ወጪው በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈነው ይኸው ፕሮጀክት በርካታ እስትራቴጂካዊ ጠቄሜታዎች ያሉት በመሆኑ በተያዘው የጊዜ ገድብ እንዲጠናቀቅ የስራ ሃላፊዎቹ አሳስበዋል። በመስመሩ ከፍተኛ ሰብል አምራች የሆኑ ወረዳዎችን እና ቀበሌዎችን የሚያስተሳስር በመሆኑ ለማዕከላዊ ገበያ የምርት አቅርቦት ሀገሪዊ ፋይዳው የጎላ በመሆኑ ይበልጥ በትኩረት እንዲሰራም አቅጣጫን አስቀምጠዋል። የመንገዱን ግንባታ ጥራት በመቆጣጠር ረገድ ሲ-ደብሊው-ሲ-ኢ እና ጂ-ኤንድ-ዋይ የተባሉ አማካሪ ድርጅቶች ዮአሺን ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ከተባለ የኮርያ ድርጅት ጋር በጥምረት ሲሆን ጥራትን በማስጠበቅ መንገዱ በተባለው ጊዜ እንዲጠናቀቅ እንዲተጉም አስገንዝበዋል ። በመስክ ቅኝቱ ላይ የታደሙት የራማ ኮንስትራክሽን ድርጅት ባለቤት አቶ ፍሬው ተድላ ተጨማሪ የማሽነሪእና የሰው ሀይልን ለፕሮጀክቱ ይበልጥ በመመደብ በተያዘው መርሃ ግብር ለማጠናቀቅ እንሰራለን ብለዋል። የመንገዱ የጎን ስፋት በወረዳ ከተማ 21.5 ሜትር ፣ በቀበሌ 12 ሜትር እንዲሁም በገጠር 10 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው እየተገነባ የሚገኘው፡፡ የቢሾፍቱ - ጨፌ ዶንሳ - ሰንዳፋ የግንባታ ፕሮጀክት አሁናዊ ይዞታው ጠጠር ደረጃ የነበረ ሲሆን መንገዱ ካለው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ አንጻር ታይቶ ነው በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ የሚገኘው። በቀጣይ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ከምስራቁ ወደ ሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል የሚደረገውን የትራንስፖርት እንቅስቃሴ አዲስ አበባ ከተማን መጠቀም ሳያስፈልግ በመዲናዋ ዳርቻ በአማራጭነት መጠቀም ያስችላል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ሶስት ድልድዮች እና የተለያዩ ፉካዎችና ከልቨርቶችን አካቶ እየተገነባ ያለ ፕሮጀክት ነው። በመስመሩ የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን ፍሰት በከፍተኛ ደረጃ በመጨመር በአካባቢው ያሉ ከተሞችን በማነቃቃት ይበልጥ ተጠቀሚ ያደርጋቸዋል:: የመንገዱ ግንባታ ስራ በ 2015 በጀት አመት በወርሃ ህዳር በኮንትራት ዉሉ መሰረት ለማጠናቀቅ በመስመሩ የሚገኙ የመስተዳድር አካላት ህብረተሰቡን በማስተባበር የሚጠበቅባቸውን እንዲወጡ የስራ ሀላፊዎች አስገንዝበዋል ።

204.8 ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የጋሸና-ላሊበላ-ሰቆጣ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ የጋሸና-ላሊበላ-ሰቆጣ መንገድ አካል የሆነው የጋሸና-ቢልባላ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ከአጠቃላይ 105 ኪ.ሜ ርዝመት ውስጥ 87 በመቶ የደረሰ ሲሆን በተያዘው ዓመት እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል። የጋሸና-ቢልባላ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ በአሁኑ ወቅት 78 ኪ.ሜትሩ የአስፋልት ንጣፍ ስራው ተከናውኗል። ፕሮጀክቱን 1.87 ቢሊዮን ብር በሆነ ወጪ በመገንባት ላይ የሚገኘው አለማቀፉ ቻይና ሬል ዌይ ኢንጅነሪንግ ቁጥር 3 የስራ ተቋራጭ ነው። የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ኢንጂነር ዘውዴ እና ዋይ ኤል ኤስ ኢንጂነሪንግ አማካሪ ድርጅቶች በጣምራ እያከናወኑት ይገኛል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም 99.8 ኪ.ሜትር የሚዘልቀው የመንገድ የፕሮጀክቱ ቀጣይ ክፍል የሆነው የቢልባላ-ሰቆጣ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ከአጠቃላይ የግንባታ ስራ ውስጥ 80 በመቶ ተጠናቋል። ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ቻይና ፈርስት ሃይ ዌይ ኢንጂነሪንግ ኮ.