ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 537 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 329 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 179 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 537 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 03 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 31، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.36‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.21‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 097 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 520 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 04 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 537
المشتركون
-124 ساعات
-167 أيام
+3130 أيام
أرشيف المشاركات
photo content

photo content
+3

photo content

photo content

photo content

photo content

የዜና ጥቆማ -ለሁሉም መገናኛ ብዙሃን

ለበርካታ ዓመታት በብልሽት ቆሞ የነበረው የጢስ አባይ 2 ኃይል ማመንጫ አንድ ዩኒት ተጠግኖ ሥራ ጀመረ ………..////………… ከስምንት ዓመታት በላይ በብልሽት ምክንያት የቆመው የጢስ አባይ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ አንድ ዩኒት ሥራ ጥገና ተጠናቆ ዩኒቱ 25 ሜጋ ዋት ኢነርጂ ማምረት መጀመሩን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ አቶ ደጀኔ ጉታ አስታወቁ፡፡ ኃላፊው እንደገለፁት የዩኒቱ ውሃ መውጫ በደለል ስለተሞላና የተርባይን ሻፍት ዝንፈት በማጋጠሙ ዩኒቱ ከስምንት ዓመታት በላይ ሥራ አቁሞ ነበር። ችግሩን ለመቅረፍም የውጭ ድርጅቶች ከተቋሙ የፋይናንስ አቅም እና ከጣቢያው አገልግሎት በላይ የሆነ ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ በመጠየቃቸው የተቋሙ ሠራተኞች በራስ ተነሳሽነት ሥራውን መጀመራቸውን ተናግረዋል። የጥገና ቡድኑ መሪና የፊንጫ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሹመት በላቸው በበኩላቸው የጥገና ሥራው ከተጀመረ በኋላ የተርባይን ሻፍት ዝንፈትን የማስተካከል፣ ዩኒቱ እንዲሰራ ለማድረግ ተሸከርካሪ አካሉን ወይም ሮተር ከፍ የማድረግ (Lifting Pump)፣ የተርባይኑን ተሸከርካሪ አካል የማስተካከል ሥራዎች (Thrust bearing adjustment)፣ የአውቶማቲክ የቮልቴጅ መቆጣጠሪያ (Automatic Voltage Regulator) ሥራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል፡፡ ጠላቂ ዋናተኞችን በመጠቀም የተቀረቀረን የድራፍት ቱብ በር ማውጣት( removal of stuck draft tube gate by deep water divers ) ሥራዎች መሰራታቸውንም አስታውሰዋል፡፡ የጀነሬተር ስቴተር ዋይንዲንግ በሌላ የመተካት እና ኤሌክትሪክ በውስጡ ሲያልፍ የኃይል ጭነትን የመቆጣጠር የሚያግዘውን (excitation system) ሥርዓት የማስተካከል ስራ እንዲሁም Unit Automation, Rotor pole winding and Trbine guide bearing በአዲስ የመቀየር ስራ መሰራቱንም ጠቁመዋል። ለዓመታት የቆመውን ዩኒት የተቋሙ ባለሙያዎች በኃላፊነት ስሜት በመንቀሳቀስ በትናንትናው ዕለት 25 ሜጋ ዋት እንዲጭን በማድረግ ሥራው በስኬት መጠናቀቁን ገልፀዋል። የተጠገነው ዩኒት በሙሉ አቅሙ 30 ሜጋ ዋት መጫን እንደሚችል አቶ ሹመት አስታውቀዋል፡፡ ለረጅም ዓመታት ያልተንቀሳቀሰ ዩኒትን በተቋሙ ባለሙያዎች የመጠገን ሥራ እየተለመደ ነው ብለዋል። ይህ ስራ እንዲሳካ እገዛ ያደረጉትን የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች እንዲሁም የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ኃላፊዎችና ሠራተኞች አመስግነዋል። የጢስ አባይ 2 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ የጀመረው በ1993 ሲሆን 72 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም እንዲኖረው ተደርጎ የተገነባ ጣቢያ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 26 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

