ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 548 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 340,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 158

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 548 名订阅者。

根据 26 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.05%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.01% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 053 次浏览,首日通常累积 2 491 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 27 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 548
订阅者
-724 小时
+147
+2730
帖子存档
በትግራይ በአንዳንድ አካባቢዎች የኃይል መቋረጥ ይኖራል .........///........ ወደተከዜ የኃይል ማመንጫ ግድብ የሚገባውን ውሃ በማስተንፈስ ሂደት የጣቢያው ዩኒቶች  ሥራ በማቆማቸው በትግራይ አንዳንድ አካባቢዎች የኃይል መቋረጥ ሊኖር ይችላል። ከግድቡ ውሃ ሲለቀቅ  የሚፈጠረው የእንፋሎት ጭጋግ በትራንስፎርመሮችና የኃይል ማመንጫ ቤቱ ላይ ጉዳት እንዳያስከትል ሁለቱ ዪኒቶች እንዲቆሙ ተደርጓል። በዚህ የተነሳ  የቮልቴጅ መዋዠቅ በማጋጠሙ በትግራይ ክልል አንዳንድ ከተሞች የኃይል መቋረጥ  ያጋጥማል። የክረምቱ ዝናብና ወደ ግድቡ የሚገባው የውሃ መጠን እስከሚቀንስ ድረስ ችግሩ ለቀናት የሚቀጥል በመሆኑ የኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁና ሌሎች አማራጮችን እንዲጠቀሙ እናሳስባለን። በዚህ አጋጣሚ ከግድቡ በላይኛውና በታችኛው ተፋሰስ በሚገኙት በጣንቋ፣ አበርገለ፣ በቆላ ተንቤን፣ በላዕላይ እና ታህታይ ማይጨው፣ በመረብለኸ፣ በአስገደ ጽንበለ፣ በላዕላይና ታህታይ አዲያቦ፣ በመደባይ ዛና፣ በታህታይ ቆራሮ፣ በአጠቃላይ የተከዜ ወንዝ ተዋሳኝ በሆኑ ወረዳዎች ነዋሪዎችና የመስተዳድር አካላት አስፈላጊውን ጥንቃቄ እነወዲያደርጉ ጥሪያችንን እናቀርባለን። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሎየር 1ኛ የስራ መደብ መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከላይ ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ
+2
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሎየር 1ኛ የስራ መደብ መጋቢት 11 ቀን 2016 ዓ.ም በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣው ማስታወቂያ መሰረት ከላይ ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ነሐሴ 23 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት በሚገኘው የድርጅቱ ዋና መ/ቤት የስብሰባ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 14 ቀን 2016 ዓ.ም

