EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 537 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 329,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 179 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 537 名订阅者。
根据 03 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 31,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.36%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.21% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 097 次浏览,首日通常累积 2 520 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 04 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 537
订阅者
-124 小时
-167 天
+3130 天
帖子存档
15 537
ለበርካታ ዓመታት በብልሽት ቆሞ የነበረው የጢስ አባይ 2 ኃይል ማመንጫ አንድ ዩኒት ተጠግኖ ሥራ ጀመረ
………..////…………
ከስምንት ዓመታት በላይ በብልሽት ምክንያት የቆመው የጢስ አባይ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ አንድ ዩኒት ሥራ ጥገና ተጠናቆ ዩኒቱ 25 ሜጋ ዋት ኢነርጂ ማምረት መጀመሩን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደጀኔ ጉታ አስታወቁ፡፡
ኃላፊው እንደገለፁት የዩኒቱ ውሃ መውጫ በደለል ስለተሞላና የተርባይን ሻፍት ዝንፈት በማጋጠሙ ዩኒቱ ከስምንት ዓመታት በላይ ሥራ አቁሞ ነበር።
ችግሩን ለመቅረፍም የውጭ ድርጅቶች ከተቋሙ የፋይናንስ አቅም እና ከጣቢያው አገልግሎት በላይ የሆነ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ በመጠየቃቸው የተቋሙ ሠራተኞች በራስ ተነሳሽነት ሥራውን መጀመራቸውን ተናግረዋል።
የጥገና ቡድኑ መሪና የፊንጫ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሹመት በላቸው በበኩላቸው የጥገና ሥራው ከተጀመረ በኋላ የተርባይን ሻፍት ዝንፈትን የማስተካከል፣ ዩኒቱ እንዲሰራ ለማድረግ ተሸከርካሪ አካሉን ወይም ሮተር ከፍ የማድረግ (Lifting Pump)፣ የተርባይኑን ተሸከርካሪ አካል የማስተካከል ሥራዎች (Thrust bearing adjustment)፣ የአውቶማቲክ የቮልቴጅ መቆጣጠሪያ (Automatic Voltage Regulator) ሥራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል፡፡
ጠላቂ ዋናተኞችን በመጠቀም የተቀረቀረን የድራፍት ቱብ በር ማውጣት( removal of stuck draft tube gate by deep water divers ) ሥራዎች መሰራታቸውንም አስታውሰዋል፡፡
የጀነሬተር ስቴተር ዋይንዲንግ በሌላ የመተካት እና ኤሌክትሪክ በውስጡ ሲያልፍ የኃይል ጭነትን የመቆጣጠር የሚያግዘውን (excitation system) ሥርዓት የማስተካከል ስራ እንዲሁም Unit Automation, Rotor pole winding and Trbine guide bearing በአዲስ የመቀየር ስራ መሰራቱንም ጠቁመዋል።
ለዓመታት የቆመውን ዩኒት የተቋሙ ባለሙያዎች በኃላፊነት ስሜት በመንቀሳቀስ በትናንትናው ዕለት 25 ሜጋ ዋት እንዲጭን በማድረግ ሥራው በስኬት መጠናቀቁን ገልፀዋል።
የተጠገነው ዩኒት በሙሉ አቅሙ 30 ሜጋ ዋት መጫን እንደሚችል አቶ ሹመት አስታውቀዋል፡፡
ለረጅም ዓመታት ያልተንቀሳቀሰ ዩኒትን በተቋሙ ባለሙያዎች የመጠገን ሥራ እየተለመደ ነው ብለዋል።
ይህ ስራ እንዲሳካ እገዛ ያደረጉትን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች እንዲሁም የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ኃላፊዎችና ሠራተኞች አመስግነዋል።
የጢስ አባይ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ የጀመረው በ1993 ሲሆን 72 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም እንዲኖረው ተደርጎ የተገነባ ጣቢያ ነው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 26 ቀን 2014 ዓ.ም
15 537
ተቋሙ ባለፉት 6 ወራት 7 ሺህ 668 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ አመንጭቷል
……///…….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2014 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 6 ወራት 7 ሺህ 668 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ አመንጭቷል፡፡
ከመነጨው ኤሌክትሪክ ውስጥ 7 ሺህ 372 ጊጋ ዋት ሰዓት ከውሃ፣ 270 ነጥብ 59 ጊጋ ዋት ሰዓት ከንፋስ እና ቀሪው 24 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ደግሞ ከእንፋሎት የመነጨ ነው፡፡
ተቋሙ በ6 ወራት ውስጥ ለማመንጨት ያቀደው ወደ 9 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ቢሆንም 7 ሺህ 668 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማመንጨት የዕቅዱን 84 ነጥብ 4 በመቶ አሳክቷል፡፡