ተቋሙ ባለፉት 6 ወራት 7 ሺህ 668 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ አመንጭቷል ……///……. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በ2014 በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ 6 ወራት 7 ሺህ 668 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ አመንጭቷል፡፡ ከመነጨው ኤሌክትሪክ ውስጥ 7 ሺህ 372 ጊጋ ዋት ሰዓት ከውሃ፣ 270 ነጥብ 59 ጊጋ ዋት ሰዓት ከንፋስ እና ቀሪው 24 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ደግሞ ከእንፋሎት የመነጨ ነው፡፡ ተቋሙ በ6 ወራት ውስጥ ለማመንጨት ያቀደው ወደ 9 ሺህ ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ ቢሆንም 7 ሺህ 668 ጊጋ ዋት ሰዓት ኤሌክትሪክ በማመንጨት የዕቅዱን 84 ነጥብ 4 በመቶ አሳክቷል፡፡ በግማሽ ዓመቱ የመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ2 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል፡፡ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል በነበረው ጦርነት አሸባሪው የህወሓት ወራሪ ቡድን በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ያደረሰው ውድመት ለዕቅድ አፈፃፀም ልዩነቱ በምክንያትነት ተጠቅሷል፡፡ በተጨማሪም ተቋሙ በጦርነቱ ሳቢያ የተከዜና የአሸጎዳ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎች ያሉበትን ሁኔታ ማወቅ ካለመቻሉም ሌላ ተቋሙ ያቀደውን የኢነርጂ ምርት ለማሳካት ተፅዕኖ አሳድሮበታል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 26 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+3

ተቋሙ በአፋር ክልል ለተፈናቀሉ ወገኖች በዓይነትና በጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አደረገ ........////......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሸባሪው ህወኃት በአፋር ክልል በፈፀመው ወረራ ለተፈናቀሉ ወገኖች የሚውል የ5 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ አድርጓል። ድጋፉን ለክልሉ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ቢሮ ኃላፊና የሀብት አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አህመድ መሐመድ ዛሬ ያስረከቡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙላት ገዛኸኝ ናቸው። በርክክብ ሥነስርዓቱ ላይ አቶ ሙላት ገዛኸኝ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጦርነቱ የወደሙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ከመጠገን ጎን ለጎነ የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች በጦርነቱ የተፈናቀሉ ወገኖችን ለመርዳት 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር ግምት ያለው የዓይነት እንዲሁም 3 ሚሊዮን ብር የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አድርገዋል። ተቋሙ ሠራተኞቹን በማስተባበር ያደረገው የዓይነት ድጋፍ የህፃናት አልሚ ምግብ፣ መኮረኒ፣ ዱቄት፣ አልባሳትና የንጽህና መጠበቂያ ቁሶችን ያካተተ ነው። የክልሉ የፋይናንስና ኢኮኖሚ ቢሮ ኃላፊና የሀብት አሰባሳቢ ኮሚቴ ሰብሳቢ በካሳጊታ፣ ቡርቃና ኤሊ ውሃ አካባቢ በተደረገው ጦርነት ከአንድ ወር ከሃያ ቀን በላይ በክልሉ ኤሌክትሪክ ሲቋረጥ ክልሉ ለጀነሬተር ነዳጅ ወጪ ከ9 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ አድርጓል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከፍተኛ የኤሌክትሪክ መሰረተልማቶችን በፍጥነት በመጠገን ከአፋር ህዝብ ጎን መቆሙን በተግባር በማሳየቱ አመስግነዋል። አሁን በህወኃት ጦርነት የተከፈተባቸውና የተወረሩ አካባቢዎች ነፃ ሲወጡ እንደ ከዚህ ቀደሙ ድጋፉ እንደማይለየን እምነት አለን ሲሉ ተስፋቸውን ገልፀዋል። በክልሉ የዞን ሁለት አምስት ወረዳዎች ብቻ ከሦስት መቶ ሺህ ሰው በላይ ተፈናቅሎ እርዳታ እንደሚፈልግ ኃላፊው ገልፀዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ቀደም ሲል በአማራ ክልል በጦርነቱ ለተፈናቀሉ ወገኖች ሰባት ሚሊየን ብር የዓይነትና የገንዘብ ድጋፍ ማድረጉ ይታወሳል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 21 ቀን 2014 ዓ/ም

