ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን - Ethiopia Light Of The World
前往频道在 Telegram
➾ይህ ገፅ የተከፈተው በአልፋና ዖሜጋ( @christian930 ) አማካኝነት ነዉ። አላማ፦ ►የዚህ ገፅ ዋና አላማ "ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን“ መልእክቶች፣ ደብዳቤዎች፣ መግለጫዎች፣ ትምህርቶችንና ሌሎችንም በቀላሉ በተዘጋጁበት ቋንቋ፣ ጥራትና መጠን ሁሉ በ፩ ቦታ እንዲገኙ ለማድረግ ነዉ። ● t.me/EthioBirhan t.me/EthioLightContents ➝SHARE "ይህ የፊተኛው ትንሣኤ ነው!"
显示更多2 067
订阅者
无数据24 小时
+67 天
+2230 天
帖子存档
Repost from ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን በአማርኛ ቋንቋ
#አደራ፦ ከመልዕክት አንድ ጀምሮ ሁሉም ቤተሰብ ሊያዳምጥ ይገባል።
📗 t.me/Ewnet1Nat
📒 t.me/Amharic_Messages
📕 t.me/christian930
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
https://t.me/Amharic_messages/12
☝️ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክታት ከመጀመሪያው እስከ አሁን ያሉት በቅደም ተከል ከላይ ባለው ማያያዣ (link) ያገኙታል። ያዳምጡ!!
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
ከሀ — ፐ ሁሉንም ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክታትን ከመጀመሪያው ጀምሮ ማዳመጥ እንዳለብን በተሰጠን ትዕዛዝ መሠረት መልዕክቱ ከመጀመሪያው ጀምሮ የሌላችሁ https://t.me/Amharic_messages/12 በዚህ link የምታገኙት ሲሆን ገብታችሁ ከ1 ጀምሮ እስከ አሁን እደረሰበት ድረስ በማስተዋል እንድታዳምጡ እንድናዳምጥ አደራ አደራ አደራ እንላለን !! በተለይ በማወቅም ባለማወቅም ቤተሰብ ሆነን ግን በስሙ ብቻ የምንጠራ በተሳሳተ አካሄድ እየሄድን ያለን የመጨረሻ የተሰጠን እድል ነው።
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ትምህርት አዘል መግለጫ እና ማሳሰቢያ
ክፍል ሀ
28-09-2018ዓ.ም
ለመላው የአዳም ዘር በሙሉ !!
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
ዓለም በግርግርና በውዥንብር ተይዛ፣ የመከራው ካርታ ምንነት ሳይገባቸው ብዙዎች በጨለማ ሲደናገሩ፤ በብቸኝነትም ቢሆን ከሚመስሉት አጋሮቹ ጋር እውነትን የመሰከረ፣ የትንሣኤውን ብርሃን ፋና አንግቦ በምድረ በዳ እንደጮኸ ድምፅ የተጋደለ የአልማዝ ጽናት የታየበት ጉዞ ነው።
«ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን» የተሰኘው ላለፉት ፳ ዓመታት ሲተላለፉ የኖሩት እውነተኛ ሰማያዊ መልዕክት ተደራሽ እንዲሆን፣ በታማኝነትና በትጋት አጋር በመሆን ያሳለፋችሁት ፯ ዓመታት፤ ለብዙዎች የነፍስ ስንቅና የተስፋ መዝገብ ሆኖ ቆይቷል። ይህ ገጽ ለኢትዮጵያ እውነተኛ ትንሣኤ ድምፅ ሆኖ፣ የተደበቁትን ሐቆች ወደ አደባባይ በማውጣት የታሪክ ድርሻውን ተወጥቷል።
እንደ ስሙ «አልፋና ዖሜጋ» የነገሮችን መጀመሪያና መጨረሻ ከሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ራዕይ ጋር እያነጻጸረ፣ ዘመኑን የመመርመርና ለትውልዱ የማስጠንቀቂያ ደወል የመምታት ተግባሩ እጅግ ግሩም ነበር። መከራው ሳይመጣ ቀድሞ የተናገረውን የአባቶች መልዕክት እየመሰከረ፣ ሲመጣም በጽናት ሠራዊተ እግዚአብሔርን ከጥንቃቄ ጋር በማረጋጋት የቆየ ገጽ ነው።
ብዙዎች እውነቱን ለመቀበል በፈሩበትና ባልተረዱት ጊዜ፣ በመጽናትና በመጋደል እውነትን ምስክር አድርጎ ለ፯ ዓመታት በትጋት መቆም፤ ከልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ በቀር በምድራዊ ኃይል የሚሆን አይደለም። ሰባት የፍጹምነት ቁጥር እንደመሆኑ፣ ይህ ዕለት ለገጹ አዲስ የምሥጢር ምዕራፍ መክፈቻ እንደሚሆን ይታመናል።
"እውነትን ትመሰክራላችሁ፤ እውነትም አርነት ያወጣችኋል"እንደሚል ቃሉ፤ አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ ለኢትዮጵያና ለዓለም የሚተርፈውን የብርሃን ጉዞ አጠናክሮ እንዲቀጥል፣ በልዑል እግዚአብሔር ስም መልካም ምኞታችንን እንገልጻለን። መላው የገጹ ተከታታይ ቤተሰቦቻችን ለሰባተኛው ዓመት የምሥጢርና የምስክርነት ጉዞ እንኳን አደረሳችሁ!