ለወርቅ ማዕድን ማምረቻ ፕሮጀክት ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል ስምምነት ተፈረመ ........///.......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኩርሙክ የወርቅ ማምረቻ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራርሟል፡፡ ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የኩርሙክ ወርቅ ማምረቻ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ብሮክስ ወርቁ ተፈራርመዋል፡፡ በኢትዮጵያ ኤሌክትክ ኃይል የገበያና ቢዝነስ ልማት መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሕይወት እሸቱ ስምምነቱን አስመልክተው እንደተናገሩት ከኩባንያው ጋር የተካሄደው ስምምነት ለ12 ዓመታት የሚቆይና 35 ሜጋ ዋት ኃይል ለማቅረብ የሚያስችል ነው፡፡ የኃይል አቅርቦት ስምምነት ክፍያው በዶላር እንደሚፈፀም ገልፀው ይህም የተቋሙን የውጭ ምንዛሬ በማሳደግ በኩል ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው አስታውቀዋል፡፡ እንደ አቶ ሕይወት ገለፃ ስምምነቱ ከኃይል አቅርቦት ባለፈ ለወርቅ ማምረቻ ፕሮጀክቱ ኃይል ለማቅረብ የሚያግዘውን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የዲዛይን እና የግንባታ ሥራዎችን በማከናወን ለተቋሙ ተጨማሪ ገቢ የሚያገኝበትን ዕድል ይፈጥራል፡፡ ይህም ተቋሙ በኃይል መሰረተ ልማቶች ግንባታ ሥራ ላይ ያለውን ተወዳዳሪነት ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ በሀገሪቱ እየተከናወኑ ለሚገኙ የተለያዩ ዘርፎች አስተማማኝ ኃይል በማቅረብ የኢንቨስትመንት ሥራዎችን በመደገፍ ሃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝም ተመላክቷል፡፡ የኩርሙክ ወርቅ ማምረቻ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ብሮክስ ወርቁ በበኩላቸው ከተቋሙ ጋር የተደረገው ስምምነት ፕሮጀክቱን እውን ለማድረግ ለኩባንያው እንደ ትልቅ ስኬት የሚቆጠር ነው ብለዋል፡፡ ስምምነቱ ፕሮጀክቱ ወደ ሥራ ሲገባ አስተማማኝ ኃይል ለማግኘት እንደሚያስችለው ጠቅሰው ተቋሙ በስምምነቱ መሰረት ኃይል ማቅረብ እንደሚኖርበትም አስገንዝበዋል፡፡ የወርቅ ማምረቻ ፋብሪካውን በ2018 ዓ.ም ወደ ሥራ ለማስገባት ዕቅድ እንደተያዘለት የተናገሩት ዋና ሥራ አስኪያጁ በአሁኑ ወቅትም ለፕሮጀክቱ ግንባታ የሚያስፈልጉ ነገሮችን ወደ ቦታው የማጓጓዝ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ ብለዋል፡፡ ዘጠኝ ቶን የሚጠጋ ወርቅ የማማረት አቅም ይኖረዋል የተባለው እና የ500 ሚሊዮን ዶላር ፕሮጀክት እንደሆነ የተነገረለት ይህ የወርቅ ማምረቻ ፋብሪካ በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ኩርሙክ ወረዳ የሚገነባ መሆኑንም አቶ ብሮክስ ተናግረዋል፡፡ የወርቅ ማምረቻ ፋብሪካው ተጨማሪ የኃይል ፍላጎት ሲኖረው በአቅርቦቱ እና በዋጋው ላይ ማሻሻያ እንደሚደረግበት በውሉ ላይ መካተቱንም የሥራ ኃላፊዎቹ አስታውቀዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 13 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+6

የማከፋፊያ ጣቢያው የኢንቨስትመንት ፍሰቱን ጨምሯል .....//...... የቡኢ ማከፋፊያ ጣቢያ የከተማዋንና የአካባቢውን ኢኮኖሚያዊ እድገት እያፋጠነ መሆኑን የቡኢ ከተማ አስተዳደር ገለጸ። የአስተዳደሩ ከንቲባ አቶ በለጠ ጫካ እንደገለጹት የቡኢ ማከፋፊያ ጣቢያ ከመገንባቱ በፊት ከተማዋ የኃይል አቅርቦት ከቡታጅራ ማከፋፊያ ጣቢያ ስታገኝ የነበረ ሲሆን ይህም በከተማዋና አካባቢው የሚመጡ የኢንቨስትመንት ጥያቄዎችን ተቀብሎ ለማስተናገድ እንቅፋት ፈጥሮ ቆይቷል። የቡኢ ባለ 132 ማከፋፊያ ጣቢያ ከተገነባ ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ ግን የአካባቢው የኢንቨስትመንት ፍሰት እና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል። በዚህም ከፍተኛ ኃይል የሚጠይቁ ከ40 በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፍቃድ ወስደው 6ቱ ወደ ማምረት ሲገቡ ቀሪዎቹ ደግሞ በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል። አሁንም በከተማውና አካባቢው ያለውን አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ከግምት ውስጥ በማስገባት በርካታ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ጥያቄ እያቀረቡ መሆኑንም አቶ በለጠ አብራርተዋል። የአካባቢውን የመልማት አቅምና ፍላጎት ታሳቢ በማድረግ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት እንዲኖር በማድረጉ አመስግነዋል። የቡኢ ማከፋፍያ ጣቢያው የኦፕሬሽን ባለሙያ አቶ አይሸሹም አበረ በበኩላቸው የማከፋፍያ ጣቢያው የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 4 ከተሞችና 3 ወረዳዎች እንዲሁም አጎራባች የኦሮሚያ ክልል ወረዳዎችን የኃይል ተጠቃሚ ማድረጉን ገልጸዋል። ጣቢያው 45 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ያለው ሲሆን አሁን በጥቅም ላይ የዋለው ዘጠኝ ከመቶው ብቻ መሆኑን ጠቁመዋል። ይህም ቡኢ ከተማን ጨምሮ በአካባቢው በመገንባት ላይ ለሚገኙ ፋብሪካዎችም ሆነ በቀጣይ ለሚመጡ ኢንቨስትመንቶች የኃይል አቅርቦት ጥያቄዎችን በአግባቡ ለመመለስ የሚያስችል አቅም ያለው መሆኑን ተናግረዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 13 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+9

ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ንፁህና ታዳሽ የኃይል ማዕከል ለመሆን ካላት ራዕይ ጋር የሚጣጣም ነው ........///.......... የአይሻ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በቀጣይ ለሚተገበሩ የታዳሽ ኃይል ፕሮጀክቶች ማሳያ መሆን እንደሚችል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። ተቋሙ አሜአ ፖወር ከተሰኘው የተባበሩት አረብ ኢመሬቶች ኩባንያ ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ግዥ ሥምምነት ሲፈራረም ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ንፁህና ታዳሽ የኃይል ማዕከል ለመሆን ካላት ራዕይ ጋር የሚጣጣም ነው። መንግሥት ለቱሪዝም ዘርፉ፣ ለኮሪደር ልማቱ እና ለጤናማ የኑሮ አካባቢዎች መስፋፋት ትኩረት በመስጠቱ ምክንያት የኃይል ፍላጎት እያደገ መምጣቱን ኢንጂነር አሸብር ተናግረዋል። የኢነርጂ ዘርፉ ለሀገሪቱ የኢኮኖሚ ዕድገት መፋጠን፣ የኑሮ ደረጃ መሻሻልና ለዘላቂ የልማት ግቦች መሳካት ከፍተኛውን ድርሻ እየተወጣ እንደሚገኝም ነው የጠቆሙት። ተቋሙ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ለመጣው የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ምላሽ ለመስጠት በርካታ የልማት ሥራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን ተናግረዋል። እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ ኢትዮጵያ ለታዳሽ ኃይል ባላት ቁርጠኝነት መሠረት በንፋስ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ላይ በንቃት እየተሳተፈች ነው። የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የዚሁ ዕቅድ አካል መሆኑንም ነው የገለፁት። ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ላይ መሰረት ላደረገ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ስትራቴጂዋ ተጨማሪ ግብዓት ይሆናል ብለዋል። የንፋስ ኃይል ማመንጫ ግንባታው ሲጠናቀቅ በዓመት በአማካኝ 1 ሺህ 261 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል እንደሚያመነጭም ነው የጠቀሱት። በታዳሽ ኃይል ልማት፣ ግንባታና አስተዳደር ዘርፍ የተሰማራው አሚአ ፓወር በአይሻ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ 300 ሜጋ ዋት በማመንጨት ለ25 ዓመታት ለኢትዮጵያ ለመሸጭ ነው ሥምምነቱን የፈረመው። ሥምምነቱ ከዳር እንዲደርስ ላደረጉት አካላት ምስጋናቸውን ያቀረቡት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጥረቱ በትብብርና በጋራ የማደግን አስፈላጊነት ያሳየ ነው ብለዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 12 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

photo content
+7

የፕሮጀክቱ ሠራተኞች ከ3 ሺህ በላይ ችግኞችን ተከሉ ........///...... የበቆጂ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ቋሚና ጊዜያዊ ሠራተኞች በፕሮጀክቱ ሳይት የአረንጓዴ አሻራቸውን አኑረዋል። ሠራተኞቹ የተለያየ ዝርያ ያላቸው ከ3 ሺህ በላይ ችግኞችን በመትከል አሻራቸውን አኑረዋል። የፕሮጀክቱ የሳይት ኃላፊ እንዳልካቸው ጃምቦ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ሠራተኞች የአረንጓዴ አሻራ ተሳታፊ በመሆን ለታዳሽ ኃይል ልማት አስተዋጽኦ ማበርከት ይጠበቅባቸዋል። ዛሬ የሚተከሉት ችግኞች ነገ ሀገራዊ የደን ሽፋንን በማሳደግ የአየር ንብረትን ለማስተካከልና ምቹ የሥራ ቦታ ለመፍጠር ያግዛሉ ብለዋል። የፕሮጀክቱ ሰራተኞች ችግኞቹን ለግማሽ ቀን ሲተክሉ እንደዋሉ ኃላፊው ገልፀዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

photo content
+9

የኃይል ግዥና የፕሮጀክት ትግበራ ሥምምነት ተፈረመ .........///........ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አሜአ ፓወር ከተሰኘ የተባበሩት አረብ ኢሜሬቶች ኩባንያ ጋር የኃይል ግዥ ሥምምነት ተፈራረመ። የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ትግበራ ይፋ ለማድረግ በተዘጋጀው የፊርማ ሥነ-ሥርዓት ላይ አልሚው አሜአ ፓወር ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር የፕሮጀክት ትግበራ አጋርነት እንዲሁም ከሶማሌ ክልል መንግስት ጋር የመሬት ሊዝ ሥምምነት ተፈራርሟል። የኃይል ግዢ ሥምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና በአሜአ ፓወር ኩባንያ የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ራጂሽ ራሚሽ ተፈራርመዋል። በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ወቅት ንግግር ያደረጉት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ ኢትዮጵያ በኢኮኖሚው ዘርፍ ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ዕድገት በማስመዝገብ ላይ ትገኛለች ብለዋል። በአሁኑ ወቅት ወደ ተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፓሊሲ ትግበራ መገባቱን የገለፁት ሚኒስትሩ በዘርፉ ሁለንተናዊ ብልፅግናን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰዋል። እንደ አቶ አህመድ ገለፃ የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ እና የተባበሩት አረብ ኢሜሬቶች ከዚህ ቀደም በተለያዩ መስኮች ያላቸውን ሁሉን አቀፍ ትብብርና ግንኙነት የሚያጠናክር ነው። ፕሮጀክቱ ኢትዮጵያ በአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን እያከናወነቻቸው ላሉ ተግባራት ማሳያ እንደሆነም ነው አቶ አህመድ የገለፁት። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ኢትዮጵያ የኢኮኖሚ አቅሟን ለማጠናከር በነደፈቻቸው የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን፣ የኢንዱስትሪ እና የከተሞች መስፋፋት ዕቅዶች ፈጣን ለውጥ እያስመዘገበች ትገኛለች። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሦስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ቀርፆ ተግባራዊ በማድረግ ላይ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል። የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የዚሁ ዕቅድ አካል መሆኑንም ተናግረዋል። እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ ሥምምነቱ ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ላይ መሰረት ላደረገ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ስትራቴጂዋ ተጨማሪ ግብዓት ይሆናል። የንፋስ ኃይል ማመንጫ ግንባታው ሲጠናቀቅ በዓመት በአማካኝ 1 ሺህ 261 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል እንደሚያመነጭም ነው የጠቀሱት። በአሜአ ፓወር የአይሻ 1 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ሚስተር ራጂሽ ራሚሽ በበኩላቸው የተባበሩት አረብ ኢሜሬቶች ለኢትዮጵያ ሁለንተናዊ የኢኮኖሚ ዕድገት የበኩሉን ድርሻ እንደሚወጣ ተናግረዋል። ፕሮጀክቱ ለ1 ሺህ 500 ዜጎች የሥራ ዕድል ይፈጥራል ያሉት ሥራ አስኪያጁ ኃይል ማመንጨት በሚጀምርበት ወቅትም ከ4 ሺህ በላይ ለሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ ያስችላል ብለዋል። በገንዘብ ሚኒስቴር የመንግሥትና የግል አጋርነት ቦርድ ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር አቶ አበበ ገ/ህይወት በበኩላቸው ፕሮጀክቱ በዓመት 690 ቶን የካርበን ልቀትን የማመጣጠን አቅም አለው። ከኩባንያው ጋር የተደረገው ሥምምነት ከፕሮጀክት ሥምምነት በላይ አድርገን የምናስበውና ለቀጣይ ኢንቨስትመንት መሰረት የሚጥል ነውም ብለዋል። ፕሮጀክቱ በመንግሥት እና የግል አጋርነት ማዕቀፍ በ620 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የሚገነባ ትልቅ ኢንቨስትመንት እንደሆነም ነው ዋና ዳይሬክተሩ የጠቆሙት። በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የገንዘብ ሚኒስትር አቶ አህመድ ሸዴን ጨምሮ የገንዘብ ሚኒስቴር ሚኒስቴር ዴኤታዎች፣ የመንግሥትና የግል አጋርነት ቦርድ አባላትና የጽ/ቤት ሠራተኞች፣ የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ተወካዮች፣ የመንግሥት የልማት ድርጅቶ ይዞታና አስተዳደር ዋና ዳይሬክተርና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎች፣ የተባበሩት አረብ ኢሜሬቶች ከፍተኛ የመንግሥትና የአሜአ ፓወር የሥራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 11 ቀን 2016 ዓ.ም