photo content
+7

በእሳት አደጋ የተነሳ ተቋርጦ የነበረው የወልድያ ከተማና አካባቢያው ዳግም ኤሌክትሪክ አግኝቷል ........///...... ከደሴ የኤሌክትሪክ ማከፋፈያ ጣቢያ እስከ ወልድያ ማከፋፋያ ጣቢያ በተዘረጋው የ66 ኪ.ቮ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ በደረሰ ቃጠሎ የተነሳ የተቋረጠው ኤሌክትሪክ የወልዲያ ከተማና አካባቢው ዳግም ኤሌክትሪክ አግኝቷል። ትናንት የደረሰውን የኤሌክትሪክ ምሰሶ ቃጠሎ በሌላ በመተካት ወልድያ፣መርሳ፣ ውጫሌ እና አካባቢያቸ ዳግም ኤሌክትሪክ እንዲያገኙ ርብርብ ሲደረግ ቆይቶ ወልዲያ ከደቂቃዎች በፊት ኤሌክትሪክ ማግኘት ችላለች። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮች የቴክኒክ ድጋፍ ኃላፊ አቶ ተስፋዬ መንግስቴ እንደገለፁት ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል ማግኘት እንዲችሉ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ምሰሶና ሌሎች ግብዓቶችን ሲያቀርብ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎች የቴክኒክ ሥራዎችን በመስራት ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል። በአሁኑ ሰዓት ወልዲያ ኤሌክትሪክ ማግኘት የቻለች ሲሆን በየደረጃው ሌሎች ከተሞችም ኤሌክትሪክ እንደሚያገኙ ኃላፊው ገልፀዋል። በጥገናው ላይ ርብርብ ሲያደርጉ የቆዩት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለሙያዎች መሆናቸው እየታወቀ የወልድያ ዲስትሪክት ሠራተኞች ሥራውን እንደሰሩ የተገለፀበት አግባብ ትክክል ባለመሆኑ እንዲታረምና ህብረተሰቡም ይህን እንዲረዳ አቶ ተስፋዬ አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 20 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+5

በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ሰነድ ተፈረመ ......../////....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የጂኦ ስፓሻል ኢንፎርሜሽን ኢንስቲትዩት የጂኦ ስፓሻል መረጃ ለመለዋወጥና በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸው የመግባቢያ ሥምምነት በዛሬው እለት ተፈራርመዋል፡፡ የመግባቢያ ሰነዱን የፈረሙት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ እና የጂኦ ስፓሻል ኢንፎርሜሽን ኢንስቲቱዩት ዋና ዳሬክተር ዶ/ር ቱሉ በሻ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አሸብር ባልቻ በፊርማ ሥነ - ሥርዓቱ ላይ እንደተናገሩት ተቋሙ ከዳሰሳ ጥናት አንስቶ እስከ ፕሮጀክት ትግበራው ድረስ ለሚያከናውነው ሥራ የጂኦ ስፓሻል ቴክኖሎጂ ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው። ቴክኖሎጂውን በአግባቡ መጠቀም ወጪ ቆጣቢ በሆነ መልኩ ለመስራት እና በተገቢው ሁኔታ ለማስተዳደር ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ተናግረዋል ፡፡ የትብበር ስምምነቱ በሀገር ውስጥ ያለውን አቅም አስተባብሮ ተቀራርቦ በመስራት የሀገር ሀብትን በተገቢው ሁኔታ ለመጠቀም፣ የእውቀት ሽግግርና የአቅም ግንባታ ሥራዎችን በሁለቱ ተቋሟት ለማስፋፋት ጠቀሜታው የጎላ ነው ብለዋል። የመግባቢያ ሥምምነቱ ሁለቱ ተቋማት በመረጃ በመረጃ ልውውጥ፣ በቴክኖሎጅ ሽግግር፣ በምርምርና ልማት ተቋማቱ በሚያከናውኗቸው ፕሮጀክቶች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል እንደሚያስችል በመድረኩ ላይ ተገልጿል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዱዓለም ሲኣ በበኩላቸው የመግባቢያ ሰነዱ የዘርፉን አቅም ለማገዝ፣ የግንባታ ሄደቶችን ለመከታተል እንዲሁም የኃይል ማመንጫ፣ ማስተላለፊያ መስመሮችና የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽን ሥራ በዲጂታል ቴክኖሎጂ መረጃ አሰባስቦ አስፈላጊውን ሥራ ለማከናወን ያግዛል ብለዋል፡፡ በዚህም ተቋሙን ወደ ፊት የሚያራምድ እና ዓለም አቀፍ ከሆኑ ተመሳሳይ ተቋማት የሚሰሩትን አሰራር ለመተግበር እንደሚያስችል አቶ አንዱዓለም ገልጸዋል፡፡ የጂኦ ስፓሻል ኢንፎርሜሽን ኢንስቲቱዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ቱሉ በሻ በበኩላቸው የኃይል ዘርፉን መሰረተ ልማት ማዘመን ሃገራችን በቀጣይ 10 ዓመታት ለማሳካት ላቀደቸው ሁለተናዊ እድገት ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡ በመሆኑም ተቋማቸው ያለውን የካበተ ልምድ ለማከፈል እና አብሮ ለመስራት እድል በማገኘቱ መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡ የትብብር ስምምነቱ ከኢነርጂ ተደራሽነት ጋር በተያያዘ የብሔራዊ የሀብት ጠቋሚ መረጃ (resource mapping) ፣ የብሔራዊ የመሰረተ ልማት የመረጃ ልውውጥ፣ የሶፍት ዌር ማበልፀግና የኢንፎርሜሽን ደህንነት አገልግሎት፣ የስልጠናና ልምድ ልውውጥ፣ የሳይንሳዊ ዕውቀት፣ የቴክኖሎጂ እና መረጃ ልውውጥ እንዲሁም ውጤታማ የጂኦ ስፓሻል መረጃ አያያዝና አተገባበር ላይ በጋራ ለመስራት እንደሚያስችል በመርሃ ግሩ ላይ ተጠቁሟል ፡፡ በፊርማ ሥነ-ስርአቱ ላይ ከጂኦስፓሻል ኢንፎርሜሽን ኢንስቲቱዩት የመጡ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሞያዎች ጂኦ ስፓሻል ለኃይል ዘርፍ የሚኖረውን ጠቀሜታ በተመለከተ ገለፃ አድርገዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥር 20 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+5

የሚዲያ ጥቆማ /ለሁሉም መገናኛ ብዙሃን/ ……..////…… በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በጂኦስፓሻል ኢንፎርሜሽን ኢንስቲትዩት መካከል ጥር 20 ቀን 2014 ዓ.ም ሜክሲኮ በሚገኘው የኢ. ኤ. ኃ. ዋና መስሪያ ቤት ከጧቱ 3:00 ሰዓት ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት ይፈረማል። በፊርማ ሥነስርዓቱ ላይ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ይገኛሉ። በመሆኑም በተጠቀሰው ቀን፣ ቦታ እና ሰዓት ተገኝታችሁ የዜና ሽፋን እንድትሰጡን በአክብሮት እንጠይቃለን።