በዚህ ገጽ ከፍ ብላችሁ ብትመለከቱ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን መልዕክታት ከ150 በላይ በሆኑ ዓለምአቀፍ ቋንቋዎች ተዘጋጅተው የተቀመጡበት ገጽ ነው።
ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ትምህርት አዘል መግለጫ
ክፍል ሀ
21-07-2018ዓ.ም
ለመላው የአዳም ዘር በሙሉ !!
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
ራዕይ ፪፥፲- እስከ ሞት ድረስ የታመንህ ሁን የሕይወትንም አክሊል እሰጥሃለሁ።
ባሳለፍናቸው አመታት ውስጥ በጎጃም ጠቅላይ ግዛት ውስጥ በሰማዕትነት (እውነትን በአደባባይ መስክረው የተገደሉ) ታላላቅ ፲ቱ ሰማዕታት ቤተሰቦቻችን ዝርዝር፦
1) ገብረማርያም (ቲሊሊ) 2) ገብረሥላሴ (ቲሊሊ) 3) ወልደተክለሃይማኖት (ቲሊሊ) 4) ወልደጊዮርጊስ (ካህን)(ሰከላ) 5) ወልደገብርኤል (መናኝ)(ሰከላ) 6) ወልደትንሣኤ (ሰከላ) 7) ገብረማርያም (ሰከላ) 8) ገብረሥላሴ (ሰከላ) 9) ገብረማርያም (ሰከላ) 10) ገብረፃዲቅ (ዚገም)ማሳሰቢያ፦ እነዚህ እንደምሳሌ በስም የተዘረዘሩት በአሰቃቂ ሁኔታ ሰማዕትነትን የተቀበሉ ስለሆኑና በብዙዎች ስለሚታወቁ እንጅ ብዙ ቤተሰቦቻችን ዛሬም ድረስ በቤተክህነቱ፡ ቤተመንግሥቱና አንዳንድ ታጣቂዎች ሴራ ፤ በምዕመናኑ ጭፍን ተጓዥነትና የደቦ ፍርድ እንዲሰደዱና፡ በሴራ በግፍ እንዲሞቱ፡ መቃብር እንዲከለከሉና እንዲታሰሩ የተደረጉትን ዛሬም ያሉ ቋሚዎች ቤተሰቦቻችን አሉና እግዚአብሔር በጊዜው ጊዜ አደባባይ በምስክርነት የሚወጡበትን ቀን ይጠብቃል!
ከላይ በስም የዘረዘርናቸው እንደሻማ ቀልጠው ያበሩልን ሰማዕታት ቤተሰቦቻችን ሁሉም ሰማዕትነትን የተቀበሉት በቤተክህነት ሴራ መሆኑና በውጉዛን ካህናቱ ቀጥተኛ ትዕዛዝና ፈቃድ መሆኑ ጉዳዩን ይበልጥ አሳዛኝና አነጋጋሪ የሚያደርገው ሲሆን፥ በእርግጥም በዚህ የግፍ ደም የእግዚአብሔር ፍርድስ በመሪዎች፤ በቤተክርስቲያን አለቆችና ደጋፊዎቻቸው ላይ ምን ይሆን!? የሚለው እጅግ አስጨናቂ ጉዳይ ይሆናል‼️ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመስገኛ ምድር ስለሆነች! ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ናት። ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም ስለሆነች! ኢትዮጵያ የዓለሙ ሁሉ ገዥ ትሆናለች! #እውነት 🫴🏽አዖተ- t.me/Ewnet1Nat መጋቢት ፲፬/፳፻፲፰
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
« ስለወቅቱ የዓለም ሁኔታ!