ሊሚትድ የተባለ የቻይና ዓለም አቀፍ የሥራ ተቋራጭ ድርጅት ነው፡፡ ሃገር በቀሉ ቤስት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ የቁጥጥርና የማማከር ሥራውን እያካሄደው ይገኛል። የጋሸና-ላሊበላ-ሰቆጣ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ቀሪዎቹን ስራዎች በተያዘው በጀት ዓመት በተገቢው የጥራት ደረጃና ፍጥነት እንዲጠናቀቁ ለማስቻል እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፡፡ የጋሸና-ላሊበላ-ሰቆጣን የመንገድ ፕሮጀክት ወጪ ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ካለው ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጠቀሜታ አንጻር እንዲሁም በቀጣይ መንግዱ ሊያስተናግድ ከሚችለው ብዛት ያለው ተሸከርካሪ አንጻር በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እየተገነባ ያለ መንገድ ነው። መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ በቂ የሆነ የመንገድ መሰረተ ልማት ያልነበረውን የአካባቢውን ሕብረተሰብ የዘመናዊ ትራንስፖርት ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል። አርሶ አደሮች ምርታቸውን በቀላሉና በተቀላጠፈ ሁኔታ ወደ ተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ለማመላለስ ያስችላቸዋል፡፡ የመንገዱ መገንባት ለሀገር ውስጥና ለውጪ ጎብኝዎች በዓለም የቅርስ መዝገብ ላይ ተመዝግቦ ያለውን የላሊበላን እና ሌሎች በአካባቢው የሚገኙ ጥንታዊ እና ታሪካዊ ቦታዎችን ለመጎብኘት ሁለተናዊ ፋይዳው የጎላ ነው።

ኢትዮጵያን ከደቡብ ሱዳን ጋር የሚያስተሳስረው የዲማ - ራድ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ተጠናቀቀ። 60 ነጥብ 2 ኪ .ሜ እርዝመት ያለው ይኸው የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፍጻሚውን ማገኘቱ አማራጭ የገቢ ወጪ ንግድን ለማሳለጥ ከፍተኛ ጠቀሜታን ያበረክታል። የክልሉን የመንገድ ትራንስፖርት ትስስርን ከማቀላጠፉም በላይ ኢትዮጵያ ከደቡብ ሱዳን ጋር ያላትን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት የማህበራዊ እና የኢኮኖሚ እንዲሁም የንግድ ልውውጥን የተሳለጠ ከማድረግ አኳያ የመንገዱ ፋይዳ ከፍተኛ ነው፡፡ የዲማ - ራድ ድልድይ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ለሀገራችን ዋነኛ የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኝላትን ቡናን ጨምሮ የፍራፍሬ ፣ ማር እና ቅመማ ቅመም ምርት ውጤቶችን ከምዕራቡ የአገሪቷ ክፍል ወደ ውጪ በመላክ ሀገራዊ ሚናው የጎላ ሲሆን በአካባቢው ያሉትን አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል ፡፡ በመስመሩ ላይ የሚገኙትን ከተሞች ፣ የእርሻና የኢንዱስትሪ ዞኖች እንዲሁም የቱሪስት መስህብ የሆኑ ስፍራዎችን ዘመናዊ በሆነ መንገድ በማስተሳሰር የጉዞ ጊዜንና ወጪን በመቀነስ ረገድ ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ መንገዱ ከዚህ ቀደም ለትራንስፖርት አመቺ ያልሆነ የተጎዳ ጠጠር መንገድ የነበረ ሲሆን መስመሩ ሊያበረክተው ከሚችለው ፋይዳ አኳያ ወደ አስፋልት ኮንክሪት ደረጃ እንዲያድግ ተደርጓል፡፡ ፕሮጀክቱን በኢትዮጵያ መንግስት በተመደበ 856 ሚሊዮን ብር ገንብቶ ያጠናቀቀው የኢትዮጵያ ኮንስተራክሽን ስራዎች ኮርፖራሽን ነው። የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ያከናወነው ደግሞ የኢትዮጵያ ዲዛይንና ቁጥጥር ስራዎች ኮርፖሬሽን ነው ፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም የደቡብና ጋምቤላ ክልልን የሚያገናኘው የዚሁ የመንገድ ትስስር አካል የሆነው የሚዛን ዲማ የመንገድ ፕሮጀክትም ከተወሰኑ ማስተካከያ ስራዎች በስተቀር ተጠናቋል ። ይህው ፕሮጀክት 91 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝመትን ይሸፍናል። ለፕሮጀክቱ ግንባታ 1 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር ወጪ ተደርጎበታል፡፡ ከዚህም ውስጥ 74 በመቶውን ወጪ ከአለም ባንክ በተገኘ ብድር የተሸፈነ ሲሆን የተቀረውን 26 በመቶ የኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ይሆናል፡፡ የመንገድ ግንበታውን እያከናወነ የሚገኘው MCC17 የተባለ የቻይና አለማቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው ፡፡ የማማከሩን ተግባር ደግሞ የህንዱ አርቪ አሶሲዬት ኮንሰልታንሲ ከኢትዮጽያው አማካሪ ድርጅት ኔት ጋር በጋራ እየሰሩ ነው ፡፡