በግማሽ ዓመቱ የመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ2 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል፡፡
በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በነበረው ጦርነት አሸባሪው የህወሓት ወራሪ ቡድን በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ያደረሰው ውድመት ለዕቅድ አፈፃፀም ልዩነቱ በምክንያትነት ተጠቅሷል፡፡
በተጨማሪም ተቋሙ በጦርነቱ ሳቢያ የተከዜና የአሸጎዳ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ያሉበትን ሁኔታ ማወቅ ካለመቻሉም ሌላ ተቋሙ ያቀደውን የኢነርጂ ምርት ለማሳካት ተፅዕኖ አሳድሮበታል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 26 ቀን 2014 ዓ/ም
15 537
ተቋሙ በአፋር ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖች በዓይነትና በጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አደረገ
........////.........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሸባሪው ህወኃት በአፋር ክልል በፈፀመው ወረራ ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል የ5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።
ድጋፉን ለክልሉ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ቢሮ ኃላፊና የሀብት አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አህመድ መሐመድ ዛሬ ያስረከቡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ ናቸው።
በርክክብ ሥነስርዓቱ ላይ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጦርነቱ የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ከመጠገን ጎን ለጎነ የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች በጦርነቱ የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመርዳት 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ግምት ያለው የዓይነት እንዲሁም 3 ሚሊዮን ብር የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል።
ተቋሙ ሠራተኞቹን በማስተባበር ያደረገው የዓይነት ድጋፍ የህፃናት አልሚ ምግብ፣ መኮረኒ፣ ዱቄት፣ አልባሳትና የንጽህና መጠበቂያ ቁሶችን ያካተተ ነው።
የክልሉ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ቢሮ ኃላፊና የሀብት አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ በካሳጊታ፣ ቡርቃና ኤሊ ውሃ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ከአንድ ወር ከሃያ ቀን በላይ በክልሉ ኤሌክትሪክ ሲቋረጥ ክልሉ ለጀነሬተር ነዳጅ ወጪ ከ9 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የኤሌክትሪክ መሰረተልማቶችን በፍጥነት በመጠገን ከአፋር ህዝብ ጎን መቆሙን በተግባር በማሳየቱ አመስግነዋል።
አሁን በህወኃት ጦርነት የተከፈተባቸውና የተወረሩ አካባቢዎች ነፃ ሲወጡ እንደ ከዚህ ቀደሙ ድጋፉ እንደማይለየን እምነት አለን ሲሉ ተስፋቸውን ገልፀዋል።
በክልሉ የዞን ሁለት አምስት ወረዳዎች ብቻ ከሦስት መቶ ሺህ ሰው በላይ ተፈናቅሎ እርዳታ እንደሚፈልግ ኃላፊው ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቀደም ሲል በአማራ ክልል በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች ሰባት ሚሊየን ብር የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 21 ቀን 2014 ዓ/ም
15 537
በእሳት አደጋ የተነሳ ተቋርጦ የነበረው የወልድያ ከተማና አካባቢያው ዳግም ኤሌክትሪክ አግኝቷል
........///......
ከደሴ የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ ወልድያ ማከፋፋያ ጣቢያ በተዘረጋው የ66 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በደረሰ ቃጠሎ የተነሳ የተቋረጠው ኤሌክትሪክ የወልዲያ ከተማና አካባቢው ዳግም ኤሌክትሪክ አግኝቷል።
ትናንት የደረሰውን የኤሌክትሪክ ምሰሶ ቃጠሎ በሌላ በመተካት ወልድያ፣መርሳ፣ ውጫሌ እና አካባቢያቸ ዳግም ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ርብርብ ሲደረግ ቆይቶ ወልዲያ ከደቂቃዎች በፊት ኤሌክትሪክ ማግኘት ችላለች።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች የቴክኒክ ድጋፍ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ መንግስቴ እንደገለፁት ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል ማግኘት እንዲችሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ምሰሶና ሌሎች ግብዓቶችን ሲያቀርብ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎች የቴክኒክ ሥራዎችን በመስራት ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል።
በአሁኑ ሰዓት ወልዲያ ኤሌክትሪክ ማግኘት የቻለች ሲሆን በየደረጃው ሌሎች ከተሞችም ኤሌክትሪክ እንደሚያገኙ ኃላፊው ገልፀዋል።
በጥገናው ላይ ርብርብ ሲያደርጉ የቆዩት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎች መሆናቸው እየታወቀ የወልድያ ዲስትሪክት ሠራተኞች ሥራውን እንደሰሩ የተገለፀበት አግባብ ትክክል ባለመሆኑ እንዲታረምና ህብረተሰቡም ይህን እንዲረዳ አቶ ተስፋዬ አሳስበዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 20 ቀን 2014 ዓ.ም
15 537
በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈረመ
......../////.......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የጂኦ ስፓሻል ኢንፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የጂኦ ስፓሻል መረጃ ለመለዋወጥና በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸው የመግባቢያ ሥምምነት በዛሬው እለት ተፈራርመዋል፡፡
የመግባቢያ ሰነዱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የጂኦ ስፓሻል ኢንፎርሜሽን ኢንስቲቱዩት ዋና ዳሬክተር ዶ/ር ቱሉ በሻ ናቸው፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ በፊርማ ሥነ - ሥርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ተቋሙ ከዳሰሳ ጥናት አንስቶ እስከ ፕሮጀክት ትግበራው ድረስ ለሚያከናውነው ሥራ የጂኦ ስፓሻል ቴክኖሎጂ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
ቴክኖሎጂውን በአግባቡ መጠቀም ወጪ ቆጣቢ በሆነ መልኩ ለመስራት እና በተገቢው ሁኔታ ለማስተዳደር ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል ፡፡
የትብበር ስምምነቱ በሀገር ውስጥ ያለውን አቅም አስተባብሮ ተቀራርቦ በመስራት የሀገር ሀብትን በተገቢው ሁኔታ ለመጠቀም፣ የእውቀት ሽግግርና የአቅም ግንባታ ሥራዎችን በሁለቱ ተቋሟት ለማስፋፋት ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል።
የመግባቢያ ሥምምነቱ ሁለቱ ተቋማት በመረጃ በመረጃ ልውውጥ፣ በቴክኖሎጅ ሽግግር፣ በምርምርና ልማት ተቋማቱ በሚያከናውኗቸው ፕሮጀክቶች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል እንደሚያስችል በመድረኩ ላይ ተገልጿል፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዱዓለም ሲኣ በበኩላቸው የመግባቢያ ሰነዱ የዘርፉን አቅም ለማገዝ፣ የግንባታ ሄደቶችን ለመከታተል እንዲሁም የኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽን ሥራ በዲጂታል ቴክኖሎጂ መረጃ አሰባስቦ አስፈላጊውን ሥራ ለማከናወን ያግዛል ብለዋል፡፡
በዚህም ተቋሙን ወደ ፊት የሚያራምድ እና ዓለም አቀፍ ከሆኑ ተመሳሳይ ተቋማት የሚሰሩትን አሰራር ለመተግበር እንደሚያስችል አቶ አንዱዓለም ገልጸዋል፡፡
የጂኦ ስፓሻል ኢንፎርሜሽን ኢንስቲቱዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቱሉ በሻ በበኩላቸው የኃይል ዘርፉን መሰረተ ልማት ማዘመን ሃገራችን በቀጣይ 10 ዓመታት ለማሳካት ላቀደቸው ሁለተናዊ እድገት ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡
በመሆኑም ተቋማቸው ያለውን የካበተ ልምድ ለማከፈል እና አብሮ ለመስራት እድል በማገኘቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡
የትብብር ስምምነቱ ከኢነርጂ ተደራሽነት ጋር በተያያዘ የብሔራዊ የሀብት ጠቋሚ መረጃ (resource mapping) ፣ የብሔራዊ የመሰረተ ልማት የመረጃ ልውውጥ፣ የሶፍት ዌር ማበልፀግና የኢንፎርሜሽን ደህንነት አገልግሎት፣ የስልጠናና ልምድ ልውውጥ፣ የሳይንሳዊ ዕውቀት፣ የቴክኖሎጂ እና መረጃ ልውውጥ እንዲሁም ውጤታማ የጂኦ ስፓሻል መረጃ አያያዝና አተገባበር ላይ በጋራ ለመስራት እንደሚያስችል በመርሃ ግሩ ላይ ተጠቁሟል ፡፡
በፊርማ ሥነ-ስርአቱ ላይ ከጂኦስፓሻል ኢንፎርሜሽን ኢንስቲቱዩት የመጡ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሞያዎች ጂኦ ስፓሻል ለኃይል ዘርፍ የሚኖረውን ጠቀሜታ በተመለከተ ገለፃ አድርገዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥር 20 ቀን 2014 ዓ.ም
15 537
የሚዲያ ጥቆማ /ለሁሉም መገናኛ ብዙሃን/
……..////……
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በጂኦስፓሻል ኢንፎርሜሽን ኢንስቲትዩት መካከል ጥር 20 ቀን 2014 ዓ.ም ሜክሲኮ በሚገኘው የኢ. ኤ. ኃ. ዋና መስሪያ ቤት ከጧቱ 3:00 ሰዓት ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ይፈረማል።
በፊርማ ሥነስርዓቱ ላይ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ይገኛሉ። በመሆኑም በተጠቀሰው ቀን፣ ቦታ እና ሰዓት ተገኝታችሁ የዜና ሽፋን እንድትሰጡን በአክብሮት እንጠይቃለን።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