በመላ ሀገሪቱ የሲስተም ማሻሻያ ሥራ እየተከናወነ ነው ......///...... በመላው ኢትዮጵያ የሲስተም ማሻሻያ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል አስታወቀ። ማዕከሉ እንደገለፀው በሚከናወነው የሲስተም ማሻሻያ ሥራ በአንዳንድ የሀገሪቱ ክፍሎች ከፍተኛ የኃይል ጭነት በሚበዛባቸው ሰዓታት ዛሬና ነገ የኃይል መቋረጥ ሊያጋጥም ይችላል። በመሆኑም የኤሌክትሪክ ተጠቃሚ ደንበኞች በሙሉ ችግሩን ተረድተው በትግዕስት እንዲጠብቁና ሌሎች ጊዜያዊ አማራጮችን እንዲጠቀሙ ማዕከሉ ጥሪ አቅርቧል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

የአይሻ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ ስምምነት ሊፈረም ነው ......///...... በኢትዮጵያ ከንፋስ ኃይል በማመንጨት አቅሙ ትልቁ የሆነውን የአይሻ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ግንባታ ለማስጀመር የሚያስችል ሥምምነት ሊፈረም ነው፡፡ ዛሬ እንደሚፈረም የሚጠበቀው የሦስትዮሽ የፊርማ ሥነ-ሥርዓት በገንዘብ ሚኒስቴር እና በአልሚው አሜአ ፓወር እንዲሁም በአልሚው እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መካከል የሚካሄድ ነው፡፡ 300 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ በሶማሌ ክልል አይሻ ወረዳ ላይ ይገኛል። ፕሮጀክቱ በመንግሥት እና በግል አጋርነት ማዕቀፍ የሚገነባ ትልቁና የመጀመሪያው ኢንቨስትመንት ይሆናል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+1

photo content