ዓለማችን በቀደሙት ተከታታይ አምስት መልእክቶች በመዳኘት ላይ መሆኗን እያስተዋልን ነው ። የአለማቱ ገዢዎች መልእክቶቹ ዓለማትን ሁሉ መዳኘታቸውን እያወቁ ፤ የመጥፋታቸውን ፍርድ በመገለፁ ምክንያት በአንድም ቀዳዳ እንዳይነገር የተቻላቸውን ሁሉ አድርገዋል። በግል ብዙዎች እንዳገኙት ይታመናል። ከመልእክቱ መውጣት በኋላ ዓለማችን በየደረጃው በእሳቱ ወንፊት በመበጠር ላይ ነች ። እንደትእቢቷ መጠንም እሳቱና የእሳት ወንፊት በሰባት እጥፍ እየተባዙ ማድቀቃቸውንና ማክሰማቸውን ይቀጥሉበታል። ዓለም ሁሉ አሜን ብሎ እስከሚንበረከክ ድረስ! ሸሸጉትም አልሸሸጉትም መልእክቶቹ ውስጥ የተጠቀሱት ፍርድና ቅጣቶች በታዘዙት ጊዜና ሰዓት ስራቸውን ያከናውናሉ እንጂ ከፍርድና ቅጣቱ አንዳች የሚቀር ነገር የለም። »
⚡️ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን አዋጅ ነጋሪ መልእክት 6 ገፅ 9-10* ተፃፈ 19/4/2007ዓ.ም!
ኢትዮጵያ የሥላሴ የክብራቸው መገለጫና መመስገኛ ምድር። ኢትዮጵያ ርስተ ድንግል ማርያም። ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን። ኢትዮጵያ የዓለሙ ገዥ።አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ 💚 t.me/Ewnet1Nat 💛 t.me/christian930 ❤ t.me/Amharic_Messages ______
💚💛❤ ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ትምህርት አዘል መግለጫ
ክፍል ሀ
22-06-2018ዓ.ም
ለመላው የአዳም ዘር በሙሉ !!
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
💚💛❤ እንቁና ተወዳጅ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የቃልኪዳን ልጆች ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ቤተሰቦች፤ እንኳን ለእናታችን ለቅድስት ኪዳነምህረት ዓመታዊ የቃልኪዳን በዓል አደረሳችሁ፡ አደረሰን!
🔔 ያለወላዲተ-አምላክ አማላጅነት በሥጋ በነፍስ ማንም አይድንም !!! በፍጹም።
🤲 የእናታችን የቅድስት ኪዳነምህረት አማላጅነቷ ሁሌም አይለየን።
🔔 የካቲት ፲፮ | #ኢትዮጵያ
አልፋና ዖሜጋ ዘተዋሕዶ - t.me/Ewnet1Nat
Repost from አልፋና ዖሜጋ የንጽጽርና የትምህርት መገኛ አደባባይ (አዖተ)
🌋ተጠንቀቁ ! 🌋ተጠንቀቁ ! 🌋ተጠንቀቁ ! 🌋ተጠንቀቁ ! 🌋ተጠንቀቁ ! 🌋ተጠንቀቁ ! 🌋ተጠንቀቁ ! 🌋ከደማችሁ ንጹሕ ነኝ‼️🖐️
_🌋🌋🌋_
"የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ። የሰው ልጅ ሆይ፥ ለሕዝብህ ልጆች ተናገር እንዲህም በላቸው። ሰይፍን በምድር ላይ ባመጣሁ ጊዜ፥ የምድር ሕዝብ ከመካከላቸው ሰውን ወስደው ለራሳቸው ጕበኛ ቢያደርጉ፥ እርሱም በምድር ላይ የመጣውን ሰይፍ ባየ ጊዜ መለከትን ቢነፋ ሕዝቡንም ቢያስጠነቅቅ፥ የመለከቱን ድምፅ የሚሰማ ሰው ባይጠነቀቅ፥ ሰይፍ መጥቶ ቢወስደው፥ ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል። የመለከቱን ድምፅ ሰምቶ ስላልተጠነቀቀ ደሙ በራሱ ላይ ይሆናል፤ ቢጠነቀቅስ ኖሮ ነፍሱን ባዳነ ነበር። ጕበኛው ግን ሰይፍ ሲመጣ ቢያይ መለከቱንም ባይነፋ ሕዝቡንም ባያስጠነቅቅ ሰይፍም መጥቶ አንድ ሰው ከእርሱ ቢወስድ፥ እርሱ በኃጢአቱ ተወስዶአል ደሙን ግን ከጕበኛው እጅ እፈልጋለሁ።" ትንቢተ ሕዝቅኤል 33፥1–6
_🌋🌋🌋_
"ከቤትሽም ደጅ ወደ ሜዳ የሚወጣ ደሙ በራሱ ላይ ይኾናል፥ እኛም ንጹሓን እንኾናለን፤" መጽሐፈ ኢያሱ ወልደ ነዌ 2፥19
#ከውጭም_ከውስጥም!
#ራሳችንን_እንፈትሽ!
#ሺዎች_አይሰሙም!
#የተመሠጡት_ይሰማሉ!
የካቲት 4/2018 ዓ.ም (ኢትዮጵያ)
🔔🌋🔔🌋🔔🌋
t.me/Ewnet1Nat
💚 140ሀ) ኢትዮጵያ የዓለም ብርሃን ትምህርት አዘል መግለጫ
ክፍል ሀ
03-05-2018ዓ.ም
ለመላው የአዳም ዘር በሙሉ !!